Quantcast
Channel: Amharic News & Opinion
Viewing all articles
Browse latest Browse all 13695

ትግሉን ይቀላቀሉ ፣ ተመልካች ሳይሆን ተሳታፊ ይሁኑ !

$
0
0

የካቲት 16 በሚደረገዉ የባህር ዳር ሰልፍ፣ መኢአድ እና አንድነት በጋራ የጠሩት ነዉ። ድርጅቶች እንዲህ ሲተባበሩ ያስደስታል። የተናጥል የብቻ ጉዞ የትም አይደርስምና።

ይህ ሰልፍ ምንም እንኳን የብሃአዴን አንድ አመራር አባል ለፍርድ እንዲቀርቡ የሚጠይቅ ቢሆንም፣ ጉዳዩ ከአንድ ግለሰብ ያለፈ መሆኑን መረዳት አለብን። ባለስልጣኑ ጸያፍና ነውረኛ አስተያየት ሰጡ የሚል ክስ ሲቀርበባቸው ፣ ገዚው ፓርቲ ፣ ግድ የለም፣ አሁኑኑ አይቅጣቸው፣ ቢያንስ ቢያንስ ግን «ጉዳዩን እመረምራለሁ። የተባለዉ እዉነት ከሆነ አስፈላጋዉን እርማት እሰጣለሁ» ማለት ሲገባው፣ ነገሩን አድበስብሶ ማለፉ፣ ገዢው ፓርቲ ምን ያህል ሕዝብ በፓርቲ ደረጃ እንደሚንቅ፣ ከሕዝብ ክብር ይልቅ የካድሬዎቹ ደህንነት የሚያሳስበው እንደሆነ ያመላከተ ነዉ።

በመሆኑም የሚሊየነም ድምጽ ፌስቡክን፣ የምንከታተል ሁላችንም፣ በኤሜል ፣ በትዊተር ፣ በእጃችን ያሉ መንገዶችን ሁሉ በመጠቀም ቅስቀሳዉን እንቀላቀል። ከአንድ፣ መቶ፣ ከመቶ፣ ሺህ፣ ከሺህ ሚሊዮኖች ይበልጣሉና።

በባህር ዳር ፣ ዘመድ፣ ወዳጅ፣ ጓደኛ ያለን፣ ደዉለን ወደ ሰልፉ እንዲወጡ እናበረታታ። ለሰልፉ የሚያስፈልጉ ብዙ ወጪዎች አሉ። በገንዘባችን ድጋፍ እናድርግ። ጋዜጠኞች፣ የድህረ ገጽ ሃላፊዎች፣ የተለያዩ ሜዲያዎው፣ ሰልፉን ለሕዝባችን በማስተዋወቁ ረገድ ድጋፋቸዉን ያበርክቱ። ጸሃፊያን ብእራቸውን እንዲያነሱ፣ ስለሰላም፣ ስለዴሞርካሲ፣ ስለመበት፣ ለሕግ የበላይነት እንዲጽፉ እናበረታታለን።

የቻልን በአካል ሰልፉን እንቀላቀል። ያልቻልን በመንፈስ የትግሉ አጋር እንሁን። የሁላችን የሆነቸዋን አንዲ አገር በጋራ እናድናት።1689471_680135262045226_946826287_n


Viewing all articles
Browse latest Browse all 13695

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>