Quantcast
Channel: Amharic News & Opinion
Viewing all articles
Browse latest Browse all 13695

የአንድነት አመራሮች ጊዜ ቀጠሮ ተጠየቀባቸው

$
0
0

ዛሬ ማለዳ ሜክሲኮ በሚገኘው የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የቀረቡት የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ ሊቀመንበር፣የብሄራዊ ምክር ቤት አባሉ ዘላለም ደበበና ጋዜጠኛ ነብዩ ኃይሉ በፖሊስ የአስራ አራት ቀን የምርመራ ጊዜ ተጠይቆባቸው ፍርድ ቤቱ የአስራ አንድ ቀን ጊዜ ቀጠሮ ለፖሊስ በመፍቀድ በእስር ቤት እንዲቆዩ ተወስኖባቸዋል፡፡

ፖሊስ በአንድነት አባላት ላይ ባቀረበው ክስ ‹‹ለቅስቀሳ ባልተፈቀደ ቦታ ሲቀሰቅሱ አግኝቻቸዋለሁ፣የተፈቀደላቸው ለሰላማዊ ሰልፍ እንጂ ለቅስቀሳ አይደለም በማለት ዋስትና እንዲከለከሉለት ደግሞ ‹‹ካልታሰሩ ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን ሁከት ሊፈጥሩ የሚችሉ በመሆናቸው በእስር እንዲቆዩ ይደረግልኝ››ብሏል፡፡

ተከሳሾቹ በበኩላቸው ለፍርድ ቤት ባቀረቡት መከራከሪያ‹‹ፖሊስ ባላቸው ቦታዎች አለመቀስቀሳቸውን፣ሰልፉ እውቅና የተሰጠው በመሆኑ ሁከት መፍጠር የሚለው አያስኬድም ብለዋል፡፡ጋዜጠኛ ነብዩ ኃይሉ‹‹ሰላማዊ ሰልፉ በሸገር ሬዲዩ እየተዋወቀ ፖሊስ መቀስቀስ አትችሉም ማለቱ አስገራሚ ሆኖብኛል››ብሏል፡፡10312367_628946547190283_7908140656346366611_n

10178030_628946420523629_2210739366940698651_n

10330387_628946493856955_5799780776381331354_n


Viewing all articles
Browse latest Browse all 13695

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>