$ 0 0 ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በጥናታዊ የውይይት መርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው ቃለ ምዕዳን በሰጡበት ወቅት (ፎቶ: የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት) የለውጡ ቀንደኛ ተገዳዳሪዎች፣ ‹‹ጠላቶች ነበርን፤ ዛሬ የሰማነውና ያየነው ጥናት ግን መልካም ኾኖ አግኝተነዋል፤›› ሲሉ ራሳቸውን ሒስ አድርገዋል፤ ‹‹ቤተ ክርስቲያኒቱ የተወለደችው ዛሬ ነው፤›› ሲሉም የመዋቅርና አሠራር መመሪያ ጥናቱን አድንቀዋል፤ ጥናታዊ ውይይቱ በላቀ የለውጥ መነሣሣት ቀጥሏል፤ ከፍተኛ አመራሩ የተሳተፈበት የቀዳማይ ዙር ጥናታዊ ውይይት መርሐ ግብር ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡