ግርማ ካሳ
በሕዝብና በሀገር ላይ ጥቃት ሲሰነዘር የሀገሪቷ መሪ ህዝቡን የመምራትና የማረጋጋት ኃላፊነት አለባቸው። ሳዑዲዎች በኢትዮጵያውያን ላይ አሰቃቂ ግፍ በፈጸሙ ጊዜ፣ አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ፣ ከመምራት ይልቅ ዝምታን መርጠው፣ አንዴ በካታር፣ ሌላ ጊዜ በፖላንድ ሲሽከረከሩ እንደነበረ ሁላችንም የምናውቀው ነው። "ጠ/ሚኒስትሩ የት ነው ያሉት?" የሚል ጥያቄና ትችት እየጠነከረ በመጣ ጊዜ፣ ከሣምንታት በኋላ ብቅ አሉ። በኢቲቪ ቃለ መጠይቅም አደረጉ።