
በጎንደር ከተማ በነገው ዕለት የሚካሄደውን የሰማያዊ ፓርቲ የተቃውሞ ሠልፍ ቅስቀሳ ለማካሄድ እየተንቀሳቀሰ ያለው ቡድን ሥራውን ለማሰናከል በመንግስት የፀጥታ ሃይሎች ክትትል እና ወከባ እየተደረገበት ነው፡፡
እንደሚታወቀው የፓርቲው አመራሮች እና አባላት እራሳቸውን በተለያየ ቡድን በማደራጀት የመጡበትን ተልዕኮ ለማሳካት እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ በዚህም መሠረት በቅስቀሳው ላይ ያለው ቡድን በከተማው ልዩ ልዩ ስፍራዎች ስራውን እያከናወነ ሲገኝ ነገር ግን የመንግስት የፀጥታ ሃይሎች ቅስቀሳውን ለማደናቀፍ የተለያዩ ሙከራ በማድረግ ላይ ቢሆኑም እስካሁኑ ሰዓት ድረስ ቡድኑ በከፍተኛ ቆራጥነት አፈናውን ተቋቁሞ በመስራት ላይ ይገኛል ፡፡
በሌላ በኩል የነገውን ሠልፍ የተሳካ ለማድረግ ደግሞ ሌላው ቡድን ሌሎች የተለያዩ ዝግጅቶችን በማድረግ ላይ ሲሆን ባረፉበት ሆቴል ሀኖ ስራውን በመስራት ላይ የሚገኘውን ቡድን የደሕንነት እና የፖሊስ ሃይሎች ሆቴሉን በመክበብ ጫና ለማሳደር ዛቻ እና ማስፈራሪያ እያደረሱበት ነው፡፡