Quantcast
Channel: Amharic News & Opinion
Viewing all articles
Browse latest Browse all 13695

ትብብር ለዲሞክራሲ አመራሮች ከመኢአድ እና አንድነት ጋር በባህር ዳር እየቀሰቀሱ ናቸው

$
0
0

የአሥር ድርጅቶች ስብስበ የሆነው ትብብር ለዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ አመራር አባላት ከመኢአድ እና አንድነት ጋር በመሆን በባህር ዳር ቅስቀሳ እያደረጉ እንደሆነ የደረሰን ዘገባ ያመልክታል።

የትብብሩ መስራች ድርጅቶች ዉስጥ የሐዲያ ብሔር አንድነት ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ፣የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ፣ የሶዶ ጎርደና ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት፣ የከምባታ ሕዝቦች ኮንግሬስ ፣ የኦሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ኅብረት፣ የመላው ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፣የመላው ዐማራ ሕዝብ ድርጅት፣ የጌዴኦ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ፣የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ ይገኙበታል።

የባህር ዳሩን ሰልፍ መኢአድ እና አንድነት በጋራ ከመስራታቸውም ባሻገር ፣ ሌሎች ድርጅቶችን ማሳተፋቸው ፣ በራሱ ትልቅ ዉጤት መሆኑን የሚናገሩ ጥቂቶች አይደሉም። በተለይም ድርጅቶች በወረቀት ላይ ሳይሆን፣ በሥራ ትብብራቸውን ማሳየታቸዉ ሕዝብ በተቃዋሚዎች ላይ ያለዉን አመኔታ የበለጠ እንዲጨምር የሚያደርግ ነው።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 13695

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>