በኦጋዴን አካባቢ የሚካሄደውን የነዳጅ ዘይት ቁፋሮ ኣጥብቆ እንደሚቃወም ኣማጺው የኦጋዴን ነጻ ኣውጪ ግንባር በምህጻሩ « ኦ ኤን ኤል ኤፍ » ኣስታወቀ። ኣንድ ኣንጋፋ የግንባሩ መሪ ለ« አይ ፒ ኤስ » የዜና አገልግሎት እንደገለጹት በኦጋዴን የሚገኘው የነዳጅ ዘይት ከለማ የኢትዮጵያን መንግስት ባለጸጋ ያደርገዋል።
↧