ዶ/ር ፍቅሬ ቶለሣ ጂግሳ
ይድረስ ለተከበሩ ዶ/ር በያና ሱባ፣ የኦሮሞ ዲሞክራሲ ግንባር አመራር አባል በአሉበት።
ይህን ደብዳቤ እንድጽፍልዎት ያነሳሱኝ ምክንያቶች ርስዎ በቅርቡ ለኢሳት ራዲዮ የሰጡት ቃለመጠይቅ እና አሁን ርስዎ የሚመሩት ከሣምንት በፊት የተቋቋመው "የኦሮሞ ዲሞክራቲክ ግንባር" የወሰዳቸው አቋሞች ናቸው። የርስዎ ቃለመጠይቅና የግንባሩ አዲስ አቋሞች በግሌ እንደአስደሰቱኝ በዚህ አጋጣሚ ልገልጽልዎ እወዳለሁ።