Quantcast
Channel: Amharic News & Opinion
Viewing all articles
Browse latest Browse all 13695

ሚሊየነች ድምጽ – ላስ ቬጋስ የአዲስ አበባዉን የመጀመሪያ ስብሰባ ስፖንሰር አደረገች!

$
0
0

ሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ በአገሪቷ ዉስጥ ባሉ አሥራ ሰባት ከተሞች፣ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች እንደሚያደርግ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ሕዝባዊ ስብሰባ በማድረግ የሚጀመር ሲሆን፣ በሌሎች ከተሞች ከአንድነት ጽ/ቤቶች ወደ አደባባይ በሚሄድ ትይንተ ሕዝቦች ይደረጋሉ።

addis_lasvegas-1

ላስ ቬጋስ፣ ኔቫዳ፣ ከአዲስ አበባ ጋራ ሶሊዳሪቲ በመመሰረት ፣ በዚያ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን፣ በአዲስ አበባ ለሚደረገዉ ሕዝባዊ ስብስበ የሚያስፈልገውን ወጭ ሙሉ ለሙሉ ለመሸፈን የተዘጋጁ ሲሆን፣ «ከሚሊዮኖች አንዱ ነን» እያሉም ነው።

ይህ የሚሊየነሞች እንቅስቃሴ የአንድ ፓርቲ እንቅሳቅሴ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ሕዝብ እንቅስቃሴ እንደመሆኑ፣ በአገራችን ዴሞክራሲና የስርዓት ለዉጥ እንዲመጣ የሚፈልጉ ዜጎች ሁሉ ሊቀላቀሉት፣ ሊደግፉት፣ የራሳቸው ሊያደርጉት የሚገባ እንቅስቃሴ ነዉ። ይህ እንቅስቃሴ የሚሊዮኖች እንቅስቃሴ ነው። የእያንዳንዳችን እንቅስቃሴ ነው።

በዳያስፖራ የሚሊየነሞች ግብረ ኃይል፣ በላስ ቬጋስ ያሉ ኢትዮጵያዉን ላሳዩት አኩሪና ኢትዮጵያዊ እንቅስቃሴ ያለዉን አድናቆት እየገለጸ፣ በሌሎች ከተሞችም የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እራሳቸውን እያደራጁ ፣ አገር ቤት ከፍተኛ መስዋእትነት እየከፈለ ካለው ሕዝብ ጎን እንዲቆሙ፣ ትግሉን እንዲቀላቀሉና ከሚሊዮኖች አንዱ እንዲሆኑ ጥሪ ያቀርባል።

በምትኖሩበት ከተማ ተደራጅታችሁ፣ ከዚህ ግብረ ኃይል ጋር በመስራት በአገር ቤት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን ስፖንሰር ማድረግ የምትፈልጉ፣ በሚከተሉት አድራሻ ሊያገኙን ይችላሉ።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር !

millionsforethiopia@gmail.com
404- 518-7858


Viewing all articles
Browse latest Browse all 13695

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>