Quantcast
Channel: Amharic News & Opinion
Viewing all articles
Browse latest Browse all 13695

ደብዳቤ አልቀበልም ያሉት ባለስልጣን ሊከሰሱ ነው! – አንድነት

$
0
0

‪#‎udj‬@addisabeba
የአዲስ አበባ የሰላማዊ ሰልፍና የፖለቲካ ስብሰባዎች ማሳወቂያ ክፍል ኦፊሰር የሆኑት አቶ ማርቆስ ብዙነህ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ላቀረበላቸው የሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ደብዳቤ ህገ ወጥ ምላሽ በመስጠታቸው ፓርቲው ደብዳቤውን የተቃወመበትን የህግ አግባብ በመጥቀስ ደብዳቤ ልኮላቸው ነበር፡፡

አቶ ማርቆስ በጽ/ቤታቸው በአካል የተላከላቸውን ደብዳቤ ምስክሮች ባሉበት ‹‹አልቀበልም ብትፈልጉ ክሰሱኝ››በማለት በህጋዊ መንገድ የቀረበላቸውን ደብዳቤ አልቀበልም በማለት መልሰዋል፡፡አንድነት ፓርቲ ሰዎች ሁሉ በህግ ፊት እኩል መሆናቸውንና በመንግስት የሃላፊነት ቦታ ላይ የተቀመጡ ሰዎችም ህዝቡን ማገልገል ቅሬታውንም ማድመጥ ግዴታቸው ጭምር መሆኑን በማመን ለአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል፡፡

መስተዳድሩ በቅርብ ቀናት ውስጥ በግለሰቡ ላይ ህጋዊ እርምጃ የማይወስድ ከሆነም ፓርቲው በመደበኛ ፍርድ ቤት ፍትህን እንደሚጠይቅ አስታውቋል፡፡10171151_700767163315369_1914484836_n


Viewing all articles
Browse latest Browse all 13695

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>