Quantcast
Channel: Amharic News & Opinion
Viewing all articles
Browse latest Browse all 13695

ፍኖት – በቃሊቲ እና በዝዋይ የሚገኙ ታሳሪዎች፣ የርሀብ አድማ ሊያደርጉ ነው!!

$
0
0

እስረኞቹ ህዝቡ በነቂስ በመውጣት የእሁዱን ሰላማዊ ሰልፍ እንዲቀላቀል ጥሪ አቅርበዋል!!

በቃሊቲና በዝዋይ ማረሚያ ቤቶች በግፍ ተፈርዶባቸው በእስር ላይ የሚገኙ የህሊናና የፖለቲካ እስረኞች፣ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ «የእሪታ ቀን» በሚል መሪ ቃል የሰየመውንና እሁድ ሚያዝያ 26 ቀን 2006 ዓ.ም የጠራውን ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ በማስመልከት፣ ከህዝብ ጎን ሆነን ድምፃችንን እንዳናሰማ በግፍ የተወረወርንበት እስር ቤት ቢያግደንም፣ ከአርብ ጀምሮ ሰላማዊ ሰልፍ እስከሚደረግበት እለት ድረስ የርሀብ አድማ በማድረግ ከህዝቡ ትግል ጎን በመቆም አጋርነታችንን እናሳያለን ሲሉ ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ፡፡

ህዝቡ ከየቤቱ በነቂስ በመውጣት ሰላማዊ ሰልፉን እንዲቀላቀልም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በቃሊቲ እና በዝዋይ ከታሰሩ የሕሊና እስረኞች መካከል፣ ጋዜጠኛ እስክንደር ነጋ፣ ጋዜጠና ርዮት አለሙ፣ አቶ አንዱዋለም አራጌ፣ አቶ በቀለ ገርባ ፣ አቶ ናትናኤል መኮንን፣ ጀነራል አሳምነው፣ አቶ አበበ ቀስቶ እንዲሁም ሌሎች በርካታኦች ይገኙበታል።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 13695

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>