የኮት ዲ ቯር የፍትሕ ሚንስቴር በእስር ከሚገኙት የቀድሞው የሀገሪቱ ርዕሰ ብሔር ሎውሮ ባግቦ ደጋፊዎች መካከል የቅርብ ረዳቶቻቸው ናቸው የሚባሉትን 14 ሰሞኑን በጊዜያዊ ሁኔታ ፈታ። ግለሰቦቹ የተፈቱበት ርምጃ በሀገሪቱ ለተጀመረው የዕርቀ ሰላም ሂደት ዓቢይ አስተዋፅዖ እንደሚኖረው ቢገምቱም፣ የባግቦ ደጋፊዎች በቂ እንዳልሆነ አስታውቀዋል።
↧