በመጪው እሁድ ነሃሴ 19 ቀን 2005 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ሊያደርግ የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ወደ ጷጉሜ 3 መዘዋወሩን የአንድነት ፓርቲ የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት ግብረ ኃይል ማምሻውን አስታወቀ፡፡ ግብረኃይሉ እንዳስታወቀው የአዳማ ከተማ አስተዳደር ለአንድነት ፓርቲ በፃፈው ደብዳቤ ነሃሴ 19 በከተማው ስብሰባ በመኖሩና የሀይል እጥረትም ስላለበት አንድነት ሰላማዊ ሰልፉን እንዲያስተላልፍ ጠይቋል፡፡ አንድነት ፓርቲም የቀረበለትን ጥያቄ ከግምት በማስገባት ሰልፉን ለጷጉሜ 3 ቀን 2005 ዓ.ም መዘዋወሩን የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት ግብረ ኃይል ማምሻውን አስታውቋል፡፡
#Millionsofvoicesforfreedom #Ethiopia #UDJ
↧
ሰበር ዜና ከአዳማ፤ ፍኖተ ነጻነት
↧