Quantcast
Channel: Amharic News & Opinion
Viewing all 13695 articles
Browse latest View live

አዲስ አበባ እና ጅማ ሌሊቱን በግድግዳ መፈክሮች ደምቀው አደሩ

$
0
0

ድምጻችን ይሰማ/ሰኞ የካቲት 3/2006

በትናንትናው ሌሊት በተለያዩ የአዲስ አበባ አካባቢዎች እና በጂማ ከተማ በርካታ የግድግዳ ላይ መፈክሮች ተጽፈው ማደራቸው ተዘገበ! በጂማ በራሪ ወረቀትም ተበትኗል!!!

በአዲስ አበባ ወደአስኮ በሚወስደው መንገድ በጀኔራል ዊንጌትና አካባቢው፣ እንዲሁም በጦር ሀይሎች መስመር እስከ ቤተል ድረስ ባሉ ቦታዎች በግድግዳዎች ላይ ተጽፈው ያደሩት እኒሁ መፈክሮች የሰላማዊ ትግሉን መንፈስ የሚያንጸባርቁና የህዝበ ሙስሊሙ መብት እንዲከበር፣ ታሳሪዎችም እንዲፈቱ የሚጠይቁ ነበሩ፡፡ ከተጻፉት መፈክሮች መካከል ‹‹ድምጻችን ይሰማ! ኮሚቴው ይፈታ! ህገ መንግስቱ ይከበር! የታሰሩት ይፈቱ!›› የሚሉት ጎልተው የወጡ መሆኑም ታውቋል፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ በጂማ ከተማም በግድግዳዎች ላይ በርካታ መፈክሮች ተጽፈው ማደራቸው የተዘገበ ሲሆን በከተማዋ ሌሊቱን እጅግ በርካታ በራሪ ወረቀት ተበትኖ ማደሩና የከተማዋ አስተዳደርም በሁኔታው መደናገጡን ማወቅ ተችሏል፡፡

ካሁን ቀደምም በተለያዩ ጊዜዎች ብሶቱን በግድግዳ ላይ ጽሁፎች (ግራፊቲ) ሲገልጽ የቆየው የኢትዮጵያ ህዝበ ሙስሊም ከሁለት አመታት በላይ በሰላማዊ መንገድ ሲታገል የቆየ ሲሆን የተለያዩ የሰላማዊ ትግል ዘዴዎችን በመጠቀምም ለመብቱ መከበር የሚያደርገውን ጥረት ቀጥሏል፡፡
muslim 2

 

muslim

muslim3

yesema dimstachin

yesema


አቶ አስራት ወደ ቅሊንጦ ወህኒ ቤት ተወሰዱ፤ ዳንኤል ተፈራ የፖሊስ መጥሪያ ደረሰው

$
0
0

አስራት ጣሴ

አስራት ጣሴ


በክስ ሂደት ላይ በሚገኘው የአኬልዳማ ዶክመንተሪ በድጋሚ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን መታየቱን ተከትሎ በአዲስጉዳይ መጽሔት ላይ አስተያየት የጻፉትና “በፍርድ ቤት ላይ ዘለፋ አዘል ጽሑፍ ጽፈዋል” ተብለው አርብ ጥር 30፣ 2006 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው የነበሩት አቶ አስራት ጣሴ ለቅጣት ውሳኔ 7 ቀናት ታስረው እንዲቆዩ የተወሰነባቸው መሆኑ የሚታወስ ሲሆን በዛሬው ዕለት ደግሞ ወደ ቂሊንጦ ተዘዋውረዋል ሲል አዲስ ጉዳይ መጽሔት ዘገበ።

የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዘጠነኛ ፍትሐብሔር ሁለተኛ የቤተሰብ ችሎት ጥር 21 ቀን 2006 ዓ.ም. ወጪ ባደረገው የትዕዛዝ ደብዳቤ አቶ አስራት ጣሴ በአዲስጉዳይ ሳምንታዊ መጽሔት ቅጽ 7 ቁጥር 198 የጥር ወር 2006 ዓ.ም. ዕትም ላይ ያቀረቡትን ‹‹… አሁን ደግሞ ከሰሞኑ ‘አኬልዳማ’ ድራማ በድጋሚ በተከታታይ እየቀረበና እየታየ ነው፡፡ ይህ እየሆነ ያለው አንድነት ፓርቲ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅትን በስም ማጥፋት ወንጀል በፍርድ ቤት ከሶ ገና ውጤት ባልተገኘበት ወቅት ነው፡፡ እሱም ፍትሕ ከኢሕአዴግ ፍርድ ቤቶች ይገኛል ተብሎ ሳይሆን፣ በታሪክ ምስክርነት እንዲመዘገብ ሲባል ነው፤›› የሚል ጽሑፍ ማስፈራቸውን በመግለጽ ፍርድ ቤት ቀርበው እንዲያስረዱ በፖሊስ በኩል መጥሪያ ልኮላቸዋል።

ፍርድ ቤቱ በትዕዛዝ ደብዳቤው ላይ ያሰፈረውንና አቶ አስራት በአዲስጉዳይ መጽሔት ላይ ጽፈውታል የተባለውን ጽሑፍ ‹‹ፍርድ ቤት ፍትሕ የማይሰጥ አካል መሆኑን የሚገልጽ ዘለፋ አዘል ጽሑፍ›› ሲል ገልጾታል፡፡

የአንድነት ፓርቲ በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን እና በአኬልዳማ ዶክመንተሪ አዘጋጅ ላይ ያቀረበው ክስ ሂደት በፍርድ ቤት በመታየት ላይ ቢሆንም የአኬልዳማ ዶክመንተሪ ፊልምን ጣቢያው በቅርቡ በድጋሚ ማስተላለፉ ይታወሳል፡፡

አሁን በደረሰን መረጃ መሠረት አቶ አስራት ጣሴ ከሦስት ቀናት እስር በኋላ ዛሬ ሰኞ የካቲት 3፣ 2006 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ወደ ቃሊቲ ቂሊንጦ እስር ቤት መዛወራቸው ታውቋል፡፡

ፍኖተ ነፃነት በበኩሉ የፖሊስ ምንጮቹ እንዳሉት አስራት በፖሊስ ጣቢያው በቆዩባቸው ጊዜያት በእስረኛው ተገቢው አክብሮትና መልካም አቀባበል ማግኘታቸው አሳሪዎቻቸውን አላስደሰተም፡፡ አንድነት ፓርቲን ከምስረታው ጀምሮ በከፍተኛ አመራርነት ሲያገለግሉ የቆዩትና በአሁኑ ወቅትም በፓርቲው ብሔራዊ ምክር ቤትና ስራ አስፈፃሚ የፓርቲዎችን ውህደት እንዲመሩና የአማካሪ ምክርቤት እንዲያቋቁሙ ኃላፊነት የተሰጣቸው መሆኑ ይታወቃል፡፡ አንድነት “የሚሊዮኖች ድምፅ ለፍትህ” በሚል መሪቃል የመንግስት የተለያጡ ሀላፊዎችን ለመክሰስ እንቅስቃሴ ማድረጉን ተከትሎ መንግስትም የአንድነት ፓርቲ አመራሮችን ምክንያት እየፈለገ መክሰስና ማሰር መጀመሩ ገዢው ፓርቲ አለመረጋጋት ውስጥ እንደገባ የሚያመላክት ነው፡፡

አቶ አስራት በፖሊስ ሲወሰዱ የሚያሳየው ቪድዮ ይመልከቱና ዜናው ይቀጥላል

በሌላ ዜና ዳንኤል ተፈራ ቃል እንዲሰጥ በፌደራል ፖሊስ መታዘዙን ፍኖተ ነጻነት ጨምሮ ዘገበ።

Daniel-Teferaየአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ የሆነው ወጣቱ ፖለቲከኛና ደራሲ ዳንኤል ተፈራ ማዓከላዊ ወንጀል ምርመራ በመቅረብ ቃሉን እንዲሰጥ በፌደራል ፖሊስ ታዟል፡፡ ፍኖተ ነፃነት ምንጮችን ዋቢ በማድረግ አቶ ዳንኤል ተፈራን ጨምሮ በአራት የአንድነት ፓርቲ አመራሮችና አባላት ላይ ክስ ለመመስረት ጥረት እየተደረገ መሆኑን መዘገቧ ይታወሳል፡፡

ይህ በ እንዲህ እንዳለ አንድነት ፓርቲ የአቶ አስራትን መታሰር ተከትሎ ባወጣው መግለጫው “የአቶ አሥራት ጣሴ እስር የኢህአዴግ የጉልበት ፖለቲካ ማሳያ ነው!” አለ። ሙሉው መግለጫ እንደወረደ፦

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ የተሠጠ መግለጫ

ፓርቲያችን አንድነት በተደጋጋሚ ከገዥው ፓርቲ ህግን ከለላ በማድረግ እና የመንግስትን ሥልጣን በመጠቀም የሚደርስበትን ከፍተኛ አፈና ተቋቁሞ የኢትዮጵያን ህዝብ ሉዓላዊ የስልጣን የበላይነት ለማረጋገጥ ትግሉን አጠናክሮ መቀጠሉ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡

በተለይም ፓርቲያችን በመላው የሀገራችን ክፍል የዘረጋውን መዋቅር በህዝባዊ አቅም ወደ ተሻለ ደረጃ በማሸጋገር በአምስት ዓመት ስትራተጂክ ዕቅዱ መሰረት እያከናወነ ያለው ህዝባዊ ንቅናቄ እና በተሳካ ሁኔታ ጠቅላላ ጉባዔ አካሂዶ ዴሞክራሲያዊ የአመራር ሽግግር ማድረጉ በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ ትልቅ ተስፋ ያሳደረ ቢሆንም ገዥውን ፓርቲ በአንጻሩ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንደከተተው ይስተዋላል፡፡

ኢህአዴግ ቀደም ሲል የፓርቲያችንን እንቅስቃሴ በመከታተል ከከፍተኛ አመራሮች መካከል አቶ አንዱዓለም አራጌ፤ ናትናዔል መኮንን እና ሌሎች በርካታ አባላትን የተለያየ ምክንያት ፈጥሮ እየወነጀለ ለእስር መዳረጉ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህም በድንገት የተደረገ ሳይሆን የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር እና የኢህአዴግ ሊቀመንበር አቶ መለስ ዜናዊ በግልጽ በፓርላማ ተገኝተው ‹‹አንድነት ፓርቲ እግር ሲያወጣ እግሩን እንቆርጣለን›› ባሉት መሰረት የፈጸሙት ነበር፡፡

አሁንም የራዕያቸው አስቀጣይ ነን የሚሉ የገዥው ኃይሎች ፈለጋቸውን ተከትለው የአውራ ፓርቲ (የአንድ ፓርቲ ስርዓት) ለመገንባት አንድነትን በጉልበት ፖለቲካ ማጥፋት እንደ ብቸኛ መንገድ ወስደው እየተረባረቡ ይገኛሉ፡፡ በመላው የሀገራችን ክፍል በርካታ አባሎቻችን ከስራ ተፈናቅለዋል፤ በግፍ ከሀገራቸው እንዲሰደዱ ተደርገዋል፤ ታስረዋል፤ ተደብድበዋል፡፡ ይህም በየጊዜው በፓርቲያችን ልሳን በመረጃ ተደግፎ ለህዝብ ይፋ የተደረገ ሲሆን፤ በአጠቃላይ በፓርቲያችን አመራር እና አባላት ላይ የተፈጸመውን የሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰት ባመላከትንበት ሪፖርትም ተካተቶ ለህዝብ ይፋ ተደርጓል፡፡

በተለይም የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት በሚል የተካሄደውን ህዝባዊ ንቅናቄ ተከትሎ ፓርቲያችን በተንቀሳቀሰባቸው አሥራ አንድ የሀገራችን ከተሞች ጉልህ ሚና የተጫወቱ እና በህዝብ ተቀባይነት ያላቸውን አባላት ምክንያት እየፈጠሩ እና የፍትህ ስርዓቱን የፖለቲካ መሳሪያ እያደረጉ ለእስር እና ለእንግልት መዳረጉን አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡

ኢህአዴግ ገና በጊዜ የጀመረው የ2007 ዓ.ም የምርጫ ዘመቻ የተለመደውን የጉልበት ፖለቲካ የተከተለ ሲሆን በቅርቡ በምዕራብ ሸዋ ዞን ለንሴቦ ወረዳ አቶ አለማየሁ ለሬቦ የተባሉ የሲተዳማ ዞን የአንድነት ስራ አስፈጻሚ በአዲስ አበባ ተገኝተው የፓርቲ ጉባኤ ተሳትፈው ሲመለሱ በቁጥጥር ስር ውለው ለ22 ቀናት ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ በእስር ቤት ከተሰቃዩ በኋላ መንግስትን ሰድበዋል የሚል ክስ ተመስርቶባቸው በዋስ ተለቀዋል፡፡ ይህንን ተከትሎ በየካቲት 30 ቀን የፓርቲያችን ከፍተኛ አመራር (የብሄራዊ ምክር ቤት አባል) የሆኑት አቶ አስራት ጣሴ ፍርድ ቤትን ዘልፈዋል ተብለው ለእስር የተዳረጉ ሲሆን ሌሎች አራት ከፍተኛ የፓርቲ አመራሮች ሊታሰሩ ሴራ እየተሸረበባቸው መሆኑን ምንጮች ለፓርቲያችን እያረጋገጡ ይገኛሉ፡፡

የፍትህ ስርዓቱን ዋነኛ የፖለቲካ መሳሪያ ያደረገው የኢህአዴግ መንግስት አቶ አስራት ጣሴን ለማሰር እንደ ምክንያት የተጠቀመው በአዲስ ጉዳይ መጽሄት 197 ቅፅ 7 ያወጡትን ጽሑፍ ሲሆን አጠቃላይ መልዕክቱም በኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ የሌለ መሆኑን፤ ህጎች አፋኝ መሆናቸውን፤ ኢ.ቲቪ የሰራቸው አኬልዳማ፤ ጀሃዳዊ ሃረካትና ሌሎች ለፖለቲካ ጥቃት ማድረሻ የተቀነባበሩ ድራማዎች ህገ ወጥ መሆናቸውን የሚገልጽ ነው፡፡ ይህ የፍትህ ጥያቄ ደግሞ አቶ አስራት ጣሴ ገና በጠዋት ለትግል የወጡበት፤ ከመሰሎቻቸው ጋር ሆነው አንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍት ፓርቲ እንዲመሰረት በርካታ መስዋዕትነት የከፈሉበት የፖለቲካ አላማቸው እና የፓርቲ አቋም መሆኑ ይታወቃል፡፡

‹‹የኢህአዴግ መንግስት ከሚመራቸው ፍርድ ቤቶች ፍትህ ይገኛል ብለን ሳይሆን ለታሪክ እንዲመዘገብ ወደ ፍርድ ቤት እንሄዳለን›› ሲሉም የግል ሃሳባቸው ብቻ ሳይሆን በብዙ አንቀጽ የተጠቀሰ የፓርቲያቸው አቋም ስለመሆኑም ማሳያ ነው፡፡ ከዚህም በላይ ኪሊማንጃሮ የተባለው ድርጅት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር በመንግስት ተቋማት ላይ ያደረገው ጥናት እንደሚያሳየው በህዝብ ከማይታመኑ ተቋማት መካከል ፍርድ ቤቶች በአንደኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡ ናቸው፡፡

ከነዚህ በህዝብ ከማይታመኑ ተቋማት ፍትህ አይገኝም ብሎ ማመን እና እምነትን መንገርም ሆነ መጻፍ ህገ መንግስታዊ መብት መሆኑ እየታወቀ በአካል ባልተገኙበት ችሎት በአካል ተገኝቶ ችሎትን ያወከ ወይም የዘለፈ በሚቀጣበት ፍታብሔር አንቀጽ 480 ቀርበው እንዲያስረዱ ከተጠሩ በኋላ ለእስር ተዳርገዋል፡፡ ይሁን እንጂ የተጠሩበት የፍታብሔር አንቀጽ የሚያዘው ጥፋታኛ ሆነው የተገኙ ቢሆን እንኳ በአነስተኛ የገንዘብ መቀጮ የሚቀጣ እንጂ ለእስር የሚያበቃ አልነበረም፡፡

ኢህአዴግ ይህንን እያደረገ ያለው ቀናቶች ወደ 2007 ዓ.ም ምርጫ እየገሰገሱ እና ፓርቲያችንም በህዝባዊ አቅሙ እየጎለበተ በመምጣቱ ካለቃቸው እንደተማሩት እግር ያወጣ ፓርቲያችንን እግር በመቁረጥ፤ አመራሩን ህግን ከለላ አድርገው ለእስር በመዳረግ፤ እንዳይጽፍ፤ እንዳይነገር እና በፍርሃት ቆፈን ተይዞ አንገቱን እንዲደፋ በማድረግ በምርጫ ሜዳው ከጀሌዎቻቸው ጋር ሩጠው አሸንፈናል ብሎ ለማወጅ የሚደረግ አስነዋሪ ዘመቻ ነው፡፡

ነገር ግን እንዲህ ያለው አምባገነናዊ ተግባር ትግላችንን የበለጠ አጠናክረን በመግፋት ሰላማዊ ትግሉ የሚጠይቀንን መስዋዕትነት ለመክፈል የሚያበረታን እንጂ ወደኋላ የማይመልሰን መሆኑን ዛሬም እንደ ትላንቱ ለመላው ህዝባችን እናረጋግጣለን፡፡

የፍትህ ስርዓቱም ከአንድ ፓርቲ ወገንተኝነት እንዲወጣ እና በግፍ የታሰሩ አመራሮቻችንንም በነጻ እንዲያሰናብት እንጠይቃለን !!!!

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!
የካቲት 1 ቀን 2006ዓ.ም

በአዲስ አበባ በሌሊት የሚጻፉ የተቃውሞ ጽሁፎች ቁጥር እየጨመረ ነው

$
0
0

የካቲት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከታህሳስ ወር 2006 ዓም ጀምሮ በመዲናዋ  ሌሊት የሚጻፉ  የተቃውሞ ጽሁፎችን ማየት የተለመደ እየሆነ መምጣቱን ነዋሪዎች ይናገራሉ።

ትናንት ሌሊት በአስኮ መስመር ጀኔራል ዊንጌት ከሚገኘው አደባባይ ጀምሮ አወሊያ፣ካኦጄጄ፣ አስኮ የሚወስደውን ዋና መንገዱን በመሃል በሚከፍለው እስከ 2.5 ሜትር ቁመት ባለው ግድግዳ ላይ የሙስሊሙን የመብት ጥያቄና የትግል ቀጣይነት የሚያንፀባርቁ ጽሁፎች በተለያዩ ቀለማት ተጽፈው ዛሬ ህዝብ ሲያነባቸው ታይቷል።

በአዲስ አበባ ጦር ሀይሎች፣ ወይራ ሠፈር ፣ አዉጉሥታ፣ቤቴል እና ሌሎችም አከባቢዎች ተመሳሳይ መልእክቶችን ያዘሉ ጽሁፎች ተለጥፈው ማደራቸውን ለማወቅ ተችሎአል፡፡

የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ጽሁፎችን በተመሳሳይ ቀለም ለማጥፋት ሙከራ እንደሚያደርጉ አልሆን ሲልም ስሚንቶ በመለጠፍ ለማጥፋት እንደሚሞክሩ ነዋሪዎች ይገልጻሉ።

በአዲስ አበባ የትራንስፖርት ችግሩ እንደተባባሰ ነው

$
0
0

የካቲት  ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በከተማው ውስጥ የሚገኙ የመንግስት ተሽከርካሪዎች ፣ የግል ባለንብረቶችና ባለታክሲዎች በመላ አገሪቱ የጠፋውን ነዳጅ ተከትሎ ነዳጅ ለማግኘት ላይ ታች እየተንከራተቱ ሲሆን፣  የነዳጅ መጥፋቱን  ተከትሎ የትራንስፖርት ታሪፊም  ጨምሯል። ዘጋቢያችን እንዳለው ዛሬ ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀስ 0.25 ሳንቲም ተጨማሪ ገንዘብ ለመክፈል ተገዷል፡

ነዳጅ ማደያዎችን ተዘዋውሮ የተመለከተው ዘጋቢያችን፣ በከተማው የሚገኙ ነዳጅ ማደያዎች ናፍጣም ሆነ ቤንዚን በማጠራቀሚያቸው  ውስጥ በበቂ ሁኔታ እንደሌለ እንደተገለጸለት ይህንን ተከትሎ የነዳጅ መሸጫ ዋጋ እንደጨመረ ገልጿል።

ከመኪና አገልግሎት ውጭ ነዳጅ እንዳትሸጡ ተብለው የታዘዙት የማደያ ባለቤቶች፣  ለመኪኖቹ በወረፋ ለማከፋፈል በሚያደርጉት ሙከራ፣ ነዳጅ መሸጫ ቦታዎች በመኪኖች ሰልፍ ለመጨናነቅ

የማዲያ ሽያጭ ሰራተኞች ሰልፉን መቆጣጠር ባለመቻላቸው በአካባቢ ፖሊስ እየታገዙ በማስተናገድም ላይ ናቸው፡፡

የከተማዋ ትራንስፖርት መስመሮችና መንገዶች በተለያያ አቅጣጫ ከቁጥጥር ወጭ በሆነ ሁኔታ እየተቆፈሩ በመሆኑ ብዙ መንገዶች በግንባታ ምክንያት ከፍተኛ የሆነ የትራንስፖርት መስመር መጨናነቅ አጋጥሟቸዋል።

የትራንስፖርት እጥረቱ በመንግስት ስራም ላይ  አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ መሆኑን የሚገልጸው ዘጋቢያችን፣ የመንግስት ሰራተኛው ከ4 ሰዓት በኋላ ስራ ለመግባት ተገዷል።

መንግስት ለነዳጅ መጥፋቱ የሰጠው ምክንያት የነዳጅ ማደያ ባለቤቶችን የሚያሳምን አልሆነም። የንግድ ሚኒስትሩ የነዳጅ አቅርቦት እትረት የተከሰተው አንዳንድ ነጋዴዎች በትርፍ ለመሸጥ በመፈለጋቸውና ኦይል ሊቢያ የተወሰኑ የነዳጅ መኪና ማመላለሻ ቦቴዎችን ለሌላ ድርጅት በማስተላለፉ ነው የሚል መልስ መስጠታቸው ይታወቃል።

የጀርመን የአፍሪቃ ፖሊሲ

$
0
0
የጀርመኑ የልማት ትብብር ሚኒስቴር ጌርድ ሙለር ባለፈዉ ዓርብ በአዲስ አበባ ከኢትዮጵያ መንግስትና ከአፍሪቃ ህብረት ባለስልጣናት ጋር ባደረጉት ውይይት አፍሪቃ በሀገራቸው የውጭ ፖሊሲ ላይ ትልቅ ትኩረት ማግኘቷን አስታወቁ። ሚንስትሩ እንዳስረዱት፣…

የሶቺ ኦሊምፒክ በሩሲያ

$
0
0
የኦሎምፒክ ውድድሮች ኣጀማመር፣ የታሪክ ድርሳናት እንደሚጠቁሙት፣ ከ2700 ዓመታት በፊት ነበር፣ ከክርስቶስ ልደት በፊት፣ 776 ዓ ዓለም ገደማ መሆኑ ነው፣ በጥንታዊቷ ግሪክ፣ ኦሎምፒያ በምትባል ከተማ።…

በጄዳ የኢትዮጵያ ዓ/ዓቀፍ ት/ቤት ችግር

$
0
0
በሺዎች የሚቆጠሩ ታዳጊ ኢትዮጵያዉያን እንደሚማሩበት የሚገለፀዉ በጅድ የኢትዮጵያ ዓለም ዓቀፍ ትምህርት ቤት ከተመሠረተ ከ15ዓመታት በላይ እንደሆነዉ ይነገራል።…

የአየር ኃይል አባሉ ም/መቶ አለቃ ዳንኤል የሽዋስ ሥርዓቱን ከድቶ አርበኞች ግንባርን ተቀላቀለ

$
0
0

የደብረዘይት አየር ኃይል አባል የነበረው ምክትል መቶ አለቃ ዳንኤል የሽዋስ ሥርዓቱን በመቃወም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊትን መቀላቀሉን አርበኛ ኑርጀባ ለዘ-ሐበሻ በላከው ዜና አስታወቀ።

(የአርበኞች ግንባር ሠራዊት - ፎቶ ከፋይል)

(የአርበኞች ግንባር ሠራዊት – ፎቶ ከፋይል)

እንደ አርበኛ ኑርጀባ ዘገባ አምባገነኑ የወያኔ ቡድን የታጠቀ ኃይሉን መከታ በማድረግ ንጹሃን ዜጎችን ያለ አግባብ እየጨፈጨፈ የስልጣን ዕድሜውን ለማስቀጠል የሚያደረገውን እንቅስቃሴና በሰራዊቱ ውስጥ የነገሰውን የአንድ ቡድን የበላይነት በመቃወም የደብረዘይት አየር ኃይል አባል የነበረውና L-39 ስኳድሮን ተዋጊ ጀት አብራሪ የነበረው ም/መ/አለቃ ዳንኤል የሽዋስ አገዛዙ የሚያደርስበትን ጭቆናና እንግልት ይበቃል በማለት ወደ ኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ተቀላቅሏል።

“የደብረዘይት አየር ኃይል አባልና L-39 ስኳድሮን ተዋጊ ጀት አብራሪ የነበረው ም/መ/አ ዳንኤል የሽዋስ ተቃዋሚዎችን ትደግፋለህ ከእነሱም ጋር የጠበቀ ግኑኝነት አለህ በሚል ምክንያት ተጠርጥሮ ያለምንም ወንጀል ለአምስት ወር ያህል ታስሮ እንደነበርና ከእስር እንደተለቀቀም በወያኔ የደህንነት አባሎች አማካኝነት በአይነ ቁራኛ ክትትል ይደረግበት እንደነበርም” ማስታወቁን የገለጸው የአርበኛ ኑርጀባ ዘገባ “በም/መ/አ ዳንኤል የሽዋስ የወያኔው የደህንነት አባሎች ጥላቻና ጥርጥር ምክንያት እንደገና ከተቃዋሚ ኃይሎች ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን ደርሰንበታል በማለት ወደ እስር ቤት እንዳስገቡትና ለ23 ቀናት በደብረዘይት እስር ቤት ከቆየ በኋላ ከእስር ቤት አምልጦ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊትን መቀላቀሉን ገልጿል” ብሏል።

በሌላ ዜና በሁመራ አካባቢ የሚኖሩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ላይ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ደጋፊዎች ናችሁ በማለት ታስረው የነበሩ 10 ሰዎች ላይ ከ6 ዓመት እስከ 25 ዓመት በመፍረድ ወደ መቀሌና ሽሬ እስር ቤት እንደወሰዱዋቸው ታውቋል።

በመቀሌ እስር ቤት በኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ደጋፊነትና በተለያየ የአሸባሪነት ሰበብ እየፈጠረ የሚያስረው የወያኔው አገዛዝ በመቀሌ እስር ቤት ብቻ 36,900 እስረኛ የሚገኝ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 4500 የሚሆኑት ሴቶች እንደሆኑ ታውቋል።

በዚሁ እስር ቤት ሰዎችን በሌሊት እየቀሰቀሱ በመውሰድ ደብድበው የሚመልሱ ሲሆን፣ አንዳንዶች ደግሞ በዚያው እንደወጡ እንደሚቀሩ ከአካባቢው የተገኘ መረጃ ያመለክታል።

የወያኔ ካድሬዎችም በዚሁ በመቀሌ እስር ቤት ውስጥ በሚገኙ ሴቶች ላይ የወሲብ ጥቃት እንደሚፈጽሙባቸው መታወቁን የዘገበው አርበኛ ኑርጀባ፣ በዚህም ምክንያት ሁለት ሴቶች መፀነሳቸውና አስፈላጊውን እንክብካቤ ባለማግኘታቸው ሕይወታቸው እንዳለፈ ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል ብሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በዳንሻ አካባቢ በኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ስም በሕዝቡ ላይ እያደረሰ ያለው እንግልት ተጠናክሮ ቀጥሏል።

የወያኔው ገዥ ቡድን በዚሁ አካባቢ እየደረሰበት ባለው ወታደራዊ ጥቃት ሳቢያ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር እንደ ምሽግ የሚጠቀመው እናንተን ነው በማለት የአካባቢውን ህብረተሰብ ያሰቃይ እንደነበር ይታወሳል።

በአሁኑ ወቅት ብዛት ያላቸው የዳንሻና የአካባቢው ነዋሪዎችን እያሰረ ሲሆን፣ የሚሰጠው ምክንያት ደግሞ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ያስታጠቃችሁን መሣሪያ አምጡ፣ ከእነሱ ጋርም ቀጥተኛ ግኑኝነት እንዳላችሁም ደርሰንበታል በሚል ወደ እስር ቤት እያጎራቸው ይገኛል ሲል አርበኛ ኑርጀባ ለዘ-ሐበሻ የላከውን ዜና አጠናቋል።


Amharic News 1800 UTC –ፌብሩወሪ 10, 2014

$
0
0
News, Sports, African Topics and Health…

በብአዴን ማን ይወክላል? (ከጉራማይሌ ፖለቲካ ክፍል 2) – ተመስገን ደሳለኝ

$
0
0

በዘመነ ኢህአዴግ ከታሪክ ተጠያቂነት በፍፁም ሊያመልጡ ከማይችሉ የፖለቲካ ድርጅቶች መካከል ብአዴን እና ኦህዴድ በግንባር ቀደምትነት ይሰለፋሉ፡፡ ሁለቱም ‹እንወክለዋለን› በሚሉት ሕዝብ ላይ ተደጋጋሚ ክህደት ለመፈፀማቸው፣ ደርዘን ያለፉ ድርሳናትን ማዘጋጀት እንደሚቻል እናውቃለን፡፡ አልፎ ተርፎም ህወሓትን ከመሰለ የማፍያ ቡድን ጋር ግንባር ፈጥረው ‹‹ወከልነው›› የሚሉትን የማህብረሰብ ክፍል ህልውና ማድቀቃቸው እውነት ነው፡፡ በርግጥ ምንም እንኳ የሀገር አንድነትን አደጋ ላይ የጣለ ከፋፋይ ፖለቲካን ጨምሮ ሕዝብ እና ትውልድ የሚሉ ነገሮችን ቅርጫት ውስጥ የመጣል አባዜ ቢጠናወተውም፣ ህወሓት ከቅጥረኞቹ ይልቅ የራሱ የሆነ የፖለቲካ ቁመና እና መሬት የወረደ አጀንዳ ይዞ የተነሳ መሆኑ የማይካድ እውነታ ነው፡፡

በዚህ ቁጣ እንድናገር ያደረገኝ ሰሞነኛ ምክንያት ከአንድ የብአዴን ከፍተኛ ካድሬ ነውረኛነት ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ይህ ሰው የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አለምነው መኮንን ሲሆን፣ ኢህአዴግን የተቀላቀለው በተወለደበት ሰሜን ወሎ በ1982 ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ ነበር፡፡ ከመንግስት ለውጥ በኋላም ረዝም ላለ ጊዜ በዛው በሰሜን ወሎ ከገዱ አንዳርጋቸው ጋር በኢህዴን /ብአዴን/ ተጠሪነት ሰርቷል፤ ከሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ የመጀመሪያ ዲግሪውን ማግኘቱን ተከትሎም በክልሉ አስተዳደር ስር ባለው በምፃረ ቃል ‹‹SRAR›› ተብሎ በሚጠራው (በእርሻና መልሶ ማቋቋም ላይ በሚያተኩር) ተቋም በአንድ ክፍል ኃላፊነት አገልግሏል፡፡ በምርጫ 97 ዋዜማ ደግሞ የክልሉ የማስታወቂያ ቢሮ ኃላፊ እንደነበር ይታወሳል፤ ቀጥሎም የአማራ ዲዛይንና ቁጥጥር ስራ አስኪያጅ ሆኖ ሰርቷል፤ ከ2004 ዓ.ም
መጨረሻ ጀምሮ ደግሞ የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የብአዴን ቢሮ ኃላፊ ነው (በነገራችን ላይ በአማራ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንቶች ሶስት ናቸው፤ ከአለምነው በተጨማሪ ብናልፍ አንዱአለም እና ዶ/ር አምባቸው የተባሉ ተሿሚዎችም አሉ) የሆነው ሆኖ ይህ ሰው ባለፈው ሳምንት በባህር ዳር በተዘጋጀ አንድ ስብሰባ ላይ የተናገረውን አስነዋሪ ነገር፣ ረዥም ዕድሜ ለኢሳት ይሁንና ጭው ባለ ድንጋጤ ተውጬ አድምጬዋለሁ፤ ግና ተሳዳቢው የክልሉ አስተዳዳሪ ይሆናል ብዬ አላሰብኩም ነበር፤ የንግግሩ ይዘት ከሞላ ጎደል እንደሚከተለው ይጠቃለላል፡-

‹‹….የአማራው ህዝብ በቅድሚያ እንዳይሰደድ ለማድረግ ስራ እየተሰራ ነው፣ ነገር ግን ከተሰደደ በሁዋላም ቢሆንም ሰንፋጭ የሆነውን ትምክህተኝነቱን በመተው፣ ከሌላው ጋር መኖርን መልመድ አለበት፡፡ …የአማራው ህዝብ ሰንፋጭ የሆነ ትምክህተኝነት የተጠናወተው በመሆኑ፣ በቤንሻንጉልና በሌሎችም ቦታዎች ለመሰደድ ምክንያት ሆኖታል። ….በባዶ እግሩ እየሄደ የሚናገረው ንግግር ግን መርዝ ነው። ይሄ መርዝ ንግግሩ አንድ የሚያደርግ አይደለም፡፡ …ከኢትዮጵያውያን ጋር አብሮ ለመኖር አማራው የትምክህት ለሃጩን ማራገፍ አለበት። ይሄ ለሃጭ ሳይራገፍ በጋራ መኖር አይቻልም። …ማንኛውም ስም ያወጣ ሙትቻ ፓርቲ ሁሉ መንገሻው አማራ ክልል ነው። ትምክህትን እንደ ምግብ ስለሚመገበው ነው። ያንን ምግብ እየተመገበ ያቅራራል።››

በእውነቱ ይህንን የተናገረው ፋሽስቱ ዱቼ ሞሶሎኒ አሊያም ሶማሊያዊው መሀመድ ዜያድባሬ ቢሆን ኖሮ፣ ቅኝ-ግዛት ያማለለው የፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ አድርጎ ማለፍ ይቻል ነበር፤ ግን የዚህ ልብ ሰባሪ ቃላት ባለቤት የክልሉ አስተዳደሪ አለምነው መኮንን ነው፡፡ ዳሩ እርሱስ ቢሆን ማንን እየሰማ አደገና ነው! ምክንያቱም የቀደሙት የብአዴን ሰዎች የወከሉትን ዘውግ ሲረግሙና ሲያንቋሽሹ መታዘባችን የትላንት ክስተት ነው፡፡ የታምራት ላይኔን ‹ሽርጣም ሲልህ የኖረውን ይሄን ነፍጠኛ አሁን ጊዜው ያንተ ነውና በለው› የሚለውን ሐረር ላይ የተሰማ እልቅቲ ነጋሪ አዋጅ ጨምሮ፤ የተፈራ ዋልዋ ‹አማራው በባዶ እግሩ እየሄደ፣ ስንዴ በሩ ላይ አስጥቶ በባዶ ሆዱ የሚፉልል ትምክህተኛ ነው› እስከሚለው ድረስ ያሉ በአደባባይ የተሰሙ ስድቦችን መጥቀስ ይቻላል፡፡
በዚህ ጉዳይ ላይ የመጨረሻ ምሳሌ ለማድረግ፣ እዚህ ሳምንት ድረስ በሬዲዮ ፋና እየተተረከ ያለ አንድ የጥላቻና ዘረኝነት አቀንቃኝ የሆነ መፅሀፍን ልጠቀስ (በነገራችን ላይ እንዲህ አይነቱን ለእርስ በእርስ ግጭት መነሾ የሚሆን፣ በክፋት፣ በተንኮል፣ በክበረ-ነክ ጭብጥ የተሞላን መፅሀፍ ርዕስ እዚህ ጋ ማንሳቱ አስፈላጊ ነው ብዬ አላምንምና አልፈዋለሁ)፡፡ ይህንን መፅሀፍ ደረሲው ዳንኤል ግዛው በእንግሊዘኛ ቋንቋ ያዘጋጀው ሲሆን፣ ወደ አማርኛ የመለሰው የብአዴን ታጋይና የበረከት ስምኦን ባለቤት ወንድም የሆነው መዝሙር ፈንቴ ነው፡፡

በርግጥ በምስጋና ገፁ ላይ እንደተጠቀሰው፣ እንዲተረጉመው ያዘዘውና መፀሀፉን የሰጠው ለአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች ነፃነትና ክብር በዱር-በገደል ታግያለሁ የሚለን ራሱ በረከት ስሞኦን ነው፤ ውለታውንም እንዲህ ሲል ገልፆለታል፡-

‹‹…የምተረጉማቸውን እያንዳንዳቸውን ገፆች ከስር ከስር እየተከታተለ ያነባቸውና ያበረታታኝ ነበር፡፡ ያስጀመረኝ እሱ፣ ያስጨረሰኝም እሱ ነበርና ለአቶ በረከት ስምኦን ያለኝ ምስጋና እጅግ ከፍ ያለ ነው፡፡››

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝም ‹‹አስተማሪ፣ አስገራሚና መሳጭ›› ሲል በፃፈው የጀርባ ገፅ አስተያየት፤ ይህንን እንቶ ፈንቶ እና አንድ ብሔርን ለይቶ የሚያጠቃ ውጉዝ ድርሳን ከፍቅር እስከ መቃብር ጋር በአቻነት አስከማስመሰል ታብዮአል፡፡ ህላዊ ዮሴፍም ረቂቁን በማንበብና በማረም ከፍተኛ አስተዋፆ እንዳደረገ ተርጓሚው ተናግሯል፤ በአናቱም መዝሙር ፈንቴ መፅሀፉን ከመተርጎሙ በፊት በ‹‹ደርባ ሚድሮክ ሲሚንቶ›› ፋብሪካ ውጪው ተሸፍኖለት (የማሳተሚያ ዋጋውንም የቻለው ሼክ መሀመድ አላሙዲ ነው) አደረኩት በሚለው ጉዞ፣ አማራ ረግጦ፣ ቀጥቅጦ፣ ከሰው በታች ዝቅ አድርጎ፣ መሬታቸውን በመንጠቅ አሽከር አድረጎ… እንደገዛቸው የተተረከላቸው የማንጃ እና ማኛ ብሔረሰብ አባላት ወደ ሚገኙበት ደቡብ ኢትዮጵያ ሄዶ ሰፊ ጥናትና ምርምር ማድረጉን ከነገረን አኳያ (የእንግሊዘኛውን ቅጂ ማግኘት አልቻልኩም) መፀሀፉ ቃል በቃል የተተረጎመ ነው ብሎ መቀበሉ ይቸግራል፡፡ ራሱም ቢሆን የፃሀፊው ተደራሲያኖች አሜሪካውያን መሆናቸውን ጠቅሶ ‹‹አቀራረቡን ኢትዮጵያዊ ለማድረግ ብዙ ጥረት አድርጌያለሁ›› ማለቱን ስናስተውል ከተርጓሚነትም ወሰን ተሻግሮ ተጉዟል ብለን እንድናምን ከመገፋታችንም በላይ፣ እነበረከት ስምኦን በአማራው ላይ ያላቸውን ያደረ ጥላቻ ለማንፀባረቅ የተጠቀሙበት ሊሆን ይችላል ብለን ለመጠርጠር እንገደዳለን፡፡

እንግዲህ ብአዴን ማለት፣ ከጉምቱ መሪዎቹ ጀምሮ የክልሉን ነዋሪ ‹‹ቀጣይ ነፃ አውጪያችሁ ነኝ›› የሚለውን ነውረኛውን አለምነው መኮንን ጨምሮ፣ ይህን መሰል በተዋረደ ስብዕና የሚበየኑ ምስኪን ፍጥረቶች የተሰባሰቡበት ድርጅት ነው፡፡ መሰረታዊው ጥያቄ ታዲያ፤ ለዚህ ሁሉ ሰቅጣጭ ሁኔታ፣ የክልሉ ነዋሪ የሆነው የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ ዝምታ ምን ድረስ ይሆን? የሚለው ይመስለኛል፡፡

አቡጊዳ – «አሁን ባለንበት ሁኔታ ውህደት የሚባል ነገር ቦታ የለውም» የሰማያዊ አመራር አባል

$
0
0

የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራርና የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊዉ ወጣት ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ድርጅታቸው «ውህደት ፈጽሞ አያስፈልግም ብሎ የማያምን እንደሆነ የገለሱ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን ዉህደት እንደማይታሰብ አሳወቁ። ፓርቲዉ ከሌሎች ድርጅቶ ጋር አብሮ ለመስራት እና ለመዋሃድ ፈጽሞ የተዘጋ በር እንደሌለው የገለጹት አቶ ብርሃኑ ከዉህደት በፊት ግን መቅደም ያላባቸው ጉዳዮች (የቤት ስራዎች) እንዳሉ ይናገራሉ።

መሰራት ያላባቸውን የቤት ሥራዎች ምን እንደሆነ አቶ ብርሃኑ በጽሁፋቸ ያልገለጹ ሲሆን፣ «አሁን ባለንበት ሁኔታ ውህደት የሚባል ነገር ቦታ የለውም» ሲሉ የቤት ሥራቸዉን የሰሩ ደርጅቶች እንደሌሉ በማመላከት የሚነሱ የዉህደት ጥያቄዎችን ዉድ አደርገዉታል።

በኦፌስል ከሰማያዊ ፓርት ጋር ለመዋሃድ፣ ከአንድነት ፓርቲ በስተቀር ጥያቄ ያቀረበ ድርጅት ስለመኖሩ፣ ብዙ የሚታወቅ ነገር የለም። አቶ ብርሃኑ ተከላ ያሬድ በአሁኑ ወቅት የዉህደት ጥያቄ አቀረቡ የሚሏቸውን ድርጅቶች በተመለከተ «እንደ ፓርቲ መቀጠል ስላልቻሉ ብቻ ድክመታቸውን ወደ ሌላው በማጋባት ህልውናቸውን ለማስቀጠል የሚደረግ ሙከራ የመጠፋፋት ድርጊት እንጂ ውህደት አይደለም» ሲሉም የዉህደት ጥያቄ ያነሱትን ድርጅቶች የዉህደት ጥያቄ ጥሪ አጣጥለዉታል።

በዚህ በዉህደት ዙሪያ የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አባላት አመለካከት አንድ እንዳልሆነ የገለጹት አቶ ብርሃኑ፣ «በውህደት ላይ የፓርቲው አመራር አካላት የያዙት አቋም የሁሉም አቋም ላይሆን ቢችልም ሰማያዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እንደመሆኑ መጠን የአብዛኛውን አቋም የማራመድ ግዴታ እንዳለባቸው እንዲሁም ይህንንም ግዴታቸውን በአግባቡ እየተወጡ መሆናቸውን ፓርቲው ያምናል» ሲሉም የሚወሰኑ ዉሳኔዎች ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መሆኑንም ለማስረዳት ሞክረዋል።

አቶ ብርሃኑ ተከላያሬድ ያቀረቡትን ጽሁፍ እንደሚከተለው አቅርበናል፡

============================================================
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተለያዩ ፓርቲዎች፣ ሚዲያዎች እና ግለሰቦች የሰማያዊ ፓርቲን በውህደት ላይ ያለውን አቋም ሲኮንኑት ይስተዋላል፡፡ ኩነናው ፓርቲው በውህደት ላይ ያለውን አቋም የግለሰብ አቋም ነው እስከ ማለት ይደርሳል፡፡ ስለዚህም የዚህ ጽሑፍ አላማ የፓርቲውን በውህደት ላይ ያለውን አቋም እንዲሁም እውን ፓርቲው በግለሰብ ፖለቲካዊ አቋም የሚመራነውን? የሚለውን ለአንባብያን ለማብራራት እና ለመመለስ ያሰበ ነው፡፡

እኔ እስከማውቀው ፓርቲው በውህደት ላይ ፈጽሞ የተዘጋ አቋም የለውም፡፡ ለዚህም ነው በተለያዩ ጊዜያት ፓርቲው በሚሰጠው መግለጫ ላይ አሁን ባለንበት ሁኔታ ውህደት የሚባል ነገር ቦታ የለውም የሚለው፡፡ ፓርቲ እንደ ፓርቲ የተለያዩ የቤት ስራዎች እንዳሉበት ስለሚያምን እነዚህንም የቤት ስራዎቹን በአግባቡ እና በጥራት ለመስራት ስለሚያስፈልግ ከዚህም ባሻገር ሌሎችም ፓርቲዎችም ከውህደት በፊት በአግባቡ የቤት ስራቸውን መስራት እንደሚኖርባቸውም ከማመን የተነሳ የተያዘ ጊዜያዊ እና ወቅታዊ አቋም መሆኑን ለአንባቢ ማስገንዘብ እፈልጋለሁ፡፡

በሃገራችን የፓርቲ ፖለቲካ ታሪክ ውስጥ የፓርቲዎች የመዋሃድ እና እርስ በእርስ የመበላላት ታሪክ ቢኖርም ዋናው መነሳት ያለበት ነገር ግን ከእነዚህ ታሪኮች ምን ተምረናል የሚለው ጉዳይ ነው፡፡ ታሪክ አሁንም የሚነግረን ከታሪክ የማንማር የታሪክ ቱባ መሆናችንን ነው፡፡ የቅርብ ጊዜ ታሪካችን የሆነው እና የኢትዮጵያን ፖለቲካ ወደ ኋላ የመለሰውን የ1997 ዓ.ም ምርጫ እንደ ማሳያ ሊቀርብ ይችላል፡፡ቅንጅት እንዴት ተቋቋመ? ማን ምን አተረፈ? ማንስ ምን ተጎዳ? ስንት ፓርቲዎች ህይወታቸውን ወይም ህልውናቸውን አጡ? የሚሉት እና የመሳሰሉት ጥያቄዎች በአግባቡ መልስ ማግኘት ይኖርባቸዋል፡ እነዚህ የትናንት ታሪኮቻችን ፍንትው አድርገው የሚያሳዩን ከፓርቲዎች ውህደት በፊት ምን መሰራት እንዳለበት ነው፡፡

‹‹ወንዙን ስንደርስ እንሻገረዋለን!›› በሚል አስተሳሰብ የሚደረግ ውህደት ወንዙንም ተሻጋሪውንም የሚጎዳ ስለሆነ ፈጽሞ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ቅንጅት በወቅቱ ባደረገው የወረቀት ውህደት ወንዙ ጋር ሳይደርሱ ተራራው ላይ ሲፈረካከሱ ለማየትተችሏል፡፡ ይህም ሆድን በጎመን ቢደልሉት ልበት በዳገት ይለግማል የሚለውን የሃገራችን ብሂል እንድናስታውስ ያደርጋል፡፡ ከውህደት በፊት ቅድሚያ አንድ በሚያደርጉን ጉዳዮች ላይ አብረን ለመስራት ያለን ተነሳሽነት ምን ያህል እንደሆነ ማስተዋል ይኖርብናል፡፡

እነዚህ ውህደትን የሚያቀነቅኑ ፓርቲዎች ሰማያዊ ፓርቲ እንደ ፓርቲ ባደረጋቸው የተለያዩ እንቅስቃሴዎች እና ዝግጅቶች ላይ ድጋፍ ለማድረግም ሆነ ለመሳተፍ እንዲሁም አብሮ ለመስራት ካደረጉት ጥረት ይልቅ ባይሳካላቸውም እንቅስቃሴዎቹን ለማሳነስ እና ለማጥላላት የተደረጉ ሙከራዎች ይብሱ ነበር፡፡ ከዚህ በፊት ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 25/2005 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ ባካሄደ ጊዜ ሰልፉን በጋራ ከማሳካትና ከመሳተፍ ይልቅ ከአንዳንድ የፓርቲ አመራሮች ሳይቀር እንዴት ተፈቀደላቸው ብለው ገዢውን ፓርቲ ለመውቀስ የዳዳቸውም ነበሩ፡፡

ታዲያ የራሳቸውን የቤት ስራ እንኳን በአግባቡ መስራት የተሳናቸው ፓርቲዎች እንዴት ጣታቸውን ወደ ሰማያዊ ለመቀሰር እንደሚችሉ ፈጽሞ ሊገባኝ የሚችል ጉዳይ አይደለም፡፡ ፖለቲካን ማኪያቶ መጠጫ ያደረጉ ፓርቲዎችም እንኳን ሳይቀሩ ፓርቲው በውህደት ላይ ያለውን ጊዜያዊ አቋም ለመኮነን ሲሞክሩ ማየት አስቂኝም አሳዛኝም ጉዳይ ነው፡፡ የዚህ ጽሑፍ ባለቤት እንደ ግለሰብ ከውህደት በፊት አንድ በሚያደርጉን ነገሮች ላይ ተቀራርበን ለመስራት ፈቃደኛ መሆን ይኖርብናል ብሎ ያምናል፡፡ አንዳንዶች በውስጣቸው ካለው “የብሔር ተዋጽኦ አናሳነት” አንጻር ውህደትን ሲያራግቡ መመልከት የተለመደ ነው፡፡

ሲጀምር አሁንም እንደ አምባገነኑ ኢህአዴግ ከፋፋይ የጎሳ ፖለቲካን ለማስቀጠል ከሚደረግ ሙከራ ተለይቶ አይታይም፡፡ ይህም ደግሞ መጽሐፉ ኢትዮጵያዊ ቀለሙን እንዲሁም ነብር ዥንጉርጉርነቱን ሊቀይር አይቻለውም እንደሚለው ትውልደ ኢህአዴጋውያን በፓርቲዎች ውስጥ አላግባብ ባገኙት ዜግነት የሚያራምዱት እና የሚያቀነቅኑት አስተሳሰብ መሆኑ የሚካድ አይደለም፡፡ ክፍተቶቻችንን በጊዜያዊነት ለመደፋፈን ሲባል የሚደረግ የጥድፊያ ውህደት መጨረሻው አሁን ካለንበት የፖለቲካ አዘቅት ለመውጣት የሚደረግ ትግልን እንዲሁም የህዝብን አመኔታ ለማግኘት የሚደረገውን ጥረት ወደኋላ ሊመልሰው ይችላል ብዬ አምናለሁ፡፡

መቼም እባብ ያየ በልጥ ይበረያል እንደሚባለው ሊሆን ቢችልም እንኳን እንደ ፓርቲ መጠንቀቁ አይከፋም፡፡ በአግባቡ የቤት ስራችንን ሳንሰራ በፍጹም የቤት ስራቸውን በአግባቡ ካልሰሩ ፓርቲዎች ጋር ውህደት መፈፀምም ተገቢ ነው ብዬ አላምንም፡፡ ቅድሚያ ሁላችንም ያለንበትን በእሾክ የተሞላውን የዴሞክራሲያዊ ፖለቲካ ምህዳር በመጥረጉ አንድ ላይ መስራት ይኖርብናል፡፡ ወንዙን በመሻገር አግዘኝና ይህንን እሰጥሃለው የሚባል ትብብርም ለህወሓት እና ሻዕቢያም እንዲሁም ለህወሓት እና ኦነግም አልበጀም፡፡ ትርፉ በደም እና በስጋ የተሳሰሩ ህዝቦችን በጠላትነት ከማፈራረጅ እና በደም ከማቃባት የዘለለ አልሆነም፡፡

ስለዚህም ትብብራችንም ሆነ ውህደታችን ከጥቅም ተኮርነት እና ጊዜያዊ ሆሆይታ ባሻገር የህዝብን የወደፊት ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ዛሬ ዳቦ ያቋረሰ እና ፈንዲሻ ያስበተነ ውህደት ወይም ትብብር ነገ ሃገር ሊያቋርስ እና ህዝብን ሊበትን ይችላልና ጥንቃቄ ሊወሰድ ይገባል፡፡ ውህደት ማለት የልብ እንጂ የወረቀት መሆን የለበትም፡፡ ሁሉም የቤት ስራውን ሰርቶ ሲጨርስ መሰረታዊ ልዩነቶቹ ላይ በጠረጴዛ ዙሪያ ድርድር በማድረግ ውህደት ለመፈጸም በሩን ከፍቶ የሌሎችን መምጣት ሚጠባበቅ ብቻ ሳይሆን የሌሎችንም የተዘጋ በር በተደጋጋሚ የሚያንኳኳ መሆኑ ግንዛቤ ሊወሰድ ይገባል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በውህደት ላይ ያለውን አቋም የአንድ ግለሰብ አቋም አድርገው በማቅረብ የፓርቲውን እና የአባላቱን ስም ለማጉደፍ የሚደረግ ሙከራ እውነትነት የሌለው ፍሬ አልባ ነገር መሆኑን ለማስረዳት ሰማያዊ ፓርቲ እንዴት እና ለምን ተፈጠረ የሚለውን ብቻ ማየት በቂ ይመስለኛል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ የተቋቋመው ግለሰቦች ከህግ በላይ ሆነው መተዳደሪያ ደንብ እና መርህ እየተጣሰ መቀጠል የለብንም በሚል አቋም ከፓርቲ ጥለው በወጡ ግለሰቦች መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡ ታዲያ እነዚህ ህግ እንጂ ግለሰብ አይመራንም ያሉ አባላት እንዴት ዛሬ ለግለሰብ አስተሳሰብ ተገዢ ሊሆኑ ይችላሉ ተብሎ ይታሰባል? እዚህ ጋር መዘንጋት የሌለበት ሁሉም የፓርቲ አባላት እንደ ፋብሪካ ውጤት ተመሳሳይ የሆነ አቋም አላቸው ተብሎ ሊወሰድ አይገባም፡፡ከአባላት ውስጥ ውህደትን የሚደግፉ ሊኖሩ ቢችሉም የእነዚህን አባላት አመለካከት ፓርቲው ለፓርቲው ጥቅም ከማሰብ መሆኑን ቢገነዘብም አብዛኛው የፓርቲው አባላት ለውህደት ጊዜው አሁን አይደለም ብለው የሚያምኑ በመሆናቸው የተያዘ አቋም እንጂ የአንድ ግለሰብ አቋም አይደለም፡፡

የፓርቲው ሊቀ-መንበርም ሆኑ የተቀሩት አመራር አካላት አብዛኛው የፓርቲው አባላት የሚያራምዱትን አቋም የራሳቸው ሆነም አልሆነም የማራመድ ግዴታ ያለባቸው መሆኑን የሚያውቁ እንጂ የራሳቸውን ሃሳብ በሌሎች ላይ ለመጫን የሚደረግ ምንም አይነት ሙከራ የለም ብሎ ደፍሮ መናገር ይቻላል፡፡ በውህደት ላይ የፓርቲው አመራር አካላት የያዙት አቋም የሁሉም አቋም ላይሆን ቢችልም ሰማያዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እንደመሆኑ መጠን የአብዛኛውን አቋም የማራመድ ግዴታ እንዳለባቸው እንዲሁም ይህንንም ግዴታቸውን በአግባቡ እየተወጡ መሆናቸውን ፓርቲው ያምናል፡፡

በመጨረሻም ፓርቲዬ ሰማያዊ ውህደት ፈጽሞ አያስፈልግም ብሎ የማያምን እና ከፓርቲዎች ውህደት በፊት ብዙ ስራዎች ሊሰሩ እንደሚገቡ የሚያምን መሆኑ እንዲሁም ሌሎች እንደ ፓርቲ መቀጠል ስላልቻሉ ብቻ ድክመታቸውን ወደ ሌላው በማጋባት ህልውናቸውን ለማስቀጠል የሚደረግ ሙከራ የመጠፋፋት ድርጊት እንጂ ውህደት አይደለም ብሎም ያምናል፡፡በመሆኑም በአሁኑ ሰዓት ከየትኛውም ፓርቲ ጋር አንድ በሚያደርጉን ሃገራዊ ጉዳዮች ላይ ልዩነቶቻችንን ተቻችለን እና ተከባብረን ለመስራት የምንፈልግ እና እየሰራንም የምንገኝ መሆኑን ሊታወቅ ይገባል፡፡ የሆሆይታ ውህደት ከታሰበው ጥንካሬ ይልቅ ድክመትን ሊያመጣ ይችላልና በሰከነ አዕምሮ ቢታይ ይሻላል፡፡ ካልሆነ ግን ከላይ እንዳልኩት ‹‹ሆድን በጎመን ቢደልሉት ጉልበት በዳገት ይለግማል፡፡»

መልክዓ-ሌንጮ (ከጉራማይሌ ፖለቲካ ክፍል 2 ) – ተመስገን ደሳለኝ

$
0
0

ሌላኛው ሰሞነኛ ጉራማይሌ የፖለቲካችን ገፅ አንጋፋውን የኦሮሞ ልሂቅ ሌንጮ ለታን የተመለከተው ርዕሰ-ጉዳይ ነው፡፡ ኦነግን በመመስረትም ሆነ ፖለቲካዊ ቁመና ይዞ ህልው እንዲሆን ከዮሀንስ ለታ በላይ ማንም የለፋ እንደሌለ ይነገራል፤ ዮሀንስ ከጓዶቹ ጋር ተባብሮ ድርጅቱን ሲመሰርት ካነገበው አጀንዳ አኳያ ያለውን ተዛምዶ ገልፆ ባይነግረንም፣ ከልጅነት እስከ ጎልማሳነት ይታወቅበት የነበረውን መጠሪያ ስሙን ‹ሌንጮ› በሚል ቀይሮታል፡፡

ኦነግ እስከ 1983 ዓ.ም ድረስ የሻዕቢያ እና የህወሓትን ያህል ባይሆንም ያለፈውን ስርዓት ለመቀየር የጠመንጃ ትግል አድርጓል፡፡ ከዚህም አኳያ ይመስለኛል የመንግስቱ ኃይለማርያም አስተዳደር ግብዓተ-መሬት መፈፀሙ የቀናት ጉዳይ ብቻ እንደሆነ በታመነበት ወቅት በሀገረ እንግሊዝ፣ ሰሞኑን ‹ባድመን ለኤርትራ ስጡ› እያለ በሚወተውተን ኸርማን ኮህን አርቃቂነት በተዘጋጀው የለንደኑ ኮንፍረንስ ከሁለቱ ድርጅቶች ጋር የተቃውሞውን ፖለቲካ ወክሎ እንዲገኝ የተደረገው፡፡ ኋላም የታመነው ደርሶ አገዛዙ ሲወድቅ ኦነግም የሽግግር መንግስቱ መስራች አባል ሆኖ የመተዳደሪያ ቻርተሩን ዋነኛ አዕምዶች (የመሬት የመንግስት ባለቤትነት፣ የመገንጠል መብት እና ቋንቋ ተኮሩን ፌደራሊዝም) ከማርቀቅ ባለፈ እስከ 1984 ዓ.ም የመጨረሻ ወራት ድረስ የሥልጣን ተቋዳሽ ቢሆንም፣ ኢህአዴግ ባደረሰበት ጫናና ግፊት ሥልጣኑን ለቆ ተመልሶ ወደ በረሃ መግባቱ አይዘነጋም፡፡

ግና! ይህችን ለብዙ አስርታት በታጋዮቹ ስትማተር የነበረችውን የኦነግ የመኸር አንዲት ዓመትን ተከትሎ፣ በኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች ላይ መውረድ የጀመረው የመከራና የዕልቂት መዓት ዛሬም ድረስ አላባራም፡፡ እስከዚህች ቀንም እልፍ አእላፍ ንፁሃኖች በኦሮሞነታቸው ብቻ አስከፊውን የቃሊቲ ማጎሪያ ጨምሮ በተለያዩ ገሀነም-መሰል እስር ቤቶች የምድር ፍዳቸውን እየተቀበሉ ነው፡፡ በደርግ ዘመን የኤርትራ ነዋሪዎችን ‹‹ሻዕቢያ››! በማለት በአደባባይ ገድሎ መሄዱ ቀላል የነበረውን ያህል፣ ኢህአዴግም ሃያ ሁለቱን ዓመታት ሙሉ በኦሮምኛ ተናጋሪዎች ላይ ተመሳሳዩን ታሪክ ደግሞታል፡፡ የነገይቱን ኢትዮጵያ ህልውና በሚያጠይቅ ሁኔታም በግዙፉ ቃሊቲ ‹የእስር ቤቱ ቋንቋ ኦሮምኛ ነው› እስኪባል ድረስ ያለ አሳማኝ ክስ እያነቀ ግቢውን እንዲያጥለቀልቁት አድርጓል፡፡ የዚህ ሁሉ መነሻ ሰበብ የእነሌንጮ ለታ ድርጅት መሆኑ አይካድም፡፡

ኦነግ ከ1980ዎቹ መጨረሻ ወዲህ ለስርዓቱ አስጊ እንዳልነበር እና ይዞታውን ከባሌ ወደ አስመራ እና ሚኒሶታ ማዘዋወሩን፣ በስሙ ለተፈፀመው ዕልቂት ቀማሪና አዛዡ ህወሓትም ሆነ አስፈፃሚው ኦህዴድ ጠንቅቀው የሚያውቁት ቢሆንም፤ ‹‹በስመ-ኦነግ›› ከሚፈነዱና ከሚከሽፉ ፈንጂዎች ጋር እያያዙ የክልሉን ተወላጆች የጥቃት ኢላማ ማድረጉ መደበኛ መንግስታዊ ስራ ከሆነ ሁለት አስርታት ተቆጥረዋል፡፡ የዚህ መነሾም የህወሓት ኦሮምኛ ተናጋሪ ክንፍ ከሆነው ኦህዴድ ይልቅ፣ በኃይል የተገፋው ኦነግ በብዙሀኑ ልብ ማደሩ ያነበረው ፍርሃት አንዱ ሲሆን፤ ሌላው ደግሞ ኦህኮ እና ኦፌዴን (ባለፈው ዓመት ‹‹ኦፌኮ›› በሚል ስያሜ መዋህዳቸው ይታወሳል) ያላቸውን ቅቡልነት መጨፍለቅን ያሰላ ይመስለኛል፡፡
በዚህ የተቀነባበረ ጥቃትም ብዙዎች ለህልፈት፣ እልፍ አእላፍቶች ለእስርና ለስደት ተዳርገዋል፤ ቤተሰብ ተበትኗል፤ ህፃናት ያለ አሳዳጊ፣ አረጋውያን ያለ ጧሪ ቀርተዋል፡፡ እርግጥ ይሄ ጉራማይሌ አይደለም፤ አያሌ ማስረጃ ሊቀርብበት የሚችል ተጨባጭ እውነታ እንጂ፡፡ በአናቱም ይብዛም ይነስ የቀድሞ የኦነግ መስራችና የአመራር አባሉ ሌንጮ ለታ፣ ለዚህ ሁሉ ስቃይና መከራ የድርሻውን ያህል የታሪክ ተወቃሽ (ተጠያቂ) መሆኑ አከራካሪ አይደለም፡፡

የሆነው ሆኖ በሌንጮ ኦነግ ስም ለተገደሉት ገዳዮቻቸው ለፍረድ ሳይቀርቡ፣ የታሰሩት ሳይፈቱ፣ የተሰደዱት ሳይመለሱ፣ የፈረሱ ጎጆዎች ሳይቀለሱ፣ ሌላው ቀርቶ ከኢትዮጵያም አልፎ ከኬኒያ ‹ኦነግ› እያሉ አፍነው በመውሰድ ለእስር መዳረጉ (በቅርቡ በወህኒ ቤት ሕይወቱ ያለፈውን ኢንጂነር ተስፋዬ ጨመዳን እናስታውሳለን) ዛሬም ቀጥሎ እያለ ኦቦ ሌንጮ ለታ ‹‹የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር›› የተሰኘ አዲስ የፖለቲካ ድርጅት መስርቶ፣ ለሚቀጥለው ምርጫ እያሟሟቀ ከመሆኑም በላይ በቅርቡ ወደ ሀገር ቤት ገብቶ ታሪክ እንደሚሰራ የተናገረውን ማድመጣችንን ነው ለጉራማይሌ ፖለቲካ ማሳያ ያደረኩት (ሌንጮ ኦዴግን ከመሰረተ ጀምሮ ላለፉት በርካታ ወራት ‹‹ገብተን እንታገላለን›› ማለቱን ስንሰማ ከርመናል) በተያያዘም ሰውየው የኖርዌይ መንግስት የአፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ መሆኑን ስንጨምር፣ በአንድ ወቅት ራሱም ‹‹እዚህ ኖርዌይ ቁጭ ብዬ ምን እሰራለሁ?›› እንዳለው የአማካሪነቱን ከፍተኛ ደሞዝ ጭምር ትቶ ለመምጣት መወሰኑ፣ ቀጣይ ሚናው ላይ ያለውን የመተማመን ልክ ማየት እንችላለን፡፡ ርግጥ ሌንጮ ከ40 ዓመታት በፊትም የቅርብ ዘመዱ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ለታሪክ ትምህርት ወደ ጀርመን ለመሄድ አዲስ አበባ ላይ በተገናኙበት ጊዜ ‹አንተ ታሪክ ተማር፤ እኛ ደግሞ ታሪክ ሰርተን እንጠብቅሀለን› ማለቱ አይዘነጋም፡፡ ዛሬም ከአንደበቱ የሚወጡ ቃላቶች ስለታሪክ መጨነቁን ያመላክታሉ፡፡ ይሁንና ሌንጮ ‹ታሪክ መስራት› የሚለው የእነአባዱላ ገመዳን አይነት ወዶ-ገብት ከሆነ ሀፍረቱ ለሁላችንም መሆኑ አይቀሬ ነው፡፡

በነገራችን ላይ ኦሮሚያን ለመደለል ሌንጮን በዝውውር የማምጣቱ ሥራ የተጀመረው በአቶ መለስ ዜናዊ ዘመን ነው፤ የዊክሊክስ ዘገባም እንደጠቆመው፣ መለስ ዜናው ‹‹ሌንጮ ማድረግ ያለበት እኔን ለማግኘት መሞከር ብቻ ነው፤ ይህን ደግሞ እንዴት ማድረግ እንዳለበት ያውቃል›› ማለቱን አስነብቦናል፡፡ እንዲሁም እ.ኤ.አ በ2007 ዓ.ም ኢንተር አፍሪካ ግሩፕ ባዘጋጀው፣ በአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ሕገ-መንግስታዊነት ጉዳይ ላይ በተካሄደ ኮንፈረንስ፣ የቀረበውን የሌንጮ ለታን ጥናታዊ ፁሁፍ መከራከሪያዎችን በማብራራት ተጠምዶ የነበረው የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ፕ/ር እንድሪያስ እሸቴ እንደነበረ ስናስታውስ፣ በሌንጮ የመምጣት ድርድር ውሳኔ ውስጥ የፕ/ሩን (የመንግስትን) የሰነበተ ሚና እንድንገምት እንገደዳለን፡፡ እርሱም ቢሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ፊንፊኔ ላይ የታየው በ2004 ዓ.ም እንደሆነ ይነገራል፡፡ ከዚህ ሁሉ ጀርባ ደግሞ የአሜሪካ፣ ብሪታኒያ እና ኖርዌይ እጅ እንዳለበት ተሰምቷል፡፡ ባለፈው ዓመት ህዳር ወር መጀመሪያ ሳምንት ሌንጮና አባዱላ ገመዳ አሜሪካን ሀገር በሚገኝ አንድ ሆቴል ውስጥ አርፈው የነበረ መሆኑም የአጋጣሚ ጉዳይ አይመስለኝም፡፡
ኢህአዴግ ስጋት ላይ ከጣሉት የፖለቲካ ድርጅቶች ውስጥ ግለስብን ገንጥሎ ማማለልን ተክኖበታል፤ ከሶስት ዓመት በፊት መለክት ተንፍቶለት ወዶ የገባው አባቢያ አባጆቢር (ከኦነግ መስራቾቹ አንዱ የነበረ ሲሆን፣ ለእንግሊዘኛው ‹‹ዘ-ሪፖርተር›› ጋዜጣ በሰጠው ቃለ-መጠይቅ፣ የድርጅቱ የመጀመሪያ ፕሮግራም ላይ ስለመገንጠል የሚያወራውን አንቀፅ በወቅቱ ተቃውሜ ነበር ማለቱ ይታወሳል) ዛሬ ድምፁ አይሰማም፡፡ ከኦብነግ ጋርም ተደረሰ በተባለ ስምምነት የመጡትን ግለሰቦች፣ ድርጅታቸው አሁንም አፈመዝ ካለመድፋቱ አኳያ ስናየው ጨዋታው ዕቃቃ እንደነበር ይገባናል፡፡ በዚህ ሰሞን ደግሞ ዶ/ር መራራ ጉዲና ከፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ጋር ሊወያይ ወደ ጀርመን አምርቷል፤ ሌንጮ ለታም አዳዲስ አባላትን ሊመለምል እዛው ጀርመን ይገኛል (ሁለቱ ጉምቱ የኦሮሞ ልሂቃኖች ተገናኝተው ይሆን?) በርግጥ ሌንጮ የጀርመን ቆይታውን ሲጨርስ፣ በሆላንድ ያቀደውን ተመሳሳይ መረሃ ግብር አከናውኖ በይፋ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለስ ለጉዳዩ ከሚቀርቡ የመረጃ ምንጮቼ ሰምቻለሁ፡፡

ይሁንና እዚህ ጋ የሚነሳው ጥያቄ ሌንጮ ወደ ሀገሩ ለምን መጣ? የሚል አይደለም፤ እነበቀለ ገርባን የመሳሰሉ ፍፁም ሰላማዊ እና እጃቸው በንፁሀን ደም ያልጨቀየ ፖለቲከኞችን መታገስ ያልቻለ ስርዓት፣ ለሌንጮ የሚሆን ይቅር ባይነትን ከወዴት አገኘ? የሚል ነው፤ ሁለት አርፍተ ነገር የተናገረ ሁሉ ተለቃቅሞ እየታሰረ ሌንጮ ምን ተማምኖ መጣ? በኦሮሚያ ላይ የነገሡት እነአፄ አባዱላና ኩማ ደመቅሳስ ቢሆኑ ከሌንጮ አዲሱ ድርጅት ተነፃፅሮ የሚነሳባቸውን የቅቡልነት መገዳደር ለመጋፈጥ እንዴት ፍቃደኛ ሆኑ? ምናልባት መተካካት የሚባለው ይህ ይሆን እንዴ? ወይስ መረራ ጉዲና ‹‹የኦሮሞ ሕዝብ በቁመቱ ልክ ሥልጣን ይገባዋል!›› እንዲል፣ ሌንጮ ለታም በራሱ ቁመት የተቀነበበ ሥልጣን ቃል ተገብቶለት ይሆን? …የእነዚህና መሰል ጥያቄዎች ምላሽ ዛሬም በሙት መንፈስና በታመመ ሰው እንድትመራ በተፈረደባት ኦሮሚያ ላይ በቀጣይ ከሚኖረው ፖለቲካዊ አሰላለፍ ጋር መጋመዱ አይቀሬ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡

ከዚህ ባለፈ ‹‹ጀግናው›› ኢህአዴግ የሌንጮ ድርጅትን ኦፌኮን ወይም አንድነትን እንደመሳሰሉ ፓርቲዎች ነፃ ተቃዋሚ ሆኖ እንዲንቀሳቀስ ይፈቅድለታል ብሎ ማሰቡ እጅግ በጣም የዋህነት ይመስለኛል፡፡ በርግጥ ኦቦ ሌንጮ ከሳምንታት በፊት ለጀርመን ድምፅ ራዲዮ በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ፣ በቀጣዩ ምርጫ ለመሳተፍ ስለመወሰኑ ሲጠየቅ ‹‹ፖለቲካ በምርጫ በመሳተፍ ብቻ አይወሰንም፤ ሕዝቡን ማስተማርና ማንቃቱም አንዱ መንገድ ነው›› የሚል መንፈስ የያዘ መልስ ሰጥቷል፡፡ የሆነው ሆኖ ሌንጮ ለምርጫ ቅስቀሳ አሊያም ለንቃተ ህሊና ስብከት ፊቱን ወደ ኦሮሚያ ከማዞሩ አስቀድሞ የሚከተለው ጥያቄ ተጋፋጭ ተግዳሮት እንደሚሆንበት ይታሰባል፡- በሽግግር መንግስቱ ወቅት ሥልጣን ላይ የነበርክበትን ጊዜ ተከትሎ አንተን እና ኦነግን አምነው ከቤታቸው የወጡ ልጆቻችንን፣ ወንድሞቻችንን፣ አባቶቻችንን የት ጥለሀቸው መጣህ? ሰማዕታቶቻችንንስ በማን ስም እንዘክራቸው? … Akka dhufaa jirtu barree carraa garii (sihaaqunamu)

አዲስ አድማስ – የአዲስ አበባ ከንቲባና ፖሊስ ኮሚሽነር በ“አንድነት” ተከሰሱ

$
0
0

«ከንቲባ ድሪባ ኩማና ኮሚሽነሩ መከራከሪያቸውን ለፍ/ቤት ያቀርባሉ »

«አንድነት፣ የመንግስት አካላትን በተከታታይ እከሳለሁ ብሏል»

አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት)፣ የአዲስ አበባ ከንቲባና የፖሊስ ኮሚሽነራቸው ላይ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 8ኛ ወንጀል ችሎት ክስ የመሰረተ ሲሆን ተከሳሾች መልሳቸውን ይዘው እንዲቀርቡ ለየካቲት 24 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጠ፡፡

አንድነት ፓርቲ፤ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” የተሰኘ አገር አቀፍ የ3 ወር ንቅናቄ ማጠቃለያን በአዲስ አበባ ባካሄደበት ወቅት በከተማ አስተዳደሩና በፖሊስ ኮሚሽን እስርና ወከባ እንደተፈፀመበት ገልፆ፤ በደላቸውን በማስረጃ በመዘርዘር ክስ መመስረቱን አስታውቋል፡፡
በፖሊስ ተፈፀመ በተባለ በደል ከንቲባውን በቀጥታ ለምን እንደከሰሰ ፓርቲው ሲያስረዳ፣ የአዲስ አበባ መተዳደሪያ ቻርተር ከንቲባው የከተማዋን ፖሊስ የእለት ተእለት እንቅስቃሴ የመቆጣጠር ኃላፊነት እንዳለበት ስለሚደነግግ ከንቲባውን በቀጥታ ተጠያቂ ያደርጋቸዋል ብሏል፡፡

ቅስቀሳ ላይ የነበሩ የፓርቲው አመራሮችና አባላት በጅምላ በፖሊስ ታስረው መዋላቸውን ፓርቲው ጠቅሶ፣ የቅስቀሳ ቁሳቁስ ተነጥቀናል፤ ፖስተሮችን እንዳንለጥፍ ተከልክለናል ብለዋል። የፖሊስን የእለት ተእለት እንቅስቃሴ የመከታተል ሃላፊነት የተጣለባቸው ከንቲባውና ኮሚሽነሩ፣ የፖሊስን ህገወጥ ተግባር በቸልታ አልፈውታል ብሏል – አንድነት ፓርቲ፡፡
“በቂ ማስረጃ ከተደራጀ በኋላ ነው ወደ ክስ የሄድነው” ያሉት የፓርቲው አመራሮች፤ ክሱን የመሰረቱት ጠበቃ ተማም አባቡልጉ እና ረዳታቸው መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ከንቲባውና ኮሚሽነሩ የካቲት 24 ቀን መልሳቸውን ካቀረቡ በኋላ መጋቢት 2 ቀን ክርክር ይካሄዳል ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ውስጥ ፍ/ቤት የለም ብለው እንደሚያምኑ የተናገሩት የፓርቲው መሪዎች፤ የመንግሥት አካላት የሚፈፅሙትን አፈና በይፋ ወደ ፍ/ቤት በመውሰድ የፍትህ ስርአቱን መፈተንና ለህዝብ ማጋለጥ አንዱ የትግል አላማችን ነው ብለዋል፡፡
ከሰኔ እስከ ነሐሴ 2005 ለ3 ወራት፣ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል በመላ አገሪቱ የተደረጉት ሰላማዊ ሰልፎችና ህዝባዊ ስብሰባዎች ህዝብን በማነቃቃት ስኬታማ ውጤት አግኝተንባቸዋል ሲሉ የፓርቲው መሪዎች ተናግረዋል፡፡ በሌላ በኩል፤ በፀጥታው ኃይል እና በገዢው ፓርቲ ካድሬ መካከል ልዩነት አለመኖሩን አይተናል፤ በአገሪቱ በተዘረጋ የአፈና መዋቅር ከፍተኛ የህግ ጥሰት እንደሚፈፀም አረጋግጠናል ያሉት የፓርቲው መሪዎች፤ የመንግስት ጫና ሳያሸብረው ፓርቲው ተመሳሳይ ንቅናቄዎችን በተከታታይ ያዘጋጃል ብለዋል፡፡

“የፀረ-ሽብር አዋጁን ለማሰረዝ የሰበሰባችሁትን ድምፅ የት አደረሳችሁት” የሚል ጥያቄ ከአዲስ አድማስ የቀረበላቸው አመራሮቹ፤ “የተሰበሰበውን የህዝብ ድምፅ ወደ ፍ/ቤት ለመውሰድ የህግ ባለሙያዎች እየመከሩበት ነው፣ በሁለተኛ ዙር የክስ ሂደት ውስጥ የሚካተት ይሆናል ብለዋል፡፡ በተካሄደው የ3 ወር የህዝብ ንቅናቄም መንግሥት ለጉዳዩ ይበልጥ ትኩረት እንዲሰጥ ፓርቲው ጫና ማሳረፉን የሚያመለክቱ ውጤቶች መታየት መጀመራቸውን የጠቀሱት የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሃብታሙ አያሌው፤ የፀረ-ሽብር አዋጁ ከመፅደቁ በፊት ለህዝብ ውይይት መቅረብ ሲገባው አዋጁ ወጥቶ ብዙዎችን ሰለባ ካደረገ በኋላ መንግስት ራሱን ለመከላከል የፕሮፖጋንዳና የስልጠና ዘመቻ ጀምሯል ብለዋል፡፡ ይህም ፓርቲያቸው ይዞት የተነሳው ጥያቄ ጫና ማሳረፉንና ትክክለኛ እንደነበር የሚያረጋግጥ መሆኑን አቶ ሃብታሙ ገልፀዋል፡፡

“ማንም ሰው ወይም አካል ከህግ በላይ ሊሆን አይችልም” ያለው ፓርቲው፤ ህግ በሚጥሱ የመንግስት አካላት ላይ በተከታታይ ክስ እመሰርታለሁ፤ በቅርቡም በመንግሥት ከፍተኛ አመራሮችና በገዢው ፓርቲ ላይ ተጨማሪ ክስ ለመመስረት እየተዘጋጀሁ ነው ብሏል፡፡

የኢትዮጵያና የግብፅ የውኃ ሚኒስትሮች ውይይት ያለውጤት ተጠናቀቀ

$
0
0
የኢትዮጵያና የግብፅ የውኃ ሚኒስትሮች ዛሬ አዲስ አበባ ላይ ያደረጉት ስብሰባ ያለስምምነት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ለቪኦኤ ዛሬ ማምሻውን ገልፀዋል፡፡…

አቡጊዳ – ደራሲና የአንድነት አመራር አባል፣ አቶ አንዳርጌ መስፍን ፖሊስ ፊት እንዲቀርቡ ታዘዙ

$
0
0

ወጣቱ ፖለቲከኛና ደራሲ አቶ ዳንኤል ተፈራ ፖሊስ ጣቢያ እንዲቀርብ መጠየቁ በስፋት መዘገቡ ይታወቃል። አቶ ዳንኤል መጀመሪያ ላይ እንዲቀርብ የተጠየቀዉ በስልክ፣ ሲሆን፣ ሕጋዊ መጥሪያ ወረቀት ካልመጣለት በቀር ለመቅረብ ፈቅደኛ ሳይሆን እንዳልቀረ ለማወቅ ተችሏል።

ከአቶ ዳንኤል ተፈራ በተጨማሪ፣ የአንድነት ብሄራዊ ምክር አባል የሆኑትና በርካታ መጽሃፍት በመጻፍ የሚታወቁት አዛዉንቱ አቶ አንዳርጌ መስፍንን፣ ፖሊስ ለመከሰስ እንደተዘጋጀ፣ እንዲቀርቡም እንዳዘዘ ለማረጋገጥ ችለናል።

አቶ አንዳርጌ መስፍን ከጻፏቸው በርካታ መጽሃፍት መካከል «ጥቁር ደም» የሚለው ታዋቂ መጽሃፍ ይገኝበታል። ከአቶ መለስ ዜናዊ ሕልፈት በኋላም፣ «የመለስን ራእይ እናስቀጥላለን» የሚል አቶ መለስን እንደ አምላክ የማቅረብ የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ ከልክ ባለፈበት ወቅት «በሞት መንፈስ አገር ሲታመስ» የሚል መጽሃፍን የጻፉ ደራሲ ናቸው።

አቶ አንዳርጌ መስፍን፣ በአንድነት ፓርቲ ዉስጥ በአዲሱና ከዚያም በፊት በነበረው የብሄራዊ ምክር ቤት አባል አመራር አባል ሆነው እያገለገሉ ሲሆን፣ የፍኖት ጋዜጣ ኤዲቶሪያል ቦርድ ዉስጥ ሰርተዋል።

ኢሕአዴግ በአቶ ዳንኤል ተፈራና አንዱ አንዳርጌ መስፍን ላይ ምን አይነት ክስ እንደሚያቀርብ ገና የታወቀ ነገር ባይኖርም፣ የአንድነት አመራር አባላትን እና ደጋፊዎች ለማስፈራራት፣ ለፍርድ ቤት መመሪያ በመስጠት፣ እስከ ስድስት ወራት የእስራት ቅጣት ሊበየንባቸዉ እንደሚችል የአንድነት አመራር አባላት ይናገራሉ።

በዚህ ጉዳይ ላይ አስተያየት የሰጡን የአንድነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ አቶ ሃብታሙ አያሌዉ ፣ አቶ ዳንኤልም ሆነ አቶ አንዳርጌ መስፍን ፍጹም ሰላማዊ፣ ሰው አክባሪና አገር ወዳድ እንደሆኑ በመግለጽ፣ በነርሱ ላይም ሆነ በሌሎች የአመራር አባላት ላይ እየተደረገ ያለው ጥቃት፣ በሕዝብ ዘንድ የበለጠ ተቀባይነትን ድጋፍ እያገኘ የመጣዉን የአንድነት ፓርቲ ሆን ብሎ ለማዳከም ሲባል በፖለቲካዊ ዉሳኔ የሚደረግ እንደሆነ አስረድተዋል።

«ወያኔ የሚል ቃል ተጠቅመሃል» በሚል ክስ እርሳቸዉም ቀርቦባቸዉ ከአሥራ አንድ ጊዜ በላይ፣ ፍርድ ቤት እየተመላሱ እንደሆነ የገለጹት አቶ ሃብታሙ «ያለ ምንም ጥርጥር ወደፊት እንሄዳለን። መታሰሩ በጣም ቀላል ነገር ነዉ። የሰላማዊ ትግሉ ይቀጥላል» ሲሉም የርሳቸውም ሆነ የሌሎች የአመራር አባላት መታሰር አንድነትን እንደ ፓርቲ፣ ትግሉን እንደ ትግሉ የሚያጠናክር እንጂ የሚጎዳ እንዳለሆነ አሳስበዋል።


ESAT Radio Mon, Feb 10 2014

$
0
0
ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

የኢትዮጵያና የግብፅ የውኃ ሚኒስትሮች ውይይት ያለውጤት ተጠናቀቀ –ፌብሩወሪ 11, 2014

$
0
0
Ethiopia - Egypt water Ministers meeting in Addis…

ከኢትዮጵያ የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር አቶ ዓለማየሁ ተገኑ ጋር የተደረገ ቃለምልልስ ሙሉ ቃል –ፌብሩወሪ 11, 2014

$
0
0
Interview with Alemayehu Tegenu, Minister of Water, Ethiopia…

አለምነው መኮንን ኃላፊነት የጎደለው ኃላፊ

“ጥቁሩ ሰው” – የጥቁር ሕዝብ አባት (ከስንሻው ተገኝ)

$
0
0

አንድ ዘመን ሥርዓተ መንግስቱ በመቆየትም ሆነ አባላቱ የአሥራ ሰባተኛው ክፍለ ዘመን የተረት ዓለም ሰዎች ስለ መሰሉን- ሁሉም ነገር ስለገለማን አዲስ ሥርዓት፣ አዲስ መሪ፣ አዲስ ዘመን መናፈቅ ይዘን ነበር። ሰዓሊ ሁሉ፣ ደራሲ ሁሉ፣ ጸሐፌ -ተውኔት ሁሉ እጁን የሚያሟሸው በቴዎድሮስ ሥዕል፣ ተውኔትና ታሪክ ሆነ። ብርሃኑ ዘሪሁን- የቴዎድሮስ እንባ -(መጽሐፍ) ከዚያ በፊት ደጃዝማች ግርማቸው ተክለሐዋርያት- ቴዎድሮስ (ተውኔት) አቤ ጉበኛ – አንድ ለእናቱ (ታሪካዊ ልቦለድ) ጸጋዬ ገብረ መድኅን – ቴዎድሮስ (ተውኔት)…ሥዩም ወልዴ -ሥዕል..ታደሰ ወ.አ….ቅርጻቅርጽ እና የሥነ ጥበባት ትምህርት ቤት ሥስት አራተኛ ተማሪዎች..የቴዎድሮስ ሥዕል ግጥም -ቅኔ- ሥዕል አለፈላት።

ከአሮጌና ከገለማ ሥርዓት ነፃ የሚያወጣ አመጸኛና አመጻ የሚመራ ጀግና ስንፈልግ ባጀንና ቴዎድሮስን አገኘን። ከመቶ አመት በኋላ ነው ቴዎድሮስ የተፈለገው። በአጤው ሥርዓት በአንዳንድ ደራስያንና የዘመን ታሪክን በውዳሴና በነቀፋ በሚያቀርቡ ግለሰቦች ዘንድ እንደጭራቅ ይቆጠር የነበረው መይሳው ካሣ በለውጥ መሪነት የተፈለገበት መሪ ነበር። አብዮታዊው መሪ ጓድ መንግሥቱ እንኳ፥ “ቴዎድሮስ” (ምናልባትም ዳግማዊ ቴዎድሮስ) እኔ ነኝ። የዚህን ሕዝብ አብዮት እንድመራም ከሙታን የተጠራሁ ነኝ” እስከ ማለት ደርሰው ነበር። በቴዎድሮስ መንገድ አልተጓዘም እንጂ። በተረተኞች፣ በተረበኞችና በዋልጌዎች፣ በጐታቾችና በክፍፍል በኖሩ ዘንድ ተወዳጅ ያልሆነው ሕልመኛው ቴዎድሮስ በእርግጥ ከዘመኑ አርቆና አልቆ የሚያይ ስለሆነ ከወቅቱ ደባትርና ከመሳሰሉት ጋር ስምምነት አልነበረውም።

የአገር አመራር በተበላሸና ሕዝቡ የሚያምነው መንግስት ባጣበት፣ ብሔራዊ አንድነቱና ዳርድንበር አስከባሪ በሚሻበት ሰዓት ከመሐሉ የወጣ የጐበዝ አለቃ ሲያደንቅ ይገኛል። እንዲያ ካልሆነ ደግሞ ከአባት መሪዎቹ መካከል ያደነቀውን፣ የሚያደንቀውናና የሚያከብረውን መናፈቅ ይጀምራል። ባያውቀውም። ዛሬን ያስቡአል። አገር እንደ አቃቂ በሰቃ (ኮሎናልቤ) ከስኩት ፍርክስክሱ በወጣበት፣ ሕዝብ እንዲከፋፈልና እንዲጨራረስ ማናቸውም ዓይነት ሴራ በሚጐነጐንበትና መቀበሪያ ሳይቀር “እናገኝ ይሆን” የሚል ስጋት በተጫጫነን ሰዓት “የአንድነትን ጌታ” የአገሪቱን እውነተኛ አባት መናፈቅ ያለ ነው። እነዚህማ ሸጡን። እነዚህማ ለወጡን። መሬቱን ጋጡት። ከትውልዱ አባልነት መብታችን አንዲቱንም አላከበሩልንም። የአንድነትን አባት፣ የዘላለም ኩራታችን ምንጭ፣ ሁሉንም አበሻ በእኩልነት የመራውን ጀግና እንድንናፍቅ ጊዜው አስገድዶአል። ምኒልክን! ይኸ ደግሞ ከመካከላችን እንደ ምኒልክ ያሉ የአንድነት እምነት አራማጆች እስኪንቀሳቀሱ ድረስ ነው።

ነፃነት አንድን ሕዝብ ወደፊትና ወደላይ የሚያንደረድር (የሚወስድ) ኅይል ይሻል። ስለዚህ እውነተኛና ከዚህ በኋላ የሚመሩን (ከዘመኑ ቀድሞ እንደ ተወለደው ምኒልክ) ሰዎችም ወደፊት ብቻ ሳይሆን ወደ “ላይም” ሊመሩን የተዘጋጁ ናቸው። እነዚህ ቆነጃጅት አልተወለዱም አይባልም። እንዲያውም አይተናቸዋል። ዳስሰናቸዋል። ዓለምም አውቆአቸዋል። እኛ ግን ከጥቃት፣ ከእሥራት፣ ከእንግልት…ከመከራ አላዳናቸውም፥ እስክንድርን፣ አንዱዓለምን፣ በቀለን…ካድናቸው። ለወያኔ ወረወርናቸው ለአውሬ። አገርን የሚያድን መሪ ብቻ አይደለም። ዋናው ሕዝቡ ነው። በአድዋ ወሳኙን የመሪነት ሚና የያዘው ምኒልክ ነበር። የተዋጋው ሕዝቡ ነበር። ሕዝባችን ቅንና ጀግና መሪ፣ መሪውም ታማኝና ቆራጥ ሕዝብ ያገኘበት አንድ ወቅት ይኸ ነው።

በአንጻሩ በአመራር የጊዜ ማኅፀን ውስጥ ያሉት ወይም ቢወለዱም በአመራር ጉልምስና ዘመን ላይ የሚገኙት “መልካካም የኢትዮጵያ ልጆች” ወደ አገር አዳኝነቱ መንበር ሲመጡ የሚገጥማቸው ፈተና የትየለሌ ነው። ሁላችሁም አስቡት። የተሸጠ አገርና መሬት የማስመለስ ግዴታ ሊሸከሙ ነው። የተከፋፈለ የሕዝብ ይዞታ ሊያስተካክሉ ነው። የኢኮኖሚውን ሥርዓት መስመር ሊያስይዙት ነው። “ወደ ላይ መምራት” ባልሁት የአመራር ፈርጅ ደግሞ የሚጠብቃቸው ከዚህ ሁሉ በላይ ነው። በታላላቅ ዲታዎችና መንግሥታት ትእዛዝና መሪነት ሥር የወደቀችውን አገር ዜጐችዋ ባለሥልጣናት ይሆኑ ዘንድ መንገዱን መጥረግ አለ። የሕዝብን ነፃነት፣ መብትና ሕዝቡ በአገሪቱ ላይ ያለውን ሉዓላዊነት ማወቅና ማክበር አንዱ ነው። የሕብረተሰቡን መንፈሳዊና ባሕላዊ መብቶች ማረጋገጥና የመንግስትን ጣልቃ ገብነት ማስወገድ፣ የጽሑፍና አሳብን በነፃ የመግለጥ ተፈጥሮአዊ መብቶቹን መንከባከብ፣ ፍትሕና ርትእ በራሳቸው ጐዳና ከመጓዝ እንዳይታወኩ ማድረግ ማለት ነው። ዝርዝሩ በዚህ ይቀጥላል። በመሰረቱ ደግሞ ታሪክ ስትቆፍሩ ብትውሉ አገር የሸጠ፥ የአገር መሬት የቸበቸበ መሪ ታይቶ ተሰምቶ አይታወቅም። በውጭ ምስጢር ባንክ የተቀመጠውን ገንዘብ ቁልፍ መለስ ለሚስቱ ካልሰጣት እሱም በሞቱ ከስሮአል። እኛም ያንን ለማስተካከል ብዙ ጥረት ማድረግ ይጠበቅብናል። የእሱን ወንጀል።

ጆርጅ ኦርዌል በ1984 መጽሐፉ በአምባገነኖች አገዛዝና ዘመን “እውነት ውሸት፣ ማይምነት እውቀት፣ ጥላቻ ፍቅር..ይሆናል” ይላል። ስለዚህ የወያኔን ባሕርያት የምንረዳው ዛሬ አይደለም። አብረን ኖረን የመንግስት ጠባያት ያልሆኑ- መሆንም የማይገባቸውን ስርቆትን፣ ተራ ውንብድናን፣ ቅጥፈትን፣ የጅምላ ግድያን፣ ፀረ ሃይማኖት አቋምን፣ የመብት ረገጣን…በየዓይነቱ እንደ ቡልኮ ተከናንቦ አይተነዋል። አንዳንድ ፀረ ሕዝብ ተግባራት ከየት መጡ ሳይባል እንኳ “የእሱ ሥራዎች ናቸው” ማለት ቀላል ሆኖአል። ትግርኛ ተናጋሪ ወገኖቼ ፀላዔ ሰናይ ይሉአቸዋል። አንዳችም በጐነት ያልተፈጠረባቸው ለማለት ነው። የሰሞኑን ደንባራ ፖለቲካ ለአብነት ማውሳት ለተነሳንበት ጉዳይ ብርሃን ይፈነጥቃል ባይ ነኝ።
በቅጥፈት የተካነው ሰውየ ከተለያቸው ወዲህ ወያኔዎች ያንኑ የተለመደ ውሸት ከመደጋገም በቀር ሌላ መፍጠር፣ በሌላ ስልት ማወናበድ አልሆንላቸው ብሎአል። ውሸት እንደ ቅርስ በነገሠበት አምባቸው ደግሞ ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ ያላትና ያፈራችው መንፈሳዊና ስጋዊ ቅርስ ሁሉ አንደኛ መጥፋት አለበት፣ ዳግመኛም- አገሪቱ ካልጠፋች..ታሪክዋ ከዛሬ ተጀመረ መባል አለበት። ታሪክ ከእነሱ አልነሳ ሲላቸው አሁንም ያለፈውን በጐ ታሪክ፣ አኩሪ ባሕልና ጀግንነት፣ የአንድነት ጥበቃ መንፈስ…እንደ ቀላል ነገር ለመግደል ወጥተዋል።

ውሸታቸው ባያልቅም እውነት መናገር እንጀምር

ለዚህ ሥርዓት ማንኛውም ያለፈ ታሪክ፣ ታላላቅ ጀግኖች፣ ዳር ድንበር…የረከሰና የተናቀ፣ መለወጥና መደምሰስም አለበት። ሁላችሁም ለወያኔ ዓላማና ዛቻ፣ ቅጥፈትና ፀረ አንድነት እንግዳ አንዳለመሆናችሁ የሟቹንም ዛቻና አቋም ታስታውሳላችሁ። ስለ ሰንደቅ ዓላማ ምን አለ? ስለ አገሪቱ አንድነት ምን አለ? ምንስ ፈጸመ? ተከታዮቹስ ምን እያሉና ምን እያደረጉ ናቸው? በአጭሩ የሚነገረው ውሸት፣ የፈጠራ ታሪክና ከፋፋይ ፕሮፖጋንዳ አልቆ እናርፈዋለን ብለን ስናስብ ከቶውንም ወፍጮው ይበልጥ እየፈጨ ስለሆነ በውሸቱ መካከል ስለእነሱም እውነቱን መናገር መጀመር ያለብን ይመስለኛል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትሩማን “ሪፐብሊካኖች ስለእኛ ውሸት መናገርን ካላቆሙ ስለእነሱ ያለንን እውነት መናገር መጀመር ያለብን ይመስለኛል” ብለው ነበር።

ስለ ዳግማዊ ምኒልክ ጥቂት ከመናገሬ በፊት ስለ መለስ ጥቂት-እጅግ ጥቂት ለማለት እወድዳለሁ። የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ሲዘልፍ..ዋና ዓላማው የኢዮጵያን ስም መለወጥ ነበር። ስለዚህ ለብዙ ዓመታት ኢትዮጵያን በስም ከመጥራት ይልቅ “አገሪቱ” ነበር የሚለው። ሥልጣን ሲጥመውና አገሪቱም የማትፈርስ (በቀላሉ) ስትመስለው “ኢትዮጵያ” ማለት ይዞ ነበር።

ቀደም ሲል ጆርጅ ኦርዌልን ያነሣሁበት ምክንያት “ውሸት እውነት” የሚሆንበትን ትክክለኛ አጋጣሚ መከሰት በሚመለተው ነው። እንደሚባለው በአምባገነን መንግሥት ሥር የመጀመርያው ጥቃት የሚደርሰው “በእውነት” ላይ ነው። በሕዝባዊ እውነት ላይ! በታሪኩ ላይ ነው። በጀግኖቹ ላይ ነው። ስለዚህ በአገር የተገኘው ቀጣፊ ሁሉ ዛሬ በፕሮፓጋንዳው ሰፈር፣ በአራት ኪሎ ቤተ መንግስትና በየክልሎቹ አመራር አምባ የተሰባሰቡት የሥነ አእምሮ ጠቢባን (pathological liars) የሚሉአቸው የሚታዘንላቸው ሕመምተኞች፣ እውነትን የሚፈሩ፣ እውነት ሲነገር የሚደነግጡ፣ እውነት ሲወጣ የሚረበሹ ናቸው። ስለዚህ “አንድነት” በተፈተነበትና የአገር ሽያጭ በደራበት ሰዓት አንዱ ማወናበጃ ስልት ያው ምኒልክን በወንጀል መክሰስ ነው። “አምስት ሚሊዮን ኦሮሞ ገደለ” ነው አዲሱ አማርኛ። ለመሆኑ በምኒልክ ጊዜ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር ከ5 ሚሊዮን ይበልጥ ነበር? ከዚህ ውስጥ የኦሮሞው ቁጥር ስንት ነበር? ለመሆኑ ምኒልክ ማነው? ምን ሰራ? ሕዝብን ከጫጫታው (ከዘመኑ) ለማዳን መሞከር አለብን ወይስ ታሪክ ነፃ ያወጣዋል በሚል አደብ እንግዛ?
“ ጥቁሩ ሰው” – እንደ ሰው

ታሪክ የበጐነት ምስክር – ወይም ለበጐነት የሚያደላ እማኝ ብቻ አይደለም። የአጥፊዎችን ጥፋት፣ የከሐዲዎችን አሳፋሪ ተግባር፣ የአምባገነኖችን ክፋትና ኢሰብአዊ አገዛዝ ጭምር ዘግቦ ለትውልድ ያስተላልፋል። ይሁንና ታሪክ የማያውቁ አዋቂዎች በመምሰል፣ አዳዲስ ድርሰት በመጻፍ ከሐቅ ግድግዳ ጋር የሚላተሙ፣ በባሕርያቸው ፀላዔ -ሰናይና የእውነት ጠላትነት ያላቸው ደካማ ፍጡራን መድረክ ሲደላደልላቸው የሚያዥጐደጉዱት ቅጥፈት መታለፍ እንደማይገባው እየተከሰተልን መጥቶአል። እስካሁን ግን “ለቅጥፈት ማስተባበያ” ወይም ማስተካከያ አያስፈልገውን በሚልና ውሎ አድሮ ሐቅ ይረታል በሚል እምነት ቅጥፈት ቅጥፈትን፣ ፈጠራና ድንፋታ ራሱን ሲፈጥርና እንደአሜባ ሲራባ በቸልታ ያለፍናቸው ጉዳዮች ሞልተዋል። ከሁሉም ከሁሉም አንድን ኅብረተሰብ የሚያቃጥለው የታሪኩና የጀግንነቱ መታወቂያ ሰነዶች፣ ግለሰብ ጀግኖችና ብሔራዊ መከበሪያ ሐውልቶቹና ቅሪቶቹ መደፈር ነው። በዚህ ረገድ ብዙ ተደፈርን። በዓለም አቀፍ ደረጃ የ”ታላቅ መሪነት”ን ደረጃ የተቀዳጁትን፣ ጠላት ሳይቀር የሰገደላቸውን መሪዎቻችንን ሳይቀር ዛሬ የራሳችን ልጆች በእነዚህ ላቅ ያሉ ሰዎች ላይ ሲያቅራሩ ስንሰማ እንቅልፍ መንሳቱ አልቀረም።

የወያኔ ቀዳሚ ሰልፍና ፍልስፍና ሕዝብን መከፋፈልና አገሪቱንም ማፍረስ መሆኑን ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠራጥረው ይከራከሩን የነበሩ ሰዎች ዛሬ ከግንዛቤ በመነሳት ራሳቸው “አገር እየጠፋ” መሆኑን እያረዱን ነው። በወያኔዎች በኩል ደግሞ የአገሪቱንም ሲሳይ እያፈሱ መልሰው አገሪቱን ለማጥፋት ማናቸውንም ሴራ እየፈፀሙ ናቸው። የትሮትስኪ ታሪክ መዝጋቢና የሩሲያን አብዮት ክሽን አድርጐ ያቀረበው አይዛክ ዶቸር ስለ ሩሲያ አብዮት መሪዎች ሲጽፍ “እነዚህ ሰዎች የማያውቁትንና ሊያውቁ ያልቻሉትን አገር ተረከቡ። ወይም በእጃቸው አስገቡ። ቀጥሎም የሚያምኑበትን አቃጠሉት። አቃጥለውም ሰገዱለት” ይለናል። አዎን ወያኔዎች ጥገትዋን አልበው እየጠጡ፣ አርደው ሊበሉአትም ፈለጉ” ለማለት ይቻላል። በተአምር በእጃቸው የገባችውን አገር ማዳን የብዝበዛቸውና የዘረፋቸው ዋስትና በሆነ ነበር። ይልቁን እዚህ ከደረሱ በኋላ እንኳ የዚህን አገር አንድነት ማዳን ቢሞክሩ ቢያንስ ልጆቻቸው አገር አለን እንዲሉ ባስቻላቸው ነበር። ይልቁንም ኦሮሞዎች ነን የሚሉ በዕድሜም፣ በግንዛቤና በአእምሮ ያልበሰሉ ልጆችን በመመልመል የሚያንጫጩብን እነዚሁ አገር በእጃቸው የወደቀ ሰዎች ናቸው። ምኒልክን ለመወንጀል የክሱን ነጥብ ሁሉ ከየት አገኙት?

እውን እነዚህ ጨርቋ ሕፃናት – የጨርቋ አእምሮ ውጤት የሆነ ፕሮፓጋንዳ በጩኸትና ሰላላ መላላ በሆነ ልሳን ሲያስተጋቡ የዚህ አገር ዋልታና ወጋግራ የሆነው ኦሮሞው ኅብረተሰብ ምንኛ እንደሚያፍርባቸው ትገነዘባላችሁ? ለመሆኑ ከኢትዮጵያ ታሪክ ባለቤትነትና ክብር ሊነጥለን የሚችል ማነው? ጃዋር? አያት ቅድመ አያቶቻችን ደምና አጥንት የሰጡአት አገርኮ ናት! የወያኔ የመስዋዕት ጠቦቶች ለሆኑት እነዚህ ኅፍረተ ቢሶሽስ የኦሮሞን ውክልና ማን ሰጣቸው? ስለማያውቁት፣ ስላላወቁትና ሊያውቁትም ስላልፈለጉት ሕዝብ በድፍረት መናገርን ከየት አመጡት? እነዚህ ልጆች “ወገኔ ነው” የሚሉትን ኦሮሞውን ኢትዮጵያዊ ከሌሎች (ለምሳሌም አማራው) ብሔሮች ጋር በማጋጨት ሊያመጡ የሚችሉትን ትርፍ ሊነግሩን ይችሉ ይሆን? ወይ ልክፍት!

ከሶቪየት ኀብረት ኤምፓየር መፍረስ በኋላ አንዳንድ የአሜሪካ የፖለቲካ ፈላስፎች እንደ ሶስተኛ አገር የሚታዩ የኅብረተሰብ ጽናትና ሰላም ያላቸው አገሮች በተቻለ መጠን ተሸንሽነው ብዙ አገሮች እንዲወጣቸው ሰፋፊ ጽሑፎችን በገበያ አውለዋል። ከእነዚህም መካከል መለስ ዶላር ያፈስስለት የነበረው የሐርቫርዱ ሳሙኤል ሐንቲንግተን ይገኛል። ከዚያም ሌላ አንዳንድ የሲአይኤ ቅጥረኞች ጽሑፎች በየጥናቱ መደብር አሉ። ዩጐዝላቪያ የዚህ ፍልስፍና “ጊኒፒግ” ናት። ከ1991 ወዲህ ደግሞ ኢትዮጵያ የምትታመሰው በዚሁ ረቂቅ የጥፋት አውሎ ነፋስ መሆኑን አንዘንጋው። እነሆ እንደ ጃዋር ያሉ አለማወቃቸውን እንደ እውቀት፣ ጮኾ መናገርን እንደ ሐቅ፣ የፈለጉትን ጥጃ የአምልኮ ጸጋ በመቁጠር አየረ አየራቱን ሲያተረማምሱት ከእንግዲህስ “ተመከር! ተሳስተሃል! በአገር፣ በሕዝብና በታሪክ ላይ ያመጽህ ባለጌ ነህ” ማለት የሚገባ ይመስለኛል። ልድገመውና “በአባቴ ሙስሊምና ኦሮሞ፣ በእናቴ ክርስቲያንና አማራ ነኝ” በማለት ጅምሩን በማይጠቅመው መደምደሚያ ያበላሸዋል። ጃዋር መሐመድ። ሙስሊም፣ ክርስቲያን፣ አማራ፣ ኦሮሞ! ከኢትዮጵያዊነት ውጭ ምን ይሁን?

ጐበዝ በዚህ ዓይነቱ ጊዜ ከየጉድጓዱ ብዙ አይጦች ሊወጡ ይችላሉ። አትደነቁ። አንዳንዶቹ የመታወቅ አባዜ (የእንክብካቤ እጦት አባዜ…ወዘተ) የተከሰተባቸውና “እገሌ” ለመባል የሚጣባ ሕመም ተሸካሚዎች ናቸው። አንዳንዶቹ ቀጥታ ራሳቸውን ለማያውቁት ተልእኮ በመስዋዕትነት ለመሰጠት በምንዳ የተገዙ ናቸው። ለዚህ ዓይነቱ ተልእኮ የተመደበ በጀት ስላለ ሰው ከተገኘ ገዥ አለ። ሕሊና ለሌለው፣ ለሚሸጥ ወይም ለሚያከራይ ዘወትር ክፍት ቦታ አለ። እነ እንቶኔ በዚህ የሕመም ዘርፍ ላይ በመሆናቸው ሊታዘንላቸው እንጂ ሊታዘንባቸው አይገባም። ቀደም ሲል የተጠቀሰውን ጉብል አንድ ጊዜ በአንድ የቨርጂኒያ አዳራሽ ትልቅ ስብሰባ ላይ አይቼዋለሁ። እዚያ ስብሰባ ላይ ወደ ዘጠኝ መቶ የሚጠጉ ሰዎች ነበሩ። ይሁንና እስኪታወቅ ሳይሆን እስክንሰለቸው ድረስ የባጡንም የቆጡንም ሲናገር ቆይቶ “እዚህ ሥፍራ ኦሮሞና ሙስሊም ለምን አልተጋበዘም?” ይላል። መቸም “ከእናንተ መካከል ኦሮሞ የሆናችሁ ተነሱ! ሙስሊም የሆናችሁ ተነሱ!” አይባልም። ይኸ ደግሞ ከቅን አእምሮ የመነጨ ነው አይባልም። የሌሎቹንም “ዋልጌ ጭንቅላት” ባለዶላሩ ዋሐቢ፣ የሽብሩ ልጆች እነ…..በማናቸውም ሂሣብ ሊገዙአቸው አይፈልጉም አይባልም። ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን እስከ ተዋጉላቸው ድረስ።

አንዳንድ የዋሐን ወገኖቼ የእነዚህን በጥላቻ የተፀነሱ፣ በጥላቻ የተወለዱና የጥላቻን መርዝ በመካከላችን የሚዘሩ ሰዎችን ተጽእኖ እስከ መፍራት ደርሰዋል። ኦሮሞው ኅብረተሰብ እንዳይቀበላቸው ነው? ያፍርባቸዋል። ከአገር እድር ያስወጣቸዋል። ስለዚህ በሶሻል ኔትወርኩ ረገድ ኅላፊነት የወሰዱ ሁሉ ለኦሮሞ ወገኖቻችን የመናገር ዕድል (በሰፊው) መክፈት አለባቸው። በአንድ በኩል ደግሞ ታሪክ የሚያቆሽሹትና ወደ ኋላ እየተመለከቱ የሚናገሩት እነዚህ ወገኖች ርስበርሳችን ስለጀግንነት፣ ስለታሪክ፣ ስለታላቋ ኢትዮጵያ ማንነትና ምንነት….እንድንነጋገር ዕድል እያስገኙልን ይመስለኛል።

ጥቁሩ ሰው – ለጥቁር ሕዝቦች

ጀርመኖች በኦቶፎን ብዝማርክ፣ ጣልያኖች በጁሴፔ ጋሪባልዲ፣ ፈረንሳዮች በናፖሊዮን ቦናፓርቲ፣ በዣንዣክ ሩሶ፣ በዣን ደ አርህ፣ አሜሪካኖች በጆርጅ ዋሽንግተን፣ አብርሃም ሊንከን…..እንግሊዞች በዊልያም ዘኮንከረር፣ በዊንስተን ቸርችል፣..ይኰሩም ይኩራሩም ይሆናል። የእነዚህን ሰዎች ጀብዱ ስንሰማ፣ በትምህርት ቤቶች ዝናቸውን ስናወሳና ስናጠናቸው ስለኖርን የራሳችን ሰዎች እስኪመስሉን ድረስ በልባችን ጽላት ላይ ታትመዋል። ሰዎቹ በየዘመናቸው ለአገሮቻቸው ባበረከቱአቸው አስተዋጽዎችና የተለዩ አገልግሎቶች የየአገራቸው “አባቶች” እስከ መባል ደርሰዋል። በፖለቲካና በወታደራዊ መስክ ብቻ ሳይሆን እነዚህ አገሮች ብቻ ሳይሆኑ ሌሎችም አያሌ አገሮች ለአለም ጸጋ በሆኑ ልጆቻቸው አማካይነት በኪነ ጥበባት፣ በሳይንስ፣ በሥነ ጥበባትና በኬንያ (ቴክኖሎጂ) ባርከውናል። ልጆቻቸውን ተጋርተናል።

እንደገና ጀርመኖች በሒትለር፣ ጣልያኖች በሙሶሊኒ፣ ካምቦድያውያን በፓልፓት፣ ኡጋንዳውያን በኢዲአሚን፣ወዘተ እጅግ እንደሚያዝኑና እንደሚሸማቀቁ ይሰማኛል። እኛም የዚች አገር ጐስቋሎች ኢትዮጵያውያን በሃያ አንደኛው ምዕት ዓመት መለስ የሚሉት እኩይ ነፍስ ለኢትዮጵያ የዛሬው ትውልድ በመስጠታችን ጭብጥ ልናክል ነው። ሞተ ከተባለ ወዲህ እንኳ አገር እየሰጠ፣ አረብና ሕንድ እያነገሰብን፣ ምውት መንፈሱ እንዳሸበረን ነው። ሁላችንም የዓለም ዜጎች ይቺን የጋራ መሬት እኩል እንደምንባረክባት ሁሉ ጀግንነታቸው ያሞቀን የሃያኛው ክፍለ ዘመን ግዙፋን ባለታሪኮች ነበሩ። ጀኔራል ድዋይት አይዘንሐወርን፣ ጀኔራል ጆርጅ ፓተንን፣ ፊልድ ማርሻል ሞንትጐመሪን…እንደራሳችን እንጋራለን የሚል እምነት አለኝ። “እነዚህ ሰዎች ምነው ኢትዮጵያውያን ቢሆኑ ኑሮ” ብዬ በቁጭት አልናገርም። የአንዲት ምድር (ራችን) ልጆች በመሆናቸው ብቻ እንደራሳችን ጀግኖች- የሁላችንንም እምነት በተግባር ያዋሉ፣ የሁላችንንም ጦርነቶች ተዋግተው ያሸነፉ ስለሆኑ “የሁላችንም” እናደርጋቸዋለን። እንደ ምኒልክ ያሉ – እንደ ጐበና ያሉ- እንደ አሉላ ያሉ- እንደ አበበ አረጋይና በላይ ዘለቀ ያሉ ጀግኖች አባቶች ያሉት አገር ልጆች በመሆናችን እኛም ለዓለም ባበረከትናቸው ጀግኖቻችን ኩራት ይሰማናል። በምኒልክ የተመራው የኢትዮጵያ ሠራዊት በአንዲት ጀንበር የአንድ አውሮፓ ኅይል ካንኮታኰተ በኋላ በማግሥቱ የጠቅላይ ሚኒስትር ክሪስፒ መንግሥት (በኢጣክያ ሕዝብ እንደጐርፍ መውጣት ምክንያት) ከሥልጣን ከመወገዱም በላይ በናፖሊ ከተማ የነበረውን የንጉሡን (አምቤርቶ) አልጋ ወራሽ ሕዝቡ በትከሻው ተሸክሞ “ታላቁ ምኒልክና የአድዋ ጀግኖች ኢትዮጵያውያን ለዘላለም ይኑሩ ብለህ ጩኽ” በማለት ቀኑን በሙሉ በዚህ መልክ ሲያንባርቅ እንዲውል አድርገውታል። በማግሥቱ የወጡ የኢጣልያ ጋዜጦች ኢጣሊያ ራስዋ እንደተማረከች አድርገው ጽፈዋል። ምኒልክ!
አንዳንድ የጦርነት ዘገባዎችን፣ መጻሕፍትንና ታሪኮችን ለተከታተሉ ጀግኖች የሠራዊት አዛዦች ድል ካደረጉ በኋላ “ጠላት ነው” በማለት አይንቁትም። ወይም በእጄ ገብቶአል ብለው አይበቀሉትም። እንዲያውም በ”ተቃራኒ መስክ” የተሰለፈውን በክብር ያስተናግዱታል። በጦር መሪነታቸው እጅግ የተደነቁና በመሠረቱ በተቃራኒ ዐውድ ተሰልፈው ታሪክ የሰሩ ጄኔራል መኰንኖችን ላስታውስ እወዳለሁ። በአሜሪካ የሲቪል ጦርነት የኮንፌደሬሽኑ ጦር አዛዥ ሮበርት ሊ በአሜሪካ ሕዝብ ዘንድ ከሜጀር ጄኔራል ጆርጅ ማክሊላን የበለጠ ይታወቃል። በየከተማው መንገዶች ተሰይመውለታል። የጦር ምሽጐች በስሙ ተጠርተዋል። ከስለጠነው ዓለም ሌላም ማስረጃ ለማምጣት ይቻላል።

የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ከሚያውቃቸው ታላላቅ ጄኔራሎች መካከል ሒትለር በሰሜን አፍሪካ በዋና አዛዥነት ያሰለፈው ፊልድ ማርሻል አርዊን ሮሜል (የበረሃው ተኩላ) በምዕራብም ሆነ በምሥራቅ- በአክሲስ ፓወርስም ሆነ በአላይድ ፎርስስ እጅግ የተደነቀ ነው። በመሠረቱ ለጀግና ሠራዊት ባላንጣው የተከበረ ነው። በሬሳው አይጫወትም። ወይም ወያኔዎች በኢትዮጵያ ሠራዊት ሬሳና የደከመ አካል ላይ ቆመው እንደ ፈነደቁትና እንደሸለሉት ሳይሆን የሰብአዊነት ክብርና መገመቻ ጠላትን እንደአግባቡ ማድነቅ መቻልም ነው። ለተፋላሚ ክብር መስጠትና እንክብካቤ ማድረግ ነው። እነዚህ ሰነፎች ገዥዎቻችን ምንኛ ደካሞች እንደሆኑ አያችሁት?

ከአገራችንምኮ ለዚህ ክርስቲያናዊ አርአያነትና የሰለጠነ ወታደራዊ ባሕል ምሳሌ አንቸገርም። አድዋ ላይ በአንድ ጀምበር በርከት ያሉ ጄኔራል መኰንኖችን ድባቅ የመታውና ያንኑ ያህል የማረከው እምዬ ምኒልክ በእጃቸው የገቡትን ምርኮኞች ማለፊያ ምግብ እየሰሩ (ፓስታ፣ ሞኮሮኒ ወዘተ) በደንብ ከመመገብ ባሻገር ራሳቸውና ደገኛይቱ ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ እንደ ሐኪም ቁስል መጥረግ፣ ፋሻ ማሠርና የመሳሰሉትን የሕክምና አገልግሎቶች ጐንበስ በማለት ፈጽመዋል። ጦርነቱ እንዳለቀ ምሽት ላይ በየድንኳኑ እየተዘዋወሩ “ገደልን ብላችሁ እንዴት እንዲህ ያለ ፍከራና ሽለላ ታደርጋላችሁ?” በማለት ኅዘናቸውን እስከ መግለጥ ደረሰዋል። (አንቶኒ ሞክለር ኅይለስላሴስ ዋር በሚለው መጽሐፉ በመጀመሪያው እትም እንደ መግቢያ አድርጐ ገልጦታል።

በሌላው ታሪካቸው እንደ ተገለጠው አጤ ምኒልክ ከንጉስ ተክለሃይማኖት (ራስ አዳል ይባሉ ከነበሩት) ጋር እምባቦ ላይ ሲዋጉ የጐጃሙ ገዥ ቆስለው ሲማረኩ ራሳቸው ከመሬት ተቀምጠው ቆስሉን በጨውና በአልኮል እየጠረጉ እንዳስታመሙአቸው ይታወቃል። በኋላ ደግሞ አጤ ዮሐንስ ያለ የሌለ ጦራቸውን አስከትተው ጐጃምን ወርረው፣ ሥፍር ቁጥር የሌለውን ሕዝብ ዓይን በጋለ ብረት አቃጥለው፣ ሠራዊታቸው ቤት እየዘረፈ፣ በወንዱ ፊት ሚስቱን እየደፈረና ጐተራ እያራገፈ በጠቅላላው ንጉሰ ነገሥቱ እያዩ ሲያቃጥሉ አጤ ምኒልክ “እባክዎ ጃንሆይ ከንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ጋር ተጋጨሁ ብለው ሕዝብዎን አይጨርሱት” በማለት እንደተማጸኑአቸው የተጻፈ ታሪክ ሞልቶአል። እንዲያም ቢሆን የትናንት የአገሪቱን መሪዎች ለመወንጀል አልሻም።

ወደ ሃምሳ ዓመት የሚገመት ሙያዬ ከብዙ ሰዎች ጋር አገናኝቶኛል። እንደ ደጃች ኅይለ ሥላሴ ጉግሳ ካሉ ከሐዲዎች- እንደ ራስ መስፍን ካሉ አርበኞች- እንደ ጋዜጠኛ (ከንቲባ) ደስታ ምትኬ ካሉ በየአድዋው ጦርነት ላይ ከዋሉ የታሪክ ምስክሮች፣ እንደ ፊታውራሪ ተክለሃዋርያት ካሉ በ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ አንስቶ አገሪቱን ከፊውዳል ሥርዓት ለመጠራረግና የፖለቲካውን ሥርዓት ግልብጥብጡን ለማውጣት ከደከሙ ምሁራንና መሪዎች ጋር ትከሻ ለትከሻ ባልተሻሽም አጠገባቸው ተቀምጨ ያልነበርሁበትን ዘመን ልኖረው ሞክሬአለሁ። የሁሉም የጋራ ምስክርነት (የጀግናውም የባንዳውም) ኢትዮጵያ እንደ ምኒልክ ያለ መሪ ታድላ አታውቅም። እግዚአብሔር ይመስገን፤ ጻድቁ ዮሐንስ በጐ አእምሮ የወለደው ነው።

አዎን የዚህ መጣጥፍ አጀማመሬ አውሮፓውያንና አሜሪካውያን (ሌሎችም ሕዝቦች) የሚኮሩባቸው መሪዎችና በመሰረቱም የሚያፍሩባቸው አምባገነኖችም ሊኖሩባቸው እንደሚችል ላመለክት ሞክሬአለሁ። እንዲያውም አገር በችግር ማጥ ውስጥ ስትገባ ልባቸውን፣ ጭንቅላታቸውንና እጃቸውን አስተባብረው ሕዝብን በአንድ ጐራ አሰልፈው ከታላቅ ውጤት ላይ ያደረሱት እንዲህ ያሉ መሪዎች የየአገሮቻቸው አባቶች እስከ መባል ደርሰዋል። ጆርጅ ዋሽንግተንን አላነሣሁምን? የመቶዎች ባሪያዎች ባለቤት ቢሆን እንኳ ሁሉም አሜሪካዊ የአገሪቱ አባት ይለዋል። በዚሁ ልክ የኢትዮጵያን ታሪክ የመረመሩ የውጭ አገር የታሪክ ስዎችና ኢትዮጵያውያን ምሁራን ሁሉ አጤ ምኒልክንና አሳዳጊ አባታቸው አጤ ቴዎድሮስን የኢትዮጵያ አባቶች ይሉአቸዋል። ለከፈሉት የሞት ዋጋ፣ ለተሸከሙት የኢትዮጵያ ግዙፍ ተራራ፣…ይኸ የሚበዛባቸው ክብር አይደለም። ሁለቱ ሰዎች (ባይሆን ጣይቱን እንጨምራለን) ይህን ክብር ካልተቀዳጁ ማን ሊቀዳጅ ነው? ጣይቱን እናታችን ብንል ምንኛ ደስ ባለኝ!

ያለፈው ወር የእምዬ ምኒልክ መቶኛ ሙት ዓመት ነበር። አሸናፊዎች ሁሉንም እንደ ፈለጋቸው በሚያደርጉበት፣ በብር በወርቁ በሚያዙበት፣ ታሪክ ድርሰት ሆኖ በማረሻ በሚጻፍበት፣ የአገር ዳር ድንበር ያለ ጠባቂ በሚቀርበት፣ ጀግኖች የወደቁለት አንድነት መጫወቻ በሆነበት፣ ዜጐች እየተነቀሉ ነጩ፣ ብጫው፣ ጠይሙ…የባዕድ አገር ነጋዴ የሚምነሸነሽበት መሬት ጥንቡን በጣለበት ዘመን ላይ፣ መንግስት ሌባ፣ ሌባም መንግሥት በሆነበት ወቅት-እንደ መገኘታችን ብዙ ብዙ -የለም፤ ሁሉም በጐ አገራዊ ባሕል ትርጉም ባጣበት ሰዓት በሕዝብ ዘንድ ያለው ሐቅ ሁሉ ተጠቂ መሆኑ አንድና ሁለት የለውም። እነሆ ከሃያ ሦስት ዓመታት ወዲህ የኢትዮጵያ ታሪክ ተለውጦ ስለኢትዮጵያ አንድነትና ታሪክ የቆመው ሕዝብና ተቃዋሚ ኅይሎች ከሐዲ ሲባሉ…ወርቁም ሚዛኑም እንዳልነበረ ሆኖአል። ስለዚህ በምኒልክና በጣይቱ ላይ የሚወርደውን የፕሮፓጋንዳ መዓት፣ የፈጠራ ድርሰትና ልብ ወለድ ድርሳን ስታስቡት ለመሆኑ ከወያኔ አምባ የተጠበቀው ሌላ ንግርት ምን ነበር? በግልጽ የኢትዮጵያን አንድነት ተቋቁመው ከዚህ ደረጃ ያደረሱት ግለሰቦች በረከት፣ ስብሐት ነጋ፣ ዐባይ ጸሐይና ግልገል ወያኔዎችና እንደ ወያኔ የማሰብ በሽታ ከሸመቱ ግለሰቦች ምን ይጠበቅ ነበር? የኢትዮጵያን አንድነት አባቶችና ጠባቂዎች እንዲያወድሱ ነበር? ቀደም ሲል እንዳልሁት ታሪካችንን በጽሞና እንድንመረምር ዕድል የሰጡን ይመስለኛልና በበጐነት እንጠቀምበት።

ቀደም ሲል ስማቸውን ያነሣኋቸውን ጋሪባልዲንና ቢዝማርክን ለምክንያት ነበር የጠቀስሁአቸው። ጋሪባልዲ ኢጣልያንን ለማዋሐድ፣ ቢዝማርክ ተበታትና የቆየችውን ጀርመንን አሰባስቦ አንድ አገር (ኔሽን) ለማድረግ ሲወጡና ሲወርዱ የነበሩበት ሰዓት (በዘመነ ጓድነት) አንድ ነው። አፍሪካዊው መሪ (ጥቁር ሰው) ምኒልክ በተመሣሣይ ጥሪ በታሪክ መድረክ ላይ የታየውም በዚሁ የታሪክ ወቅት ነው። በዚህ ታሪካዊ ወቅት ምን ተፈጠረ? በዘመናት ውስጥ ተሸርሽራና ተበጣጥሳ የቆየችውን ኢትዮጵያ ዳር ድንበር አንድ አደረጉ። ሰበሰቡአቸው። በእነዚህ ተግባራት ብቻ ዓለም ካደነቃቸው ከነጋሪባልዲ ጋር ታሪክን ሊሻሙ የሚገባቸው ምኒልክ ዛሬ በወያኔና አንዳንድ አጫፋሪዎች ምን እየተባሉ ነው? አንዱና ጥሩ ውሸት መፍጠር ያልቻሉት ፀረ አንድነቶች የጡት ቆረጣ ወንጀል ነው። ይኸ ከየት የመጣ ነው? ለመሆኑ ወንጀሉስ የት ነው የተፈጠረው? ትክክለኛም ሆነ አልሆነ መልስ የመስጠቱን ዕዳ የሚሸከሙት ወያኔና ሁሉም ፀረ አንድነት የሚያቀነቅንበት ዜማ የሚጫወቱት ናቸው።

በሌላ በኩል ደግሞ የኦሮሞ ሴቶችን ጡት ስለማስቆረጥ የተፈጠረው አጉል ነጥብ ከአማራው (ማለትም ከክርስቲያን) ባሕልና እምነት ጋር ጨርሶ የሚሄድ አይደለም። በአንጻሩ ለጋብቻና ለመሳሰለው ዕድሜና እጆቹ እርፍ ለመጨበጥ የደረሰ ኦሮሞ ገበሬ ሚስት ሊያገባ የሚችለው አማራ በመስለብ መሆኑን እንኳ ለመስማት ፈልጌ አላውቅም። በእውነቱ ግን ወንጀሉ በየዘመኑ ለሚፈጠር ኦሮሞ ሁሉ እንዲቆየው አልሻም። በዚሁ ዓይነት አጤ ዮሐንስ ወሎንና ጐጃምን “ፈጅተውታል፣ አቃጥለውታል” በሚል የዛሬና የወደፊቱ ጐጃሜና ወሎየ ሁሉ ትግሬንና አጤ ዮሐንስን እንዲጠላ አላደፋፍርም። በውነቱ ደግሞ ዘወትር የምናወድሰው ታሪካችን አላስፈላጊና አሳፋሪ ጓዝም አለው። ቀደም ሲል ያነሳናቸው የኢጣልያንና የጀርመን የዛሬ ትውልዶች የየራሳቸው አንካሳ ታሪክ አላቸው። እኛ ላይ ሲደርስ ነው ከተደረገውና ከተፈጸመው ሁሉ በላይ የታሪክ ድሪቶና ቡትቶ ያየነው።

ኢትዮጵያዊነት አረጀ?

ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትንና የዚችን አገር ቁሳዊና መንፈሳዊ ሀብታት፣ ዜግነትንና እሴትን የሚጸየፍ አንድ ምስኪን ልጅ በአልጀዚራ ሲናገር ብዙ ኢትዮጵያውያን ሰምተውታል። የጋናው ኒክሩማህ፣ የኬንያው ኬኒያታ የኮትዲቮሩ ሑፌትቧኘ፣ የማላዊው ካሙዙባንዳ…በጆርጅ ፓድሞን መሪነት..ወደ አንድ የለንደን የስብሰባ አዳራሽ (በ1953 እ.አ.አ) የገቡበት ሁኔታ ትዝ ይለኛል። አዳራሹ በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አሸብርቆአል። እነዚህ በኋላ የአፍሪካ ታላላቅ መሪዎች የሆኑ የዚያን ዘመን የነፃነት ታጋዮች አረንጓዴ፣ ብጫና ቀይ የሆነውን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ እያውለበለቡ ወደ አዳራሹ ሲገቡ የነበረበትን የክብር ሰልፍ ሳስብ በቦታው ለመገኘት እንደ ታደለ ሰው ዛሬ የልቤ ኩራት ወደር ያጣል! የጃንሆይ አጤ ኅይለሥላሴን ምስል በኮታቸው ክሳድ ላይ ያደረጉት እነ ንክሩማህ ሁኔታ ወለል ብሎ ይታየኛል። አዳራሹ በአእምሮዬ ይመጣል። ኢትዮጵያዊነትና “ኢትዮጵያዊ ነኝ” የዓለም ጭቁን ሕዝቦችና በተለይም የጥቁር ሕዝብ ኩራት እንደሆነ እነ ጃዋር ሰምተው ያውቃሉ? ለጥቁር ሕዝቦች ሁሉ “ኢትዮጵያ” ምን ትርጉም እንደምትሰጥ ለመሆኑ እነዚህ ይቺን አገር ካላፈራረስን እንሞታለን የሚሉ ሰዎች በመጠኑስ ቢሆን ያውቁ ኖሮአልን? “ኢትዮጵያዊነት” ከተራ ስያሜና ከአንድ ተራ አገር መጠሪያ በላይ መሆኑን ያውቁ ኖሮአልን? ለእነዚህ ሕዝቦች ዞሮ መግቢያና መመኪያ …መንፈሳዊ ቤታቸውና ምስለ-ገነት የመሆንዋን ሐቅ ምን ያህል ሰምተዋል? የማርከስ ጋርቪን ፍልስፍና ያውቁታልን? ዛሬ ዛሬ ደግሞ እግዚአብሔር (ያህዌ ኤሎሒም) ለአዳምና ለሔዋን የፈጠረላቸው ገነት በአንደኛዋ የኢትዮጵያ ክፍል የመሆንዋ ግልጽነት አማራውን፣ ኦሮሞውን፣ ትግሬውን፣ ከምባታውን፣ ሐድያውን…ለሁሉም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አባላት ተጨማሪ ኩራት በሆነ ነበር። (ከላይ የነካካኋቸውን ነጥቦች በይበልጥ ለማወቅ ማርከስ ገርቪንና ዱቢድ ሜሬዲትን ያነብቡአል።) በነገራችን ላይ ማርከስ ገርቪና ራስ መኮንን ይባል የነበረው ጃሜይካዊ ጓደናው በጃንሆይ ቅሬታ ያደረባቸው እነሱ ካሰናዱአቸው 3ሺ ዓለም አቀፍ ተጋዳዮች ይልቅ በእንግሊዝ ጦር በመጠቀማቸው መሆኑ ይነገራል።

በኢትዮጵያዊነት ማፈር እንደ አልጀዚራው ጉብል ባሉ የሐቅ ማይማን እየተነገረ ነው። ያ ጉብል – ጃዋር ደግሞ በሌላ ጊዜ በመቅለስለስ መልክ “ እኔ በአባቴ ኦሮሞና ሙስሊም፣ በእናቴ አማራና ክርስቲያን ነኝ።” ሲል አድምጨዋለሁ። የልጅነት ተማሪዬ ሌንጮ ለታ የደረሰበትን አጉል አጋጣሚ ያስታውሰኛል። የኦነጉ መሪ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ልብ ሲዘዋወር በነበረባቸው ወራት በጣም የተከበሩ አባቶች ወደ ነበሩበት ወደ ጅባትና ሜጫ ሄዶ ነበር። ያ አካባቢ እጅግ አስተዋይ የሆኑት ፊታውራሪ አባዶዮ ሠርገኛ ጤፍ አስመጥተው “ከዚህ መካከል ነጩንና ጥቁሩን ለይልኝ” ብለው ጥላቻንና ጠላትነትን ያወገሁበት አካባቢ ነው። ታዲያ ሌንጮ “አማሮች ያገኙን እንደእነዚህ እንስሳት ከብቶች አድርገውን ነው” ብሎ ሲጀምር “ልጆቻችንና ወንድሞቻችን..አንተ የምትላቸው አማሮች ናቸው። እኛም አማሮች፣ አማሮችም ኦሮሞዎች ናቸው።” ብለው በማስጠንቀቂያ ሸኝተውታል። የሮይተርን ቀጥታ ምስክርነት ለመጥራት እችላለሁ። ታዲያ ጃዋር እንደ ነገረን፣ ኦሮሞም ነው። አማራም ነው። ሙስሊምም ነው ክርስቲያንም ነው። ኢትዮጵያዊ ካልተባለ ምን ሊሆን ፈለገ? ቅጥ አምባሩ የጠፋበት አይደለም ትላላችሁ?

እነዚህን ሰዎች ሳስብ ኢሳይያስና መለስን አስባለሁ። የኦሮሞ ነፃነት ግንባር የሚለውን ድሪቶ የለጠፈባቸው ኢሳይያስ አፈወርቂ ነው። ወይም ኦነግን ጠፍጥፎ የሰራው እሱ ሲሆን “ኦሮሚያ” የሚለውን በታሪክም በተረትም የማይታወቅ የሕልም ዓለም ክልል ስያሜ ደግሞ በዳቦ ስምነት ያሸከማቸው አስመሮም ለገሰ የተባለው የእኛው ዩኒቨርሲቲ ውጤት ነው። በነገራችን ላይ የአስመሮም ለገሰ የገዳሥርዓት መጽሐፍ እስኪወጣ ድረስ ኦሮሚያ የሚባል ቃል አላውቅም ነበር። እንደ ነገሩ ደግሞ መጽሐፍ አገላባጭ ሰው ነኝ፥ እላለሁ።
የኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ-ይልቁንም መንግሥታዊው መድረክና አጀንዳ የፀረ አንድነቱ አቋም ማራገቢያ እንደ መሆኑ አገሪቱን ወደ ማፍረስ እየረሸጋገሩም ይመስላል። ለሱዳን፣ ለሳዑዲ፣ ለሕንድ፣ ለቻይና፣ ለፓኪስታንና ዶላር ላለው ሁሉ ተከፋፍሎ የተረፈውን ማለቴ ነው። ከዚህ መሠረትነት በመነሳት የሺህ ዘመናት ሥልጣኔ የነበረው የኦሮሚያ በአማሮች ተወርሮ “ኢትዮጵያ” የተፈጠረችው ከአንድ መቶ ዓመታት ወዲህ በዚያ መንግስት ፍራሽ ላይ ነው እየተባልን ነው። የዜጐች፣ የታሪክ ተመራማሪዎች ዝምታ ለተረትና ለቧልት መፈጠር፣ ለልብ ወለድ ታሪክ መፈብረክ አስተዋጽዖ አድርጐአል። ኦሮሞው ኅብረተሰብ (በብዙዎች አካባቢዎች- ለምሳሌ በወሎ ወዘተ ጋላ ማለት ስድብ ሳይሆን የተከበረና ትርጉሙም ትልቅ ማለት ነው) የዚህ አገር ታሪክ ተጋሪ፣ ፈጣሪና በግንባር ቀደምም እንደ አገሪቱ ዳር ድንበር ተከላካይና መከታ ሆኖ የቆየ ነው። አንዲት የምኒልክ ስንኝ በማስታወሻነት ከእናንተ ጋር ባቆይስ? እነሆ!

“ጐበና ጐበና ጐበና የኔ
የጦር ንጉሥ አንተ ያገር ንጉሥ እኔ” አዳዲሱ ድርሳናቸው ከዚህ ሐቅ ጋር የሚጋጭባቸው ደራስያን “አዳዲስ ታሪክ የመጻፍን የአሸናፊዎች አንበሶችን ሚና” ይዘዋል። እኛም ማፈሪያዎች እነሱም ማፈሪያዎች ነን። ይህን እንቀበል!

ስለ ጥቁሩ ሰው

ወደ ሌላ ከመሻገሬ በፊት ከምኒልክ የተለያዩ ጠቅላይ ገዢዎች መካከል ዋነኞቹ (ሦስቱ) ስለ አገርና ስለ ምኒልክ የነበራቸውን ቁምነገሮች ለማንሳት እወድዳለሁ፤
“ምኒልክ ትንሽዋን ወላይታ ወስዶ ትልቂቱ ኢትዮጵያን ሰጠኝ። በእውነት ምኒልክ የእኔም የኢትዮጵያም አባት ነው። – ካዎ ጦና ጋጋ – የመላው ወላይታ ርእሰ መሳፍንት ልጅ እያሱ ቀድሞ ኩምሳ ሞረዳ ይባሉ የነበሩትን የደጃች ገብረእግዚአብሔር ሞረዳን ልጅ ለማግባት ጥያቄ ሲያቀርቡላቸው – “ ምነው! ምነው ጌታዬ! እኔና እርስዎ ኮ ወንድማማች ነን። እኔ በመንፈስ ከአጤ ምኒልክ ተወልጃለሁ (አበልጅ) ስለዚህ እርስዎና እኔ ወንድማማች ነን። የእኔን ልጅ ሊያገቡ አይችሉም። ( አንዳንድ የወለጋ አረጋውያን በዚህ ላይ ሲጨምሩ ሰምቻለሁ። ተጨማሪው ቃል “ሲሆን ባል ሲመጣለት አባት ሆነው የሚለመኑ፣ ቆመው የሚድሩ መሆን ይገባዎታል”)
የደጃዝማች አባ ጅፋር አባ ጆብር (የከፋው ገዥ) ዘመድ የሆነ አንድ ሰው ዘወትር ይሹሙኝ እያለ ደጅ ይጠናቸው ነበር ይባላል። እንዲያውም አንድ ቀን እጅግ አምርሮ “ለመሆኑ እነዚህ ለሹመት ያበቁአቸው ሰዎች ከእኔ ይቀርቡዎታልን? ለእኔ አንድ የሹመት ቦታ አጥተው ነው?” ይላቸዋል።

አባ ጅፋር በተለመደው ስል አነጋገራቸው “የሕዝብ አደራን በተመለከተ ምኒልክ እጄን ይዞ ነው የነገረኝ። ያ ባይሆን ኖሮ እኔ እዚህ አልገኝም ነበር። ምኒልክ እጁን ይዞ “ሹመት የሕዝብ ነው- ሹመት ሺህ ሞት ነው” ብሎናል። ወንድሜ! ወደ ሥልጣን የገቡት እንዴት በነፃነት እንውጣ እያሉ ይጨነቃሉ። ይህንን የማያውቁ ደግሞ እየዘለሉ መግባት ይመኛሉ። እንድታውቅልኝ የምመኘው ከዓለም መንግስታት እኩል ያደረገን ምኒልክ አደራ ከባድ መሆኑን ነው።”
በነገራችን ላይ አጤ ምኒልክ ዘወትር ምሳና ራት ሲበሉ አብረዋቸው ማዕድ የሚቀርቡ (ሁል ጊዜ) ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ፣ ደጃዝማች ወልደሚካኤል ጉዲሳ (የአጤ ኅይለሥላሴ አያት)፣ ፊታውራሪ ቱሉ፣ አፈ ንጉሥ በዳኔና ብላታ አቲከም ነበሩ።

በአንድ ነጥብ እንለያይ። አጤ ምኒልክ በአንድነት አሰባሳቢነትና ተበታትና የቆየች አገራቸውን ወደ አንድ ኅብረት በማምጣት ረገድ የየአካባቢው መሪዎችን ትብብር በግድን በውድም ተቀዳጅተዋል። ስለዚህም በወለጋ ደጃዝማች ገብረ እግዚአብሔር፣ በከፋ ደጃዝማች አባጅፋር፣ በወላይታ ካዎ ጦና ጋጋ አካባቢያቸውን ይዘው፣ የውስጥ አስተዳደራቸውን አደራጅተው ሕዝቡን ይመሩ ነበር። ይሁንና በአርሲ በኩል ለጊዜው ሕዝብ የሚቀበለው ጐላ ያለ ተወላጅ በመታጣቱ አጐታቸው ራስ ዳርጌ ተመደቡ። ራስ ዳርጌ ደግሞ እጅግ ሃይማኖተኛ፣ ሕዝቡን በርኅራኄ የሚመለከቱ የአባትነት ተቀባይነት የነበራቸው ስለሆኑ አንዳች ዓይነት ግፍ ለመፈጸም ባሕርያቸው የማይፈቅድላቸው ሰው ነበሩ። እንግዲህ “አጤ ምኒልክ ጡት አስቆረጡ” የሚባለው አነጋገር አርሲ ውስጥ መሆኑ ነው። ማንም እንደሚገምተው ጡት የመቁረጥ የአረመኔ ተግባር የአማራ ባሕርይም የክርስቲያን ሕዝብም ተግባር አይደለም። በአንጻሩ እነ አባ ባሕርይና ሌሎችም ሥፍር ቁጥር የሌላቸው የታሪክ ጸሐፊዎችም ለአካለ መጠን የደረሰ አንድ ኦሮሞ ጐልማሳ ከማግባቱ በፊት ብልት እስከ መስለብ፣ ጡት እስከ መቁረጥ የደረሰ “ጀብድ” መቁጠር መቻል አለበት፥ ይሉናል። ይኸም የትናንት ታሪክ ነው።

ለማንኛውም ተረት እየፈጠሩ ታሪክ፣ ድርሳን እየጻፉ በሕዝብ ዴሞክራሲ ስም ወደ ኋላ እየሄዱ የአገር ጊዜና ዕድሜ ከማባከን ይልቅ ጥላቻን ቀብረን፣ ፍቅርንና አንድነትን አንግበን ሰላም የተጠማችውን አገር ወደ ሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ማሸጋገር አይበጅም ኖሮአል? ዓለም እየታዘበን አይደለምን? ምን ይሁን ነው የምንለው?
በሕብረተሰብ ትክክለኛ አመራር ባሕርይ መንጸባረቅ ያለበት አንድ ክስተት “የነገው ከዛሬው” የተሻለ፣ ብሩሕ፣ አሰባሳቢ፣ እኩልነት የዳበረበት፣ ነፃነት የከበረበት መሆን አለበት። ያለፈው ጓዝና ጉዝጓዝ እንደ ጸሐይ ማብራት የሚገባውን “ነገ”ን በጨለማማ ገጽታው ሊያደበዝዘው አይገባም። ከትናንትና ከዛሬው ይልቅ “በነገው” ተስፋና አለኝታ መጣል ይገባናል። እንዲያም ቢባል ከትናንቱ ብሔራዊ ውርስና ቅርስ -ከትናንቱ የእድገትና የአንድነት መሠረት መካከል- ምኑም ማናምኑም በዛሬና በነገው ቀጣይ ታሪካችን ውስጥ ሥፍራ ሊኖረው አይገባም አይባልም። ታሪካችንም ሆነ የነገው “ጸጋችን” ምንም ዓይነት ተቀባይነት አይኖረውም አይባል። አያቱንና አባቱን የማያውቅ ትውልድ በፈንታው ለነገው ትውልድ አባትነትና አያትነት አይሰማውም። አዎን የምንኰራባቸው አባቶችና እናቶች አያቶችና ቅም አያቶች ያሉንን ያህል አሳፋሪዎች፣ ፈሪዎችና ደካሞች፣ መልቲዎችና ሰነፎች የሆኑ ዜጐችም ነበሩብን። አሉብንም።

እነዚህን ማወቁ-ታሪካችንን ጠንቅቀን መረዳቱ፣ ጀግንነትን ለማደስና ከቶውንም ያንን አዳብረን የዓለም “ጨው” እስከምንባል ድረስ ለመጓዝ ዓለማቀፋዊነት መሠረት ይሆነናል። አፍሪካውያን ብቻ ሳይሆን፣ ጥቁር ዓለምንም ብቻ ሳይሆን- የዓለምን ነፃነት ወዳጅና አክባሪ ሕዝቦች ሁሉ የሚያደንቁት “ምኒልክ” ከዚች አገር የጐን አጥንት የተከፈለ ነው። አንድን አገር ታላቅና ገናና፣ የተከበረችና የታፈረች የሚያደርጉአት ሕዝብዋ ሲሆኑ ለዚያ ሁሉ ታሪካዊ ሥፍራ ተቀዳጅነት የሚያስፈልጉ መሪዎች ናቸው። ኢትዮጵያ ውስጥ በመሪነት የተነሡትን ልዩ ልዩ ነገሥታትና የዛሬዎችንም አምላክ ለቅጣት የሰጠንን ጨምሮ- ለኢትዮጵያ አንዳች ክብር ያመጣውን ዋነኛ ሰው ለማግኘት ብዙ ማሰስ አስፈላጊ አይደለም። የዶክተር ሥርግው ሀብለ ሥላሴን “አጤ ምኒልክ” ማንበብ የአሰሳው ፍጻሜ ሊሆን ይችላል። ደራሲው በዚህ መጽሐፍ ከሳባ ንግስት አንስቶ እስከ ቀዳማዊ ኅይለሥላሴ ድረስ ይዘልቃል። ለዚህ አገር ታዋቂነት- ይልቁንም ዳር ድንበርዋንና ነፃነትዋን በማስከበር ረገድ ድንቅ አስተዋጽዖ ያደረጉ፣ በመንፈሳዊና ቁሳዊ ሥልጣኔ ታስደመሙ መሪዎችን ታሪክ ለላንቲካ ያቀርባል። ከሙሉው- ከዚያ ሁሉ ጀግናም ሆነ ሰነፍ መሪ መሐል አንድ ሰው ነጥሮ ይወጣል። በፀረ አንድነት ኅይልነት ጸንቶ ያለው ወያኔ ይንጨርጨር እንጂ- ወያኔና ሻዕቢያ የፈጠሩአቸው ትንንሽ ጩዋሒዎች ይንጨርጨሩ እንጂ ሰውዬው ወጣቱ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን “ጥቁሩ ሰው” የሚለው ነው።

ይቺ አገር በነፃነት የተፀነሱ፣ በነፃነት ያደጉና ድሀም ቢሆኑ በነፃነት የሚራመዱ ዜጐች እናት ናት። ያቺ አገርና ሕዝብዋ ከምን ጊዜውም በላይ ያልተጠናቀቀ ብሔራዊ ዕዳ፣ ለትውልዶች የሚጠቅም ቅርስ ለማቆየት በጥድፊያ ላይ ያሉ ወገኖች እናት ናት። እዚህ መሬት ማሕፀን ውስጥ የተከበሩ ጀግኖች ተኝተዋል። በዚች ዛሬ የታሪክ መጫወቻ በሆነች አገር ማኅፀን ውስጥ ታላላቅ ጀብዱ ፈፅመው ያንቀላፉ፣ በልዩ ልዩ ሙያና በፍልስፍናም ጭምር ልቀው ያላቁን ታላላቅ ነፍሳት የእናት አገራቸው እቅፍ ሞቆአቸው ተኝተዋል። ዓምደ ጽዮን፣ ያሬድ፣ በካፋ፣ ቴዎድሮስ፣ ዮሐንስ፣ ምኒልክ፣ ሀብተ ጊዮርጊስ፣ አሉላ፣ አብዲሳ አጋ፣ በላይ ዘለቀ፣…የተኙባትና እረፍት ላይ ስላሉም መሬቲቱ በጥንቃቄ መረገጥ ያለባት ናት። እነሱን ያህል ለመሥራት ያልቻልን ሰነፎች እንደ መሆናችን ቆምብለን ራሳችንን መርገምም የሚገባን ነን። ይኽ ሁሉ የወያኔ ልዑካን ጫጫታ አያሳፍርም? ይኸ ድምፅ ከየት መጣ? ወሮበሎች አያሰኝንምን? ስድ አደግ ማለት- የእምነት ድህነት ማለት- የሕሊና ባዶነት ማለት- የአቋም ምስኪንነት ማለት ምን ማለት ነው? ይኸው በአደባባይ እየታየ ነው። (በዚህ ጉዳይ ላይ እመለስበታለሁ)

Viewing all 13695 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>