Quantcast
Channel: Amharic News & Opinion
Viewing all 13695 articles
Browse latest View live
↧

ኢሕአዴግ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችን ሊያስር መሆኑን ፍንጭ ሰጠ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ዛሬ ማለዳ በአዲስ አበባ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በመወጣት ድምጻቸውን ካሰሙ በኋላ የኢሕአዴግ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ሬድዋን ሁሴን ለመንግስት መገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ “ፓርቲው ህገ መንግስቱን በመጣስ በሃይማኖት እጁን መክተቱና በህግ የበላይነት አምናለሁ እያለ በፍርድ ቤት ጉዳያቸው የተያዘባቸው ሰዎች በሁካታ ይፈቱልን ማሰኘቱ ተጠያቂ ያደርገዋል” አሉ።

964382_10200726554220184_1320094080_oአቶ ሬድዋን በፍርድ ቤት ሽብርተኛ የተባሉ ሰዎችን ሰማያዊ ፓርቲ እንዲፈቱለት መጠየቁ አግባብ አይደለም ካሉ በኋላ “የሃይማኖት አክራሪነትን አጀንዳው አድርጎ ሲንቀሳቀስ የነበረው ሰማያዊ የፖለቲካ ፓርቲ ጸረ ህገ መንግስታዊ እንቅስቃሴው ዛሬ በጠራው ሰልፍ ተጋልጧል ብሎ ኢህአዴግ ያምናል።” በማለት የፓርቲው ሰዎችን ለማሰር ያለውን እቅድ ፍንጭ ሰጥቷል።

የኢሕአዴግ መንግስት በተለያዩ ጊዜያት በልምድ እንደታየው ግለሰቦችን ማሰር ሲፈልግ “ሕገመንግስቱን” እንደሚጠቅስ የሚያስታውሱት የፖለቲካ ተንታኞች ኢሕአዴግ ይህን “ሰማያዊ ያዘጋጀውን ሰላማዊ ሰልፍ ላልተፈለገ አላማ አውሎታል” ሲል መግለጹ እንደተለመደው ሰበብ ፈልጎ ለማሰር ያለውን እቅድ ያሳየ ነው ብለውታል።

አቶ ሬድዋን በመግለጫቸው “በሰልፉ በአብዛኛው የተንጸባረቀው የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ይፈቱ እየተባለ መስተጋባቱ፤ ፓርቲው ህገ መንግስቱን በመጣስ በሃይማኖት እጁን መክተቱና በህግ የበላይነት አምናለሁ እያለ በፍርድ ቤት ጉዳያቸው የተያዘባቸው ሰዎች በሁካታ ይፈቱልን ማሰኘቱ ተጠያቂ ያደርገዋል” ሲሉ በግልጽ መናገራቸውን የተመለከቱ የፖለቲካ ተንታኞች ስርዓቱ ይህን አይነት መግለጫ የሚሰጠው ከፍራቻ እንደሆነ ተናግረዋል።

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀ መንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት በበኩላቸው ለመንግስታዊ ሚዲያዎች ሰጡት በተባለው አስተያየት በሃይማኖት ውስጥ ችግር አለ እስከተባለ ድረስ እና የታሰሩ ሰዎች እስኪፈቱ ድረስ ፓርቲው ትግሉን ይቀጥላል ብለዋል። በዛሬው በሰልፉ በቅርቡ በቤንሻንጉል ክልል እንግልት የደረሰባቸው የአማራ ክልል አርሶ አደሮች አደሮች ጉዳይ ፣ በአሸባሪነት ተጠርጥረው የታሰሩ የፖለቲካ መሪዎችና የህዝበ ሙስሊሙ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት እንዲሁም የጋዜጠኝነት ሙያቸውን በአግባቡ በመወጣታቸው የተወነጀሉ ጋዜጠኞች ከእስር ይፈቱ የሚሉ ጥያቄዎች ተነስተዋል፡፡ በየትኛውም አካባቢ ተዘዋውረን የመኖር መብታችን ይከበርልን ፣ ህገ መንግስቱን የሚቃወሙ አፋኝ አዋጆች ይሰረዙልን ብለዋል ሰልፈኞቹ ሲሉ የመንግስት መገናኛ ብዙሃንም ዛሬ ጠዋትም ዘ-ሐበሻ መዘገቧ ይታወሳል።

↧

ወርሃ ግንቦት ሲታወስ! – (ኢሮብ መብት ተማጓች ማኅበር የበተነው ጽሑፍ)

$
0
0

irob ethiopia ከ1990 ዓ.ም ወዲህ ወርሃ ግንቦትን በተለይ ደግሞ ግንቦት 23 ደስታና ሀዘን በተቀላቀለው ስሜት ነው የምናስታውሰው። ሀዘን የሚሆንብን ሻዕቢያ እንደሚወረን እየታወቀ የኢትዮዽያ መንግሥት ምንም ዓይንት ዝግጅት ሳያደርግ በመወረራችን ዳር ድንበራችንን ለማስከበር ከፍተኛ የሆነ የሰውና የንብረት መስዋዕትንት በመክፈላችን፣ ወረራውን ተከትሎ በሻዓቢያ ታግተው የተወሰዱ መቶ-እጥፍ ወገኖቻችን እስከ ዛሬ የደረሱበት ሳይታወቅ ይኸው አስራ ሶስት ዓመታት ማስቆጠራችንና ከሁሉም በላይ ደግሞ ታግተው የተወሰዱ ዜጎችን በሚመለከት የኢህአዴግ አገዛዝ ምንም ዓይነት እርምጃ ባለመውሰዱ፤ ወራሪው የሻዓቢያ ሠራዊት ዳር ድንበራችንን መውረሩና ህዝባችንን ለሁለት ዓመት በባርንት ቀንበር ሥር ማቆየቱ አንሶ ሉዓላዊ የኢትዮጵያ ግዛቶችን ለድርድርና ለግልግል ዳኝነት በማቅረብ ለሻዓቢያ ፍላጎት እንድንንበረከክ በመደረጉ፤ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነትን ማስከበር በሚመለከት፡ በኢህአዴግ አገዛዝ ላይ እምነት እንድናጣ ስለሆን ሻዓቢያ በወረራ ይዟቸው የነበሩ የኢሮብ ህዝብ መኖሪያ አከባቢዎች ዛሬም የጦር ሰፈር በማድረግ በርካታ ወገኖቻችን ለልዩ ልዩ በሽታዎች መዳረግ፣ ለባህላችን ውድቀትና የበርካታ ወገኖቻችን ትዳር መፍረስ፣ እንዲሁም በአከባቢው የነበሩ ዛፎችና ደን፣ ሥሩ እየተነቀለ ለማገዶ እንጨት መዋል ወዘተ. እንጂ አከባቢያችን የልማት ማእከል ሲሆኑ ለማየት ያለመታደላችን፤ ናቸው።
በዚህ ሁሉ አሳዛኝ ሰቆቃና ቊጭት ማኸልም የምንጽናናባቸውና የምንኮራባቸው በዜጎቻችን የተፈጸሙ ጀግንነቶችና ቁምነገሮችም አሉ። ይኸውም፤ እናት ኢትዮጵያ ለሕይወቱ የማይሳሳ፤ ለነፃነቷና ለክብሯ ውድ ሕይወቱን የሚሰጥ ጀግና ህዝብ ያላት ሀገር መሆኗ ነው። እንደ ትናንቱ በሻዕቢያ የእብሪት ወረራ ወቅትም ውድ ልጆቿ ከአጽናፍ እስከ አጽናፍ ቀፎው እንደተነካ ንብ አንድ ላይ ሆ ብለው በመነሳት ለክብሯ ሲሉ ከፍተኛ መስዋእትነትን ከፍለዋልና እጅግ በጣም እናከብራቸዋለን። እነዚህ ሰማእታት የከፈሉት መስዋዕትነትም እኛ ብቻ ሳንሆን መጪ ትውልዶችም በኵራት የሚመለከቱትና የሚመኩበት ከመሆኑም በላይ ለዘለዓለም ሲዘክሩት የሚኖር ይሆናል። አመራሩ ቢክዳቹህም አገራዊ ግዳጃቹህን ተወጥታችኋልና እናከብራቹሀለን በናንተም እንኮራለን ልንላቸው እንወዳለን።
በሁለተኛ ደረጃ የኢህአዴግ አገዛዝ ህዝባችን ደም ገብሮ ወረራውን የቀለበሰ ማግስት የኢህአዴግ አመራር አልጀርስ ድረስ በመጓዝ ለአቶ ኢሳያስ እጅ ነስቶ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚያስደፍር ሰነድ በመፈራረም የግልግል ፍርድ ቤት እንዲቋቋም መፍቀዳቸው የሚታወስ ነው። በዚህ ውል መሠረት የሚከራከርላት ወኪል ያልነበራት ኢትዮጵያ ሄግ ላይ የተሰየመው “የግልግል ፍርድ ቤት” ሲፈርድባት ተመልክተናል። ሽንፈቱን እንደ ድል የቆጠሩት የኢህአዴግ መሪዎች ብይኑ የተሰጠበት ዕለት ከጠየቅነው በላይ ተፈርዶልናል ብሎ በመዋሸትና በለመዱት የማጭበርበር ተግባር ዜጎችን ለማታለል በመሞከር ህዝብ ደስታውን እንዲገልጽ ጥሪ ማቅረባቸውም የሚዘነጋ አይደለም። እዚህ ላይ ከጠየቅነው በላይ አግኝተናል ሲሉ የጠየቁት ከየት እስከ የት እንደነበረ ግልጽ አለመሆኑ ልብ ሊባል ይገባል። የኢሮብ ርእሰ ከተማ ከዓሊተና ወደ ዳውሃን የተዛወረበት ሁኔታን ግምት ውስጥ በማስገባት ካየነው “ከጠየቅነው በላይ አግኝተናል” የሚለው ሐረግ ምን ማለት ሊሆን እንደሚችል እያንዳንዱ አንባቢ የራሱ ድምዳሜ ላይ እንዲደርሰ መልሱን በባዶ ሙላ ልናልፈው መርጠናል።
ዋናው ቁምነገሩና እጅጉንም የኮራንበትና ቀጣይ ትውልዶችም እጅጉን በኵራት የሚያስታውሱት ታሪካዊ ትምህርት ያገኙበታል ብለንም የምናምነው ህዝባችን የኢህአዴግ መሪዎች ዳር ድንበርን የመስጠት ውዲት ቀድሞ በመገንዘቡ ሴራውን ለማክሸፍ ዝግጁ ሆኖ መጠበቁ ነው። የህወሓት/ኢህአዴግ መሪዎች ሄግ ላይ የገጠማቸው ድል እንበለው ሽንፈት (እንደየአተረጓጕማችን ሊለያይ ይችላል) እንደ ደረሰ ለጭፈራ ካነሳሱት ህዝብና ከነባራዊ ሀቁ ጋር መፋጠጥ ነበረባቸው። በመሆኑም፤ ስለደረሰው ሁኔታ ለማስረዳት ከህዝብ ጀርባ ደባ ለመፈጸም ሰፊ ውስጣዊ ውይይት በማካሄድ ስራ ተጠመዱ። በዚህም፤ ግዛታችንን ለሻዓቢያ አሳልፈው ለመስጠት የነበራቸው ዝግጁነት ተግባራዊ ማድረግ ስለፈለጉ ህዝብን የሚያግባቡበት ሌላ ዘዴ ስላጡ መልካም አማራጭ ሆኖ ያገኙት የደረሰውን ሽንፈት ለኤርትራ በተወሰኑት አከባቢዎች ነዋሪ ለሆነው ህዝብ በየቀበሌው እየለያዩ ለማስረዳት በመወሰን አገባብ የሌለውን የክህደት ሥራውን እንዲያከናውኑ ካድሬዎቻቸውን ማንቀሳቀስ ጀመሩ። ከፍተኛ ካድሬዎቻቸውም በሄግ ብይን መሠረት የምትኖሩበት መሬት ለኤርትራ እንዲሰጥ ስለተወሰነና ኒውዮርክ የሚገኘው የተባበሩት መንግሥታትም ሊቀጣን ስለሆነ እናንተ ትነሳላቹህ መሬቱም ለኤርትራ ይሰጣል በማለት ለማስፈራራትና ተጽእኖ ለመፍጠር ሙከራ አደረጉ። በዛን ወቅት ነበር የኢሮብ ህዝብ ሄግም ሆነ የተባበሩት መንግሥታት የምትሉዋቸው ለኤርትራ የሚሰጡት መሬት ካላቸው ይስጡዋቸው፤ ይህ ግን የኛ መሬት ነውና እንኳን መሬታችንን ተንከባልሎ ወደ ኤርትራ ግዛት የሚወድቅ ድንጋይ ቢኖር እንኳን የሚከፈለውን ከፍለን እንመልሳለን ነበር ያላቸው። ይህ ህዝባችን ለመብቱ መከበር የሰጠው የእምቢተኝነት መልስ እጅጉን የሚያኮራ ነው። በመሆኑም፤ ይህ የህዝብ እምቢተኝነት ሉዓላዊ የኢትዮጵያ ግዛት እስከ ዛሬ ሳይሸራረፍ እንዲቆይ አስገድዷልና እጅጉን አስደስቶናል።
ስለሆነም፤ ትውስታችን በቊጭትና በደስታ በተደበላለቀ ስሜት የሚገለጽ ነው ስንል እነዚህን ከላይ የጠቃቀስናቸውን ጭብጦችና ስሜቶች ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ነው። እዚህ ላይ አንድ ልብ ሊባል የሚገባ ቁምነገር መኖሩን አንባቢ እንዲገነዘበው እንፈልጋለን። ይኸውም፤ ለኤርትራ ሊሰጧቸው ባዘጋጁዋቸው አከባብዎች የሚኖሩ ህዝቦችን በተናጠል ከቦታው እንዲነሱ ሲያዋክቧቸው ለሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ የተገለጸ ነገር እንዳልነበረ ነው። በአቶ መለስ ዜናዊና በአቶ ሥዩም መስፍን በመገናኛ ብዙኃን ለኢትዮጵያ ህዝብ የተነገረው “የአሸንፈናል” የማጃጃል ሙከራ እንዳይከሽፍ በመስጋት ሀቁን ከኢትዮጵያ ህዝብ እንዲደበቅ የማድረግ ሙከራ እንደነበረ
መዘንጋት የለበትም። የኢሮብ ህዝብ እሺ ብሎ የህወሓት/ኢህዘዴግና የካድሬዎቹን ፍላጎት ተቀብሎ ቢሆን ኑሮ፤ ጉዳዩ እንዳለ ተሸፋፍኖ ይቀር እንደነበረ የሚያጠራጥር አይደለም። እነሱ ያሰቡት የኢትዮጵያ ህዝብ ሳያውቀው በሎህሳሳ መሬቱን ለኤርትራ በመስጠት የኢትዮጵያ ህዝብ ሳያውቀው ሸፋፍነው በደባ ሊያልፉት ነበር። የኢሮብ ህዝብ ግን እምብየው፤ ይህ የኛ መሬት ነው በማለት ለትውልዶች የሚተርፍ ኩራት አለበሱን። የህወሓት/ኢህአዴግ ፍላጎት ግቡን መትቶ ቢሆንና ህዝቡ እሺ ብሎ መሬቱን ለቆ ወጥቶላቸው ቢሆንና የኢትዮጵያ ህዝብ ጉዳዩን አጣርቶ ቢደርስበት፤ የህወሓት/ኢህአዴግ መሪዎች ያለ ምንም ሓፍረት “የኢሮብ ህዝብ በራሱ ፈቃድ ነው ቦታውን የለቀቀው። ባይሆን ኑሮ እኛ ግዛታችንን አሳልፈን አንሰጥም ነበር” ወይም ደግሞ “የኢትዮጵያ ህዝብ ዳር ድንበሩን ሳያውቀው ስለቆየ ነው እንጂ እንዲያውም የኛ ያልነበረ እነ ዓሊተናን አስመልሰናል” የሚል ራስን የመሸንገል አባዜ ይዘው ብቅ ሊሉ ይችሉ እንደነበር ሳይታለም የተፈታ ነው። ዛሬ ስለባድመ ስያወሩ ስለኢሮብ ግዙፍ መሬት ወደ ኤርትራ መካለል ማንሳት የማይፈልጉበት ምክንያትም ይህ ነው።
ስለዚህ የኢሮብ አባት እናቶች አኵርታቹሁናልና ምስጋና ይድረሳቹህ!
ይህንን እንደመንደርደርያ ካኖርን ዘንዳ፤ ግንቦት 23 ቀን 1990 ዓ.ም እሁድ ሌሊት የሻዓቢያ ሠራዊት ለመጀመሪያ ጊዜ የኢሮብን መሬት እንደወረረ ይታወቃል። የሻዓቢያ ወረራ ያተኵረው ዓይጋ ላይ ነበረ፣ዓላማውም ከኢሮብ መሬት ለጦር እቅድ ምቹ ከሆኑት አንደኛ የሆነውን የዓይጋ ከፍታዎችን በቁጥጥራቸው ሥር ማድረግ ነበር። ይሁን እንጂ ለኢሮብ ጅግኖች ምስጋን ይግባቸውና የሻዕቢያ እኩይ እቅድ በዛ ቀን አልተሳካም። በዚሁ ዕለት ንጋት ላይ መሬቱ መወረሩን የተገነዘበ የአከባቢዉ ህዝብ ከጠላት ትጥቅ እየነጠቀ በመዋጋት ወራሪውን ወደ መጣበት መለሰ። ስለዚህም ”ዕጡቃት-ሰንበት” የሚል ስያሜ አገኘ። በዚህ ምክንያት ግንቦት 23 ወይም በዚሁ ሳምነት ሌላ አብዛኛው የኢሮብ ህዝብ የተሰማማበት ቀን (24፣ 25…) ከዓይጋ ኮረብታዎች ጀምረው ከኢሮብ ዳርቻ በጣም እስክርቁ ድረስ ሻዓቢያን እያሳደዱ በመግረፍ ላይ የወደቁት ሊረሱ የማይገባ ጀግኖቻችን መታሰቢያ ቀን በየዓመቱ በዚሁ ሳምነት እንዲዘከርና እንዲከበር የኢሮብ መብት ተማጓች ማኅበር (ኢ.መ.ተ.ማ) ለኢሮብ ህዝብ ሃሳቡን ያቀርባል።
ዕለተ ሰንበት ግንቦት 23 ቀን 1990 ዓ.ም እብርተኛው የሻዓቢያ ሠራዊት የኢሮብን መሬት ለመቆጣጠር በታንኮችና በከባድ መሣርያ በመታጀብ የዓይጋ ኮረብታዎችን ለመቆጣጠር ዘመተ። በጊዜው በኢትዮጵያ መንግስት በኩል በቦታው ምንም የመከላከያ ኃይል ስላልነበረ፤ ሉዓላዊ የኢትዮዽያ መሬት የመከላከል ዕዳ በኢሮብ ህዝብ ጫንቃ ላይ ወደቀ። በመሆኑም በወቅቱ በኢሮብ ወረዳ ቀላልና ጊዜ ያለፈበት መሳሪያ የታጠቁ በጣት የሚቆጠሩ ምሊሻዎች ህዝባቸውን ከኋላቸው አስከትለው ሻዕቢያን ለመጋፈጥ ወደ ዓይጋ ከፍታዎች ተምዘገዘጉ። ምልሻዎቹ የኢሮብ ልማዳዊ የመልእክት ማስተላለፍ ዘዴን በመጠቀም የወረራውን ዜና ባጭር ጊዜ ውስጥ ህዝብ ጆሮ እንዲደርስ አደረጉ። ዜናውን የሰማ ህዝብም ቀፎው እንደተነካበት ንብ መጥረብያ ያለው መጥረብያውን፤ ገጀራ ያለውም ገጀራውን በማንሳት አገርን ለመከላከል ከየአከባቢው ወደ ዓይጋ ኮረብታዎች መትመም ጀመረ። ምልሻዎቹም ጋራ ሽንተረሩን አብጠርጥረው በሚያውቋቸው የዓይጋ ኮረብታዎችና የዘገብላ በረሃ ላይ የሻዓቢያን ሠራዊት በውግያ ያሽመደምዱት ጀመር። ለእርዳታ የመጣው ህዝብም የቆሰለና የተሰዋ የወገን ምልሻ ትጥቅ በማንሳት ብቻ ሳይሆን ከሻዓቢያ ወታደሮች ጋርም ጉሮሮ ለጉሮሮ እየተናነቀ ነጥቆ በመዋጋት ጦርነቱ ተጧጧፈ። እዚህ ላይ ጦርነቱ የተጀመረ ዕለት በጦርነቱ ጀመርያ ሰዓቶች የተፈጸመ የዕጡቓት-ሰንበት ቆራጥነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ታሪክ በሚገባ መዝግቦ ከትውልድ ወደ ትውልድ ማስተላለፍ ያለበት አንድ ቆራጥነታቸውን የሚመሰክር ገጠመኝን አስታውሰን እንለፍ። ይኸውም ፤ አንድ የተወሰነ ኃይል የያዘች የሻዓቢያ ቡድን በአንድ አከባቢ አድፍጣ ቆይታ አንድ ሁለት የኢሮብ ምልሽያዎችን ትከባለች በዚህ ጊዜ በጠላት የተከበቡ አርበኞች በሳሆ ቋንቋ “ታሃም ኒም ማኪክ ኖያ አዶሳይ ሳባዓየ” የሚል መልእክት ያስተላልፋሉ። ትርጉሙም “እነዚህ የኛ አይደሉምና እኛን ጨምራቹህ ምቷቸው” ማለት ነው። በዚህም፤ ዕጡቓት-ሰንበቶች ወገኖቻቸውን ለይተው በመተው ያ የጠላት ቡድንን እንዳለ እዛ አስቀርተውታል።
አሁን በውጊያው ማኸል ስለታዩ ዘርፈ-ብዙ ገጠመኞችን ማንሳት እዚሁ አቁመን ወደ ተነሳንበት የውጊያው አካሄድ እንመልሳቹህ! ይኸውም በውጊያው ያልጠበቀው ጥቃት የደረሰበት ሻዓቢያ የታጠቀውን መድፍና መትረየስን ማንጣጣት መጀመሩ ነው። ታንኮቹም የተሸከሙትን እሳት መትፋት ጀመሩ። ሆኖም እነዛ ምልሻዎችና በዛች ዕለተሰንበት የብረት ምንነት ያወቁ የዕጡቓት ሰንበት ተርቦች የሻዓቢያን ሠራዊት በታጠቁት ቀላል መሣሪያ ያጣድፉት ጀመር። በሰዓታት ጦርነት ሻዕቢያ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ቁስለኛና ሬሳውን መቊጠር ጀመረ። ያን ያህል ከባድ ጥቃት እየደረሰበት ያለው በጣት በሚቆጠሩ ምልሻዎችና የብረት ምንነትና ውጊያ ጠንቅቆ በማያውቅ ህዝብ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት ስላልነበረውም ሽሽቱን ተያያዘው። እነዛ የዕጡቓት ሰንበት ተርቦች ግን ሸሽቷል ብለው አልቆሙም። ሻዓቢያን እየተከታተሉ አጨዱት። ሻዓቢያም የቻለውን ያህል ሬሳና ቁስለኛውን እየጫነ እግሬ አውጭኝ ሽሽቱን ተያያዘው። የኢሮብ ተርቦችም ወደ ሰንዓፈ ከተማ እስኪቃረብ ድረስ እየተከተሉ አጠቁት። በዚህ አኳሀን ከሦሰት ቀናት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ የኢሮብ ህዝብ በትዕቢት ተወጥሮ የመጣው ሻዓቢያን አስተንፍሶ ሙትና ቁስለኛ በማድረግ እየተከታተለ ወደ መጣበት መለሰው። ይህንን ታምር የፈጸሙ ጀግኖች “ዕጡቓት ሰንበት” የእሁድ ታጣቂዎች የሚል የቅጽል ስያሜ ተሰጣቸው። ዕጡቓት ሰንበት የሚል ስያሜ ያገኙት ያለምክንያት አይደለም። ከነዚህ በዛች ወቅት ጦርነቱ ውስጥ ተሳትፈው የተሰዋ ወይም የቆሰለ ወገናቸውን ትጥቅ እያነሱ እንዲሁም ከወደቀውና ከሚሸሸው ጠላት መሣርያ እየነጠቁ በጥቂት ቀናት ጦርነት ወደ ተፈለገው ምዕራፍ ካደረሱት ውስጥ የሚበዛው ከዛች ዕለት በፊት ብረት የሚባል ነገር ይዘው የማያውቁ ነበሩ። በዛች ቅጽበት ግን በጦርነቱ ማኸል የብረት አያያዝ የሚያውቁት የማያውቁትን እንዴት እንደሚተኵስ እያሳዩዋቸው ነው ሻዓቢያን ያሽመደመዱት። በዛች ዕለተ ሰንበት ታጥቀው የሻዓቢያን ሠራዊት ገጥመው በማሸነፋቸው ነው ዕጡቓት ሰንበት የሚለውን ስያሜ ያገኙት። በዚህም ኢሮብን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን አኩርተዋልና እንኮራባቸዋለን።
ይህ በግንቦት መጨረሻ ሳምንት 1990 ዓ.ም. በዓይጋ ኮረብቶች የተካሄደው የመከላከል ጦርነት የሻዓቢያን ትዕቢት ያስተነፈሰና የኢሮብ ህዝብ ለዳር ድንበሩ ያለው ቀናኢነት በግልጽ ያስመሰከረ ከመሆኑም በላይ የየዕለቱ ውጊያ የሻዓቢያን ሽንፈት ያበስር ነበር። ሆኖም፤ ያ ድል እንዲሁ ዋጋ ሳያስከፍል የተገኘ አልነበረም። በዓይጋ ከፍታዎች የተንጠፈጠፈው ደም የወራሪ ጠላት ብቻ ሳይሆን የተርቦቹ የዕጡቓት ሰንበት የኢሮብ ጀግኖችንም ጭምር ነው። ጀግኖቻችን ከወራሪ ጠላት ጋር ጉሮሮ ለጉሮሮ ተናንቀው ወድቋል። እንደነሱ ዓይነት ጀግኖች ባይኖሩን ኖሮ ሻዓቢያ በትእቢት እንደተወጠረ መላዋን ኢሮብ ምንም ጥይት ሳይተኵስ የመቆጣጠር ህልም ይዞ እንደተነሳው ሊሳካለት በቻለ ነበር። ጀግኖቹ ግን መስዋእትነት በመክፈል የሻዓቢያን ህልም ለማክሸፍ በቁ። የመንግስት በቂ እርዳታ ታክሎበት ቢሆን ኖሮ ለሁለት ዓመታት በሻዕቢያ ሥር በባርነት ቀንበር መማቀቅ ይቅርና ሻዕቢያ ዳር ድንበራችን ሊደፍር የሚችልበት ዕድልም አይኖረውም ነበር። ያም ሆነ ይህ እነዚህን ጀግኖቻችንን ልናስታውአቸውና ታሪካቸውም ከትውልድ ትውልድ እየተወራረሰ ለዘላለም ሲታወስ እንዲኖር ሁላችንም በጋራ ታሪካቸውን ማደስ አለብን ብሎ ኢ.መ.ተ.ማ በጽኑ ያምናል። ስለሆነም፤ እነዛን ጀግኖች ለሀገራቸው ሉዓላዊነትና ዳር ድንብር መከበር የወደቁበት ቀንን በየዓመቱ ለመዘከር እንዲቻል የኢሮብ ጀግኖች ያ እኩይ ወረራ ካከሸፉባቸው ቀናት አንደኛውን በመምረጥ የነዚህ ጀግኖች የመታሰብያ ቀን እንዲሆን ማድረግ ለሁላችንም ክብር ሲሉ ለከፈሉት ውድ ዋጋ እውቅና መስጠት ተገቢም፤ አስፈላጊም በመሆኑ የኢሮብ ተወላጆች በያሉበት ሊያስቡበት ይገባል ብሎ ኢ.መ.ተ.ማ ያምናል ጥሪም ያቀርባል።
የሰማዕታቶቻንን ቀን “ዕጡቓት ሰንበት” ድል የመቱበት ቀን እንዲሆን የሚመረጠው ያለምክንያት አይደለም። በግንቦት መጨረሻ ሳምንት 1990 ዓ.ም የኢሮብ ህዝብ በዓይጋ ላይ ያሰመዘገበው ድል በኢትዮዽያ መንግስት ተጠብቆ ቢሆን ኑሮ ሻዕቢያ ራሱን ዳግም በማደራጀት የኢሮብ መሬትን እስከ ዓሊተና ድረስ አይዝም ነበር፣ ከዛ በኋላ የተከፈለው መስዋእትነት አይከፈልም ነበር፣ ከዛም አልፎ የኢትዮጵያ ግዛቶች በአልጀርስ ስምምነት ተሳበው ለኤርትራ አይሰጡም ነበር ብሎ ኢ.መ.ተ.ማ በጽኑ ስለሚያምን ነው። እንዳለመታደል ሆኖ ግን የኢትዮጵያ መንግሥት ሓላፊነቱን ለመወጣት ባለመቻሉ ተጨማሪ መስዋእትነትና የግዛት መነጠቅን ለማስተናገድ በቅተናል። ያም ሆኖ ለውጤቱ የኢትዮጵያ መንግሥት በሓላፊነት የሚጠየቅበት ጉዳይ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ለናት አገር ሲሉ የወደቁትን በወደቁበት ቀን እናስታውሳቸው።
መ.ኢ.ተ.ማ በዚህ አጭር መግለጫ የጦርነቱን ዝርዝር ታሪክ ለማስፈር የቃጣ አለመሆኑና ለወደፊት በጥልቀት የሚመለስበት መሆኑን እየገለጸ፤ ታሪኩ ታሪካችን በመሆኑና ተሰንዶ ለትውልዶች መተላለፍ አለበት ብሎ ስለሚያምን በዚህ የታሪክ ምዝገባ ውስጥ የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት የሚችል ሁሉ ሓላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪውን ያቀርባል።
ክብር ሕይወታቸውን ለከፈሉልን ጀግኖች!!
የመታሰብያው ቀን በአሸናፊነት በተወጡበት ዕለት ይዘከራል!!
ኢመ.ተ.ማ
ግንቦት 2005 ዓ.ም

↧
↧

የሙስና ክተት፤‎ ‎ከታምራት ላይኔ እስከ መላኩ ፈንታ

$
0
0

አቶ ታምራት ላይኔ

አቶ ታምራት ላይኔ

ብዙዎቹ ቱባ የመንግስት ባለስልጣናት ሙሰኞች መሆናቸው ይታወቃል ፡፡ ይቅርታ በፍርድ ቤት ቋንቋ ‹‹ ተጠርጣሪ ›› ፣ በሰልጣኝነት ቋንቋ ‹‹ ዕጩ ›› ለማለት ስነ ምግባሩ ያስገድደናል ፡፡ አማርኛው ይገጣጠም ከተባለ ተጠርጣሪ ወይም ዕጩ ሌቦች ሊባሉ ነው ፡፡ መቼም ለዚህ አባባል ትክክለኛነት የግድ የባንክ ደብተራቸውን መመልከት አይገባም ፡፡ ባለስልጣናቱ በ 4 እና 6 ሺህ ብር ደመወዛቸው ለፈረንጅ እና ለተቋማት ኪራይ የሚበቃ ግዙፍ ህንጻ በየስርጓጎጡ መገንባታቸውን ፣ ብር በየቀኑ እያጨዱ የሚያቀርቡላቸውን ሱቃቸውንና መኪናዎቻቸውን ፣ በራሳቸውም ሆነ በዘመዶቻቸው ከአዲስ አበባ እስከ ሁሉም ጫፎች ያሰባሰቡትን መሬት ማየት ይበቃል ፡፡
የእድል ጉዳይ ሆኖ ግን እጃቸው ለካቴና የሚበቃው የጥቂቶች ነው፡፡ ነገረ ስራቸውን ሲከታተል የሚቆየው ተዘራፊ ህዝብ የሚበሳጨውም የቅጣቱ መንስኤ ፍትሀዊ ይዘትን መሰረት ባለማድረጉ ነው ፡፡ ለበርካታ አመታት ተቆርቋሪ መስለው እንደሚዘርፉ እየታወቀ በሌብነታቸው ብቻ አይጠየቁም ፡፡ በአንዲት ጠማማ ቀን ሌብነቱ ላይ ፖለቲካ ወይም ያልተገባ ‹‹ ነገር ›› ሲጨምሩ ግን ‹‹ ባቡሩ ›› ወህኒ ቤት ያደርሳቸዋል ፡፡
መቼም ይህ ሀሳብ መላምት አይመስልም ፡፡ ምክንያቱም ፤
‹‹ የታምራት ላይኔ ጦር ግባ ተብለሃል ! ›› ሲባል ሰምተናል ፡፡
አቶ ታምራት ‹‹ እለፍ ተብለሃል ›› ሲባሉ የሚጠበቀውን የጀግንነት ፉከራና ቀረርቶ አላሰሙም ፡፡ ስኳር አብዝተው መላሳቸው በቅኔ ተደጋግሞ ሲነገራቸው ልምዳቸውን ተጠቅመው አሪፍ የመልስ ምት ይመልሳሉ ብሎ የሚጠብቀው ብዙ ነበር ፡፡ ለምሳሌ ያህል ‹‹ የኔ ስኳር መቃም ምን ይደንቃል ፣ ሸንኮራ አገዳውን የሚጨረግደው ሞልቶ ›› የሚል አይነት ፡፡ ሆኖም የማይጠበቀውን እንባ ነበር በፍርድ ቤትም ፣ ከእስር በኃላም በስብከት ግዜ ያንቆረቆሩት ፡፡ የፍርድ ቤቱ ምልልስ ሲበዛባቸው ግን በእሳቸው ፣ በልጃቸውና ባለቤታቸው ላይ የተፈጸመውን ደባ በለሆሳስም ቢሆን አስረድተዋል ፡፡
‹‹ የስዬ አብርሃ ሜካናይዝድ ቀጥል ተብለሃል ! ›› ሲባልም ተገርመናል ፡፡
አቶ ስዬ ግን ዝምታ ለበግም አልበጃት በሚል ሀሳብ ገና ከጠዋቱ ነበር ባለፉበት ችሎት ሁሉ ፉከራና ቀረርቶ የተጠቀሙት ፡፡
‹‹ ዘራፍ ! ስዬ አብርሃ !
የድል የጀግንነት ቀለሃ
ማነው ወንዱ ያለ ግብሩ ስም የሰጠው
ላም ባልዋለበት ኩበት የለቀመው ! ››
አቶ ስዬ ለተከሰሱበት አንድም የሙስና ጉዳይ እውቅና አልሰጡም ነበር ፡፡ ‹ እኔ የታሰርኩት በሌብነት ሳይሆን ከአቶ መለስ ጋር በነበረኝ የፖለቲካ ልዩነት ነው ›› ነበር ያሉት ፡፡ አንዳንድ ተረበኞች ግን ያ ሁሉ ተገዛ የተባለው ትላልቅ መኪና የህወሃት ነው ወይስ የኢፈርት ? ማለታቸው አልቀረም ፡፡
‹‹ የአባተ ኪሾ ሻለቃ እለፍ ተብለሃል ! ›› ሲባል ተደምመናል ፡፡
 መላኩ ፈንታ እኚህ ናቸው።

መላኩ ፈንታ እኚህ ናቸው።

ቀስ እያሉ እየጋሉ የመጡት አቶ አባተ አንድ ደፋር ሀሳብ ሰንዝረዋል ይባላል ፡፡ ‹ እኔ በሙስና የምጠየቅ ከሆነ እገሌ / እገሊትም መጠየቅ ይኖርበ / ባታል › የሚል ፡፡ ወሬው በአለ ተባለ ሃዲድ መጥቶ ጆሮአችን የደረሰ በመሆኑ መጠየቅ አለበት የተባለውን ከፍተኛ ባለስልጣን ስም አናነሳም ፡፡
እናም ይህን የመሰለው የክተት ጥሪ ቀላል አልነበረም ፡፡ አቶ ቢተው በላይን ጨምሮ ሌሎች የመንግስት ባለስልጣናትም ጥሪው ደርሷቸው የደንቡን አድርሰው ተመልሰዋል ፡፡ በርግጥ ሊጠሩ ከሚችሉ ‹‹ አዝማቾች ›› መካከል አንዳንዶቹ ከኑግ ጋር እንደተገኘ ሰሊጥ ላለመወቀጥ ፣ ወይም ምን ያለበት ምን አይችልም እንዲሉ… ብቻ በአንድም ሆነ በብዙ ምክንያቶች ከቻሉ በቦሌ ካልቻሉ በሞያሌ ወጥተዋል ፡፡ በዚህ መልኩ መውጣታቸው እንጂ ኢህአዴግ የብዙዎቹን ስም እየጠራ ብዙ ነጋሪት ለመጎሰም በበቃ ነበር ፡፡ በርግጥ ድርጅቱ ከነበሩበት ከፍተኛ ቦታ አውርዶ መሬት ዘጭ የሚያደርጋቸው የተለያየ ታርጋ በመስጠት ነው ፡፡ በችሎታ ማነስ፣ በእድሜ መግፋት፣ ታማኝነት በማጉደል፣ ኔትወርክ በመፍጠር የሚባሉት የተለመዱ ዓይነቶች ናቸው ፡፡
በእውነተኛ ጨዋታ ህዝብና መንግስት ላይ ተገቢ ያልሆነ ፋውል በመስራትም ይሁን ፣ በተለያዩ ጥቅማጥቅሞች አይናቸውን በታወሩ ዳኞች ግፍ ቀይ ካርድ በማየት እስር ቤት ተወርውረው የነበሩት ባለስልጣናት / ታምራት፣ ስዬ፣ አሰፋ፣ ቢተው፣ … / ቅጣታቸውን ጨርሰው ዛሬ በራሳቸው መስመር እየተጓዙ ናቸው ፡፡ በያሉበት ሆነው እንደ አዲስ የተነሳውን የመንግስት ጥሪ ወይም ‹‹ እለፍ ተብለሃል ! ›› ን እንደሚሰሙ አይጠረጠርም ፡፡ ጥሪውንም ሆነ ያሳለፉትን መሪር ቆይታ ሲያስታውሱ ቀረርቶና ፉከራ ሳይሆን አሳዛኝነት ያላትን የጦር ሜዳ መዝሙራቸውን ደጋግመው የሚያንጎራጉሩ ይመስለኛል
‹‹ እንዳያልፉት የለ ያ ሁሉ ታለፈ
ታጋይ የህዝብ ልጅ በደሙ በላቡ ታላቅ ታሪክ ጻፈ ››

በርግጥ የእስር ቤቱ ሰቆቃ ታልፏል ፡፡ ምን አዲስ ነገር ጻፉ ? የሚል ጥያቄ ግን በአሽሙረኞች ተያይዞ መነሳቱ አይቀርም ፡፡ ‹‹ ከፖለቲካ መሪነት ወደ ሃይማኖት ሰባኪነት ! ›› ይሉናል አቶ ታምራት ‹‹ ፈጣሪን ከመክዳት የፈጣሪ ታላቅነትን ወደ መቀበል ! ›› በማለት አስረግጠው ይነግሩናል ፡፡ ‹‹ ከሰው ገዳይነት ወደ ሰው ተንከባካቢነት ! ›› ቢሉ ማን ይከለክላቸዋል ፡፡ ‹‹ በሃይል ተማምኖና በደመ ነፍስ ተናግሮ ህዝብን ከማስቀየም በመጽሀፍ እያመኑ ፍቅርን ማካፈል ›› ቢሉ ከአንደበታቸው ማር ፈሰሰ አይባልም ? ፡፡ በርግጥም ጉዞው ከአንዱ ዋልታ ወደ ሌላኛው ጫፍ በመሆኑ አዲስ ነገር መሆኑ አያጠራጥርም ፡፡
‹‹ ከኢህአዴግነት ወደ ተቃዋሚነት ! ›› ይሉናል አቶ ስዬ በበኩላቸው ‹‹ ከአብዬታዊ ዴሞክራሲ ወደ ሊበራል ›› በማለትም የፕሮግራሙን መሰረታዊ ልዩነት ሊያብራሩ ይችላሉ ፡፡ ነገሩን ላጡዘው ብለው ካሰቡ ደግሞ ‹‹ ከጎጠኝነት ወደ ህብረ ብሄራዊነት … ከገንጣኝነት ወደ አስመላሽነት… ›› በማለት ምርጫ ሳይደርስ የእንካ ሰላንቲያ መድረክ እንዲከፈት ሊያደርጉ ይችላሉ ፡፡ ምናባቸውን ለማስፋትም የእውቀት ትጥቆችን በውጭ ሀገር እየሸማመቱ መሆኑን ቢጠቃቅሱ አዲሱ ሲቪያቸውን አደለቡ ማለት ነው ፡፡ ይሄ ሁሉ ሆኖ የአቶ ስዬ ለውጥ ከፖለቲካ ምህዋር ባለመውጣቱ መሰረታዊ ለውጥ አይደለም ብሎ ለመከራከር መንገድ ይከፍታል ፡፡ እንደውም አንዳንድ ወገኖች አዲስ ወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ወይስ አሮጌ ወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ የሚል ፈታኝ ጥያቄ ይወረውራሉ ፡፡ በሁለቱ ፓርቲዎች መካከል ያለውን ልዩነትና ህዝባዊ ጥቅም ፈትፍቶ ማስረዳት የሚችል ፖለቲከኛ ካለ ግን የጎዳናቸውን ‹‹ አዲስነት ›› ማስረዳት ይችላል ፡፡
ለማንኛውም የኢህአዴግ ባለስልጣናት መዝሙሯንና ጥሪዋን እንደ አንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ መመልከት ይኖርባቸዋል ፡፡ ምክንያቱም የተራ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ብዙዎቹ ለጥያቄ ትፈለጋለህ መባላቸው አይቀርም ፡፡ ከእስር በኃላ ደግሞ ‹‹ እንዳያልፉት የለ ! ›› የምትለውን መዝሙር ሊደጋግሟት ግድ ይላቸዋል ፡፡ ምነው ቢሉ – ለመጽናናት ፡፡
እናም ጥሪው ቀጥሏል …
‹‹ የመላኩ ፈንታ ብርጌድ እለፍ ተብለሃል ! ›› ተብሏል ሰሞኑን ፡፡
ይህ ጦር በምክትላቸው በአቶ ገ/ዋህድ ገ/ጊዮርጊስና ልማታዊ በነበሩ ቱጃር ነጋዴዎች የተዋቀረ በመሆኑ የክብደቱን ደረጃ ከፍ ያደርገዋል ፡፡ እንደውም አንዳንድ ነገረኞች በኪሳቸው መደለብ ‹ ቼልሲ › በቅርበታቸው ደግሞ ‹ ፋቲክ ያለበሱ አጋዚዎች › ለማለት እየዳዳቸው ይመስላል ፡፡ ይህ ዜና ከተነገረ በኃላ የተደናገጡ ፣ የተደመሙ ፣ የተደሰቱና እስካሁንም እየሆነ ነገር ባለው ጭፍግ ድራማ እየተዝናኑ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ከኤርትራ ህዝብ ብዛት በሶስት እጥፍ ይበልጣሉ ፡፡
አቶ መላኩ ‹‹ እለፍ ተብለሃል ! ›› ሲባሉ በምላሻቸው የማንን ስልት እንደሚከተሉ ናፋቂ ሁኔታ ፈጥሯል ፡፡ ክሱን አምነው ይቀበላሉ ወይስ በታኮነት ስለሚያገለግለው ፖለቲካና ሌሎች አዳዲስ ጉዳዮች ዘርዘር አድርገው ይነግሩን ይሆን ? አንዳንድ ሚዲያዎች እንደገለጹት በባህርዳሩ ስብሰባ ታክስ የማይከፍሉ በርካታ ‹ ልማታዊ › ካምፓኒዎች መኖራቸውን ጠንከር አድርገው ተችተው ነበር ፡፡ ይህ ማለት ደግሞ ሾርባው ውስጥ ነጭ ሽንኩርትን የሚወክለው ዝርፊያና ጥቁር አዝሙድን የመሰለው ‹‹ ነገር ›› ተደባልቀው ይገኛሉ ማለት ነው ፡፡
ጸረ ሙስና ኮሚሽን የአቶ መላኩን ብርጌድ አንድ ዓመት ከ 8 ወር በፈጀ ጥናት ነው ገቢ ያደረኳቸው ቢልም ኢኮኖሚስቱ አቶ መላኩም ለመንግስታቸው የማይታመን ገቢ መፍጠራቸውን ልብ ይሏል ፡፡ እንደው ለምሳሌ በሙግታቸው ፣
‹‹ ዘራፍ ! መላኩ !
ስራ ነው አምላኩ
አንድ እንጀራ ልኩ
ሳታውቁት አትንኩ … ›› ብለው ከተነሱ በተያዙበት ጉምሩክ ምን ሰርተው ቆዩ የሚለውን ጥያቄ መመለስ ሊገባን ነው ማለት ነው ፡፡ የኢትዮጽያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን በአዲስ መልክ እአአ በ2008 ሲቋቋም በቦታው የተሾሙት በአቶ መለስ ዜናዊ አማካኝነት ነበር ፡፡ መ/ቤቱን በአዲስ አደረጃጀትና አሰራር በአጭር ግዜ በማዋቀር ፣ የታክስ ከፋዩን ቁጥር በማብዛትና አዳዲስ የታክስ ስርዓቶችን ስራ ላይ በማዋል ባስገኙት ለውጥ ተጨብጭቦላቸዋል ፡፡ ሰውየው ቦታውን ከመያዛቸው በፊት የመንግስት ገቢ 19 ቢሊየን ብር ነበር ፡፡ በእሳቸው የስራ ዘመን ማለትም በ2011/12 የፌዴራል መንግስት ገቢ 71 ቢሊየን ብር መድረስ ችሏል ፡፡ አንዳንዶች የቅጣትና የማስገደድ ስርዓትን በመከተላቸው ያገኙት ውጤት ነው እያሉ ቢያሟቸውም የፈጠሩት ለውጥ ግን ትልቅ ሊባል የሚችል ነው ፡፡
የአቶ መላኩ ክስ ሌላ ጦስ ሊያስከትል ይችላል ብለው የሚያስቡ የህብረተሰብም ክፍሎችም ጥቂቶች አይደሉም ፡፡ ምክንያቱም የሃብት ስር በሆነው ቦታ ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሲጠቀሙ የነበሩ ባለስልጣናትና ትላልቅ ነጋዴዎች በርካታ በመሆናቸው አንዱ ሌላውን ወደ ጥቁሩ መረብ የማስገባቱ ስራ ሊቀጥል ይችላል በማለት ፡፡ በርግጥ የስነምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ ከ50 በላይ የሚሆኑ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ነጋዴዎችና ሌሎች ተጠርጣሪ ሰዎችን መያዙን የመግለጹ ጉዳይ እየተነሳ ያለውን ሀሳብ የሚያጠናክር ይመስላል ፡፡
የሰላም፣ ልማትና እድገት ጸር የሆነውን ሙስና በተደራጀ መልኩ መዋጋት ግድ ነው ፡፡ የሚያሳፍረው ግን ባለስልጣናት ለስርዓቱ ታማኝ እስከሆኑ ድረስ ሀገሪቷን ይጋጡ የሚለው ድሃ አስተሳሰብ ነው ፡፡ ብዙዎቹ መንግስትን የሚጠራጠሩትና አብረው ለመስራት ሙሉ ልብ የማይሰጡት ባለስልጣናትን እየቀጣ የሚገኘው በሚያደርሱት በደልና በንጹህ የሌብነት ተግባራቸው አለመሆኑ ነው ፡፡ ከዘራፊነታቸው ይልቅ የፖለቲካ አለመታመናቸው ነው ሚዛን ደፊ ተደርጎ የሚቆጠረው ፡፡
ከ 176 ሀገሮች የ113ኛ ደረጃ በያዘች ሀገር ሙስናን በርካሽ የፖለቲካ ጥቅም ማስታመም ቀስ በቀስ ሀገርን ለመግደል ምቹ ሁኔታ እየፈጠሩ የመጓዝ ያህል የሚያስቆጥር ነው ፡፡ ታዲያስ መጋዚን Global Financial Integrity የተባለ ድርጅትን ጠቅሶ እንደዘገበው ከ 2001 – 2010 ባለው ግዜ ውስጥ በኢትዮጽያ ባለስልጣናትና በተለያዩ ሰዎች ወደ ውጭ የወጣው ገንዘብ 16 . 5 ቢሊየን ዶላር ነው ፡፡ ይህ መረጃ ሊያሳዝነንም ሊያሳፍረንም ይገባል ፡፡ ይህ ሁሉ ሀገራዊ ሀብት ወደ ውጭ የወጣው በላይኞቹ ባለስልጣናት ቀጥተኛ ተሳትፎና የተዘዋወረ ድጋፍ ጭምር መሆኑ መታወቅ አለበት ፡፡
እንግዲህ አደኔን አጠናክሬ እቀጥላለሁ እያለ የሚፎክረው ጸረ ሙስና ኮሚሽን መረቡን በጣም እየተረተረ ባህሩ ውስጥ በጣለ ቁጥር አዞ አይደለም ሻርክን ሊያጠምድ ይችላል ፡፡ ጉዱ የሚፈላው ያኔ ይሆናል ፡፡ ወይ ከሻርኩ ጋር መጋፈጥ አለበት አሊያም መረቡን ለሻርኩ ጥሎ እግሬ አውጪኝ ይላል ፡፡ ይህን የመሰለ አጋጣሚ ከተፈጠረ እንደ ፉከራው በተግባርም ሩቅ ለመጓዝ የሚያስችል መተማመኛ አይገኝም ፡፡
ስለ Back Fire ወይም ተቃራኒ ውጤት ውስን ምሳሌዎችን ልወርውርና ጽሁፌን ልቋጭ ፡፡
. መንግስት አጋጣሚዎችን በመጠቀም ሙሰኞችን የሚሸከምበት ጫንቃ እንደሌለው ለህዝብ ያስረዳል ፡፡ የሙስናው ስር ሄዶ ሄዶ ጭንቅላት ላይ ከደረሰ ግን ክሱ እንዲለዝብ ወይም እንዲሰረዝ ይደረጋል – Back Fire – 1
. ጸረ ሙስና ኮሚሽን አንድ ሰሞን የጀመረው ዘመቻ እንደጋለ እንዲቀጥል ድጋፍ አድርጉልኝ በማለት ለህዝቡ ጥሪ ያቀርባል ፡፡ የጥቆማው ምንጭ ሄዶ ሄዶ ከትልቅ ባለስልጣናት እልፍኝ ዘው ሲል አብሮ መግባት ይከብዳል ፡፡ ውሻው … ፖሊሱ … ንጉስ አይከሰስ የሚለው ብሂሉ… ለቋጥኙ ዘብ ይቆማሉ ፡፡ ጸረ ሙስና በደከመ ትንፋሽ ‹ ጥርስ የሌለኝ አንበሳ ሆኛለሁ › ሲል ይሰማል – Back Fire – 2
. የአቶ መላኩ መ/ቤት ውስጥ ብዙ ሙሰኞች መኖራቸውን ህዝቡ ይጠቁም ነበር ፡፡ ይህን ሃሳብ በመያዝ ይመስላል ሪፖርተር በአንድ ወቅት ከሚ/ሩ ጋር ቆይታ አድርጎ ነበር ፡፡ ይህ አቤቱታ አውነት ነው ? ሲል ላቀረበው ጥያቄ የሰጡትን ምላሽ እንደወረደ አቅርቤዋለሁ
‹‹ I can not say that our employees do not have problems . For that reason we have put in place special administrative rules . We have applied these rules from hiring to firing . አቶ መላኩም Firing ተደርገዋል … an employee who is unethical and incompetent will have no excuse for coming back . አቶ መላኩም ይቅርታ የማግኘታቸው ጉዳይ የጠበበ ይመስላል … for instance, we have fired fifty employees so far and instituted criminal charges against some of them . አቶ መላኩም ቢያንስ ተጠርጣሪ ወንጀለኛ ተብለዋል … We have managed to have them sentenced up to ten years in prison . አቶ መላኩም በሙግታቸው ካልረቱ በስተቀር ጥቂት የማይባሉ ዓመታትን ወህኒ ቤት ያሳልፋሉ – Back Fire – 3
የተቃራኒው ውጤት / Back Fire / እየበዛ ከሄደስ ? ህዝቡ የነጋሪቱን ጥሪ በሚከተለው መልኩ ለመጎሰም ይገደዳል
‹‹ የኢህአዴግ ፓርቲ ግባ ተብለሃል ! ››

↧

ሸንጎ በአ.አ የተደረገውን ሰልፍ “በሺዎች የተጀመረው እንቅስቃሴ የሚሊዮኖች ይሆናል” አለ

$
0
0

shengo(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) በዛሬው እለት በሰማያዊ ፓርቲ ጠሪነትና በተለያዩ ድርጅቶች ተባባሪነት በአዲስ አበባ ለተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ያለውን አድናቆትና የትግል አጋርነት በድጋሜ እንደሚገልጽ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ። ድርጅቱ ለዘ-ሐበሻ በላከው መግለጫ “ይህ በሽዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ጎሳ፣ዕድሜ፣ጾታና እምነት ሳይነጥላቸው በአንድ ሆነው የሀገራችንን ህብር በሚያንጸባርቅና በታላቅ ሥነስርዓት የጋለ ስሜታቸውን በይፋ የገለጡበት ህዝባዊ ሠልፍ ፣ በሕዝባችን ላይ የተጫነው የፍርሀት ድባብ እየተሰበረ መምጣቱን የሚያመለከት ታላቅ እርምጃ ነው።” ብሎታል።
“ይህ እጅግ ብዙ ወጣቶችን ያሳተፈ፣ ስሜት ቀስቃሽና ታላቅ ወኔ የታየበት የህዝብ ቁጣ፣ ህዝባችን ለዓመታት የተጫነበትን የግፍ ቀንበር ሊሸከም የሚችልበት ጀርባ እንደሌለው በግልጥ ያሳየበት ቀን ነው።” የሚለው የሸንጎ መግለጫ “ይህ ስላማዊ ሰልፍ የኢትዮጵያ ህዝብ መሰረታዊ መብቶች ሙሉ በሙሉ እንዲከበር፣ ጎሳ ተኮር የህዝብ ማፈናቀል እንዲያበቃ፣ የኑሮ ውድነት እንዲወገድ፣ በፖለቲካ ጉዳይ በእስር ላይ ያሉ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎችና ነጻ ጋዜጠኞች በአስቸኳይ እንዲፈቱ፣ የመደራጀት መብት ሙሉ በሙሉ እንዲከበር፣ በየሃይማኖቶች የውስጥ ጉዳይ የመንግሥት ጣልቃ ገብነት እንዲቆምና የታሰሩት የሙስሊሙ ተወካዮች እንዲፈቱ በመጠየቅ የሀገሪቱን ሕዝብ ብሶት በሚገባ አንፀባርቋል።” ካለ በኋላ “የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) እነዚህና ሌሎች መሰረታዊ የመብት ጥያቄዎች ባሰቸኳይ እንዲመለሱና ከዚህም አልፎ የአምባገነንነትና የጎጠኛ ስርዓት አክትሞ ህዝብ በምርጫ የራሱን መንግሥት የመመስረት መብቱ እንዲረጋገጥ ለማስቻል ከተለያዩ ኢትዮጵያዊ ሀይሎች ጋር ተባብሮ ትግሉን እንደሚቀጥል አሁንም ያረጋግጣል።” ሲል አቋሙን አስታውቋል።
“በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን፣ ከሀገር ውጭም፣ ዓለምአቀፉ ህብረተሰብ፣ ያለውን ሁኔታ ይበልጥ ተረድቶ፣ በመፍትሄ ፍለጋው አንጻር፣ አወንታዊ ሚና እንዲጫወት፣ ሸንጎው የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን አጠናክሮ ይቀጥላል።” ሲል አቋሙን ያጠናከረው ሸንጎ “የተባበረ የህዝብ ትግልን ሊመክት የሚችል ምንም ሀይል የለምና፣ መብታችንን ለማሰከበር ትግላችን ተጠናክሮ ይቀጥል። ዛሬ የተካሄደው ሕዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ፣ ለተከታታይ ሕዝባዊ ንቅናቄዎች በር ከፋች እንጂ መደምደሚያ እንደማይሆን ሸንጎው ይተማመናል።” ብሏል።
ሸንጎው በመግለጫው ማጠናቀቂያ ላይም “ሰላማዊው ትግሉ እንዳይቀጥል የሕወሓት/ኢሕዴግ አሸባሪ አገዛዝ ብዙ ጥረት እንደሚያደርግና ደፍረው በወጡትና ባዘጋጁት ላይም ስበብ እየፈጠረ የሽብር ክንዱን ከመሰንዘር ስለማይመለስ ከወዲሁ ነቅቶ መጠበቅና በጋራ መከላከል የሚቻልበት ዘዴ እንዲፈጠር፣ ተደናግጦና በርግጎም የተጀመረው የነጻነት ጉዞ እንዳይከሽፍና እንዳይቆም ሸንጎ ያሳስባል። ሁሉም ዜጋ የተቻለውን ሁሉ እንዲያደርግም ጥሪ ያደርጋል።” ብሏል።

↧

በስደት የሚገኘው ሲኖዶስ በገለልተኝነት ያሉ አብያተ ክርስቲያናት እንዲቀላቀሉት ጥሪውን አቀረበ (መግለጫውን ይዘናል)

$
0
0

Holy Sinod Ethiopia
(ዘ-ሐበሻ) በዳላስ ቴክሳስ ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ጉባኤውን አድርጎ ያጠናቀቀው በብጹዕ ወ ቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ የሚመራው ሕጋዊው ሲኖዶስ ባወጣው ባለ 8 ነጥብ መግለጫው በገለልተኝነት ያሉ አብያተ ክርስቲያናት የቅዱስ ሲኖዶሱን ጥሪ በአንድነት ተቀበለው፤ ለትውልድ የምትተላለፍ አንዲት፣ ቅድስት፣ ሐዋርያዊትና ኩላዊት ቤተክርስቲያንን የሚጠቅም፤ እንዲሁም አገርንና ወገንን የሚጠቅምና የሚያኮራ ሥራ ለመሥራት ቅዱስ ሲኖዶሱን እንዲቀላቀሉ ጥሪውን አቀረበ።

ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

↧
↧

የፖለቲካ ኃይል ሽግሽግ ትግል – ቁጥር 01

$
0
0

ግርማ ሞገስ (girmamoges1@gmail.com)
ሰኞ ግንቦት 26 ቀን 2005 ዓ.ም. (Monday, June 3, 2013)

(ግርማ ሞገስ)

(ግርማ ሞገስ)

ሰማያዊ ፓርቲ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ እሁድ ግንቦት 25 ቀን 2005 ካለምንም እንከን ተጠናቀቀ። አምባገነን መለስ ዜናዊ ከግንቦት 8 ቀን 1997 ዓመተ ምህረት ጀምሮ በሽብርተኛ ህጎቹ እና ተግባሮቹ የገነባው የፍርሃት ፖለቲካ ህንጻ ፈረሰ። በዚኹ እለት የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ኃይሎች ማዕከል በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ መስኮች መፈጸም አለባቸው የሚላቸውን እርማቶች በንግግሮች እና በመፈክሮች በአደባባይ አስታወቀ። እነሱም ከሞላ ጎደል እንደሚከተለው ሊቀርቡ ይችላሉ፥ “መብት መጠየቅ ወንጀል አይደለም፣ ነፃነት እንሻለን፤ ፍትህ እንሻለን፤ አንለያይም፤ የህሊና፣ የሃይማኖት እና ሌሎች ፖለቲከኛ እስረኞች ይፈቱ፤ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ጥያቄዎች ይመለሱ፤ በአገራችን ሰላም አጣን፤ ልማት እያሉ ሙስና ሰሩ፤ በኑሮ ውድነት የጎበጠው ትከሻችን እረፍት ይሻል፤ ህዝብ ማፈናቀል የዘር ማጥራት ወንጀል ነው፤ ህገ-መንግስት ይከበር፤ የሽብር፣ የነፃ ፕሬስ እና የሲቪክ ድርጅቶች ህጎች ይከለሱ ወይንም ይሰረዙ፤ ኢቲቪ ሌባ፣ ኢቲቪ ውሸት፣ ኢቲቪ ሽብር” የሚሉት ነበሩ።
979885_10200726530979603_470373367_o
መንግስት ለተጠየቀው ጥያቄዎች አዎንታዊ መልሶች መስጠት ይጠበቅበታል። ሁሉም ነገር በእጁ እና በደጁ ስለሆነ አዎንታዊ መልስ ለመስጠት የሚያስቸግረው ምንም ነገር የለም። ዛሬ ብድግ ብሎ “እስከ ዛሬ ድረስ ለፈጸምኩት ጭቆና ይቅርታ ይደረግልኝ። የዜጎችን ነፃነት ከዛሬ ጀምሮ አከብራለሁ። እስረኞችን ነገ እፈታለሁ። በኢትዮጵያ በነፃ ፕሬስ ላይ የጫንኩትን ጭቆና ከዛሬ ጀምሮ አንስቻለሁ። ኢ.ቲቪ እና አዲስ ዘመን ጋዜጣ በአንድ ወር ውስጥ ከመንግስት ፖለቲካ ነፃ ሆነው እንዲደራጁ አደርጋለሁ። ህዝብ ማፈናቀል በኢትዮጵያ ዳግም አልፈጽምም። የተፈናቀሉትም ካሳ ተከፍሏቸው እና ህጋዊ ዋስትና ተስጥቷቸው ወደቀድሞ ኑሮዋቸው እንዲመለሱ በአንድ ወር ውስጥ እፈጽማለሁ። አፈናቃዮችን ፍርድ ቤት አቀርባለሁ። ሁሉም በሙስና የሚታሙ ባለስልጣኖች አዜብ መስፍን ሳትቀር ክትትል እንዲደርግባቸው አደርጋለሁ። አንድን ሙሰኛ ከሌላ ሙሰኛ ሳላበላልጥ ሁሉም ሙሰኞች ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ አደርጋለሁ። በዚህም በዚያም እያልኩ በየውሩ ከደሞዛችሁ እምቆርጠውን ከዚህ ወር ጀምሮ በማቆም የኑሮ ውድነት ያጎበጠው ትከሻችሁ እንዲያገግም አደርጋለሁ። ህገ-መንግስት አከብራለሁ።”

በስልጣን ላይ ያለው አምባገነን መንግስት ከፍ ብለው ከተዘረዘሩት ውስጥ ከፊሉን ያህል በማድረግ እንኳን ከአምባገነንነት ወደ ተሻለ የፖለቲካ ኃይል ሽግሽግ (Political Power Shift) ሊያደርግ ይችላል። ይኽን በማድረግ የነፃነት እና የዲሞክራሲ አድማሶች እንዲሰፋ ያደርጋል። በምላሹ የህዝብ ድጋፍ ሊያገኝ ይችላል። የህዝብ ድጋፍ ማግኘት ማለት ደግሞ የፖለቲካ ድጋፍ ማገኘት ማለት ነው። እነዚህን እርምጃዎች በመውሰድ መንግስት ከተቃዋሚ ዲሞክራሲ ኃይሎች ጋር የፖለቲካ ስልጣን ሽግሽግ ያደርጋል ማለት ነው። ይኽን በማድረግ መንግስት የሚያጣው ነገር ቢኖር አምባገነንነትን ብቻ ነው። ምርጫው የእርሱ ነው። በታሪክ ግን አምባገነኖች ካልተገደዱ በስተቀር በፈቃዳቸው የፖለቲካ ስልጣን ሽግሽግ ያደረጉበት ጊዜ ስለመኖሩ ተጽፎ ያየሁት መረጃ የለኝም።

መንግስት ከፍ ብለው ለተዘረዘሩት ጥያቄዎች አዎንታዊ ምላሽ ካልሰጠ በአምባገነንነት መቀጠል መርጧል ማለት ነው። እሱም ቢሆን ችግር አይሆንም ለዲሞክራሲ ሰራዊት። የዲሞክራሲ ሰራዊት በሰላማዊ ትግሉ የዲሞክራሲ ማዕከሉን መሰረት እና አቅም ያጎለምሳል። ይኽን ማድረግ እንደሚቻል ታሪክ ትመሰክራለች። ይሁን እንጂ መንግስት አምባገነንነትን ከመረጠ ስትራተጂካዊ የፖለቲካ ስህተት መፈጸሙን ልብ ሊል ይገባል። ነፃ ምክር ነው!

ሲጠቃለል፥ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓመተ ምህረት በኢትዮጵያ ሁለት የፖለቲካ ማዕከሎች እንዳሉ እና በመካከላቸው ሰላማዊ ትግል እንደሚካሄድ አሳይታናለች። የዲሞክራሲ ኃይሎች የሚያደርጉት የፖለቲካ ኃይል ሽግሽግ (Political Power Shift) ትግል በስልጣን ላይ ከሚገኘው አምባገነን መንግስት አንፃር የፖለቲካ መሰረታቸውን እና አቅማቸውን ሳያቋርጥ ሽቅብ ማሳደግ አለበት። በውጤቱም የፖለቲካ ኃይል ደረጃቸው ቀስ በቀስ ከበታችነት ወደ አቻነት ከዚያም ወደ በላይነት ደረጃ ይጓዛል። የበላይነት ደረጃ መያዝ ማለት የኢትዮጵያን ህዝብ የመንግስት ስልጣን ባለቤት ማድረግ ማለት ነው። መንገዱ ደግሞ ምርጫ ወይንም ግብጽ ሊሆን ይችላል።

የፖለቲካ ኃይል ሽግሽግ ትግል ሌላ ቁልፍ የሰላማዊ ትግል ጽንሰ አሳብ ነው። አፈጻጸሙን በስፋት ማወቅ ጠቃሚ ነው የተሳካ ሰላማዊ ትግል ለማድረግ። የሽግሽግ ትግልንም ከበካዮች (Contaminants) መጠበቅ ያስፈልጋል።

Golgul/ጎልጉል በፌስ ቡካችሁም (https://www.facebook.com/goolgule) ላይ በማቅረባችሁ ምስጋናዬ ከፍ ያለ ነው። አሁንም ቀጥሉበት። ዘሃበሻም እንደዚሁ። የረጅም ጊዜ የሰላማዊ ትግል ጉዋደኛዬ አብርሃ (ኢትዮሚዲያ) ምስጋናዬን ተቀበለኝ። እንዲሁም ቋጠሮ፣ ኢትዮጵያ ዛሬ፣ አቡጊዳ፣ አሲምባ፣ ECADFORM እና ያላየሁዋችሁ ድረገጾች በሙሉ ለምትለግሱኝ ትብብር ምስጋናዬ ገደብ የለውም። ትግሉ የጋራ ቢሆንም!

↧

ዶ/ር በያን አሶባ ለግልጽ ደብዳቤዬ ለሰጡት ምላሽ መልስ – ከዶ/ር ፍቅሬ ቶለሳ

$
0
0

ዶ/ር ፍቅሬ ቶለሳ

ዶ/ር ፍቅሬ ቶለሳ

ውድ ዶ/ር በያን አሶባ

በቅርቡ ለጻፍኩልዎት ግልጽ ደብዳቤ የከተቡልኝን አጻፋ በኢትዮሚዲያ ድህረ ገጽ አስፍረው ዐየሁት። የደብዳቤዎን ርዕስ እንደአጤንኩት “እኚህ ሰው በጣም ትልቅ ናቸው፤ ቢዘገዩም መልስ ሰጡኝ። እንግዲህ ስለሕዝባችን እጣ ፈንታ በቁምነገር ሊያነጋግሩኝ ነው” በማለት አክብሬዎት ነበር። ወደ ውስጥ ዘልቄ ሳስተውለው ግን ለካስ እርስዎ የሕዝባችንን ሕይወት የሚነካውን አንገብጋቢ ቁምነገር ወደ ጎን ትተው የእርስዎን እና የእኔን ስሞች አንስተው እየሰነጣጠቁ ኖሯል የከተቡልኝ።

ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

↧

Hiber Redio: ግብጽ እውን በአባይ ጉዳይ በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት ታነሳለች? (ወቅታዊ ዘገባ)

$
0
0

የህብር ሬዲዮ ዕሁድ ግንቦት 25 ቀን 2005 ፕሮግራም

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

<<የቬጋሱን ክለብ ችግር የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈጻሚውም ቦርዱም ያውቀዋል።ለምን አልፈቱትም አላውቅም። እኔ ተጫዋች ሲበደል አልወድም ለምን እስካሁን ውሳኔ አልተሰጠም ብላችሁ እንዳትጠይቁኝ።…ይሔ ችግር የፌዴሬሽናችንን ህልውና ሳያጠፋ ቦርዱ ውሳኔ እንዲሰጥ እጠይቃለሁ>> አቶ ተካበ ዘውዴ
- የፌዴሬሽኑ የውድድር አስተባባሪና የቀድሞ ብሔራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ
- በቬጋስ ከስራ ማቆም አድማ እስከ እስር የኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ታክሲ አሽከርካሪዎች መብት ትግል
- ግብጽ እውን በአባይ ጉዳይ በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት ታነሳለች? (ወቅታዊ ዘገባ)
- ሙስናው ምነው ገቢዎች ላይ ብቻ ቆመ? ዋናዎቹስ? (ትንታኔ አለን)
ሌሎች ቃለ መጠይቆችም አሉን

ዜናዎቻችን:-
- ሕዝቡ ፍርሃትን አሸንፎ ለሰላማዊ ሰልፍ ወጥቶ ምሬቱን መግለጹ ብዙዎችን አስገርሟል
* ሰማያዊ ፓርቲ ከሁለት ወር በፊት ለግራዚያኒ ሰልፍ ሲጠራ አመራሮቹ መታሰራቸው ይታወሳል
- የኢትዮጵያውያን ሰሜን አሜሪካ ፌዴሬሽን አመራሮች በቬጋስ ተጫዋቾች ሊከሰሱ ነው
- ፌዴሬሽኑ ተጫዋቾች አይወክለንም ባሉት ግለሰብ ስር ተመዝግበው እንዲመጡ ውሳኔ ወስኗል
- ግብጽ በኢትዮጵያ ላይ ጥቃት ብትፈጽም የከፋ ኪሳራ እንደሚጠበቃት የእገሪቱ ከፍተኛ ጄነራል አስጠነቀቁ
- በኢትዮጵያ ውስጥ መሬት የተቀራመቱ ባእዳን ባለሃብቶች ከአገዛዙ ጋር ሆድ እና ጀርባ እየሆኑ ናቸው ተባለ ኢሃዲግ እርምጃ እስውዳለሁ ሲል ዝቷል
- ሟቹ መለስ ዜናዊ የ3ቢሌዮን ዶላር ባለቤት መሆናቸው ዛሬም እያነጋገረ ነው

ሌሎችም ዜናዎች አሉን:-

↧

Sport: ብራዚላዊው አጥቂ ኔማር ባርሴሎና ገባ

$
0
0

Neymar-Barcelona

Neymar: Barcelona complete ÂŁ49m signing of Brazil striker

ብራዜላዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኔማር ለስፔኑ ሃያሉ ክለብ ባርሴሎና ለመጫወት በ48.6ሚሊዮን ኢሮ ከቀድሞው ክለቡ ሳንቶስ ተዘዋውሯል፡፡
የ21 ዓመቱ ብራዚላዊው ኔማር በባርሴሎና ለ5ዓመት ለመቆየት ተስማምቷል፡፡ ኔማር በሳኦ ፖሎ ቆይታው 229 ጭዋታ አድርጎ 138 ጎሎችን አስቆጥሯል፡፡ ለሀገሩ ብራዚልም በተሰለፈባቸው 33 ጭዋታዎች 20 ጎሎችን በስሙ አስቆጥሯል፡፡
ኔማር በአምስት ዓመት የባርሴሎና ቆይታ 190 ሚሊዮን ዩሮ ያገኛል፡፡ ኔማር ኑካንብ እስከሚደርስ ድረስ ለሳንቶስና የባለቤትነት መብት ላላቸው ሶስት ካንፓኒዎች 57ሚሊዮን ዩሮ ወጥቶበታል፡፡
ኔማርን ለማስፈረም የወጣው ወጪ ውድ መሆኑ ሌሎች ክለቦች የኔማር ፈላጊ ሆነው በመገኘታቸው ነው ብለዋል የባሴሎና ምክትል ፐሬዘዳንት ጆሴፕ ባርቶሚዩ፡፡
በተመሳሳይ ዜና ማንችስተር ሲቲ በሲቪያ የክንፍ ተጨዋች የሆነውን ጀሰስ ናባስን በ17 ሚሊዮን ዩሮ ለማዘዋወር ሁለቱ ክለቦች መስማማታቸውን የሲቪያ ድረ -ገፅ አረጋግጧል፡፡ የ27 ዓመቱ ናቫስ እ.ኤ.አ በ2010 በተካሄደው የአለም ዋንጫ የውጤታማው የስፔን የእግር ኳስ ቡድን አባል መሆኑ ይታወሳል፡፡

↧
↧

ሁመራን የብሄር ግጭትና የኤርትራ ታጣቂዎች አመሷት

$
0
0

(ሁመራ ከተማ)

(ሁመራ ከተማ)


(ፍኖተ ነፃነት) በምዕራብ ሁመራ ማይካራ መቻች በተከሰተ የብሔር ግጭት የሰዎች ህይወት ጠፋ፤ መንግስት ግጭቱን ለማስቆም የወሰደው እርምጃ አለመኖሩ በአካባቢው ተከታታይ ግጭቶች ሊቀሰቀስ ይችላል የሚል ስጋት መፍጠሩን የአካባቢው ምንጮች ለፍኖተ ነፃነት አስታወቁ፡፡
ሱዳን ጠረፍ ላይ ቅዳሜ ግንቦት24 ቀን 2005 ዓ.ም በብሄር ምክንያት የተቀሰቀሰው ይኸው ግጭት በሁለት ቀናት ውስጥ የ12 ሰዎችን ህይወት መቅጠፉንፉን የፍኖተ ነጻነት ምንጮች ጨምረው ገለፀዋል፡፡ በኢትዮጵያና ሱዳን ጠረፍ አካባቢ በምትገኘው መቻች በረሃ በቀን ራያ የተሰማሩ ሰዎች በብሄር እየተቧደኑ መገዳደል ከጀመሩ ሶስት አመታት ማስቆጠራቸውን ያስታወሱት ምንጮቻችን መንግስት ችግሩን መፍታት ምንም አይነት ሚና ለመጫወት አለመፍቀዱ የሟቾቹንና የተጎጂዎቹን ቁጥር እንዲያሻቅብ አድርጓል፡፡
ሰራተኞቹ በወሎ፣በጎጃም፣በጎንደርና በራያ ተወላጅነት ተቧድነው በካራ፣በዱላና በእሳት በፈጠሩት ግጭት የሰው ህይወት ተቀጥፏል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው አካባቢውን ጠሚያውቁ አስተያየት ሰጪዎች “መንግስት በኢትዮጵያ የብሄር ጥያቄ ተመልሷል በማለት የብሄር ብሄረሰቦችን በዓል በሚያከብርበት ወቅት በጎሳ ፖለቲካ እንዲህ አይነት ዘግኛኝ ድርጊቶች እየተፈጠሩ የሰው ህይወት መብላታቸው ጥያቄዎቹ በተገቢው መንገድ ላለመመለሳቸው ማሳያ ይሆናል” ብለዋል፡፡
በተያያዘ ዜና በዚሁ በሁመራ በረከት ወረዳ ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ በመግባት ለመዝረፍ የሚሞክሩ ሽምቅ ተዋጊዎች በተለያዩ ጊዜያት ድንገተኛ ወረራ በማድረግ የአካባቢውን ነዋሪዎች ሲያስጨንቁ እንደነበር የጠቀሱት ምንጮቻችን በቅርቡ ታጣቂዎቹ አካባቢውን ከሚጠብቁ ሚልሺያዎች ጋር ባደረጉት የተኩስ ልውውጥ በሁለቱም ወገን ህይወት መጥፋቱን አጋልጠዋል፡፡ በተደጋሚ የማያባራ የተኩስ ልውውጥ መስማት በአካባቢው የተለመደ እንደሆነም የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ጨምረው ገልፀዋል፡፡
በሁመራ ስለተከሰተው የግጭት ለማጣራት የአካባቢውን ባለስልጣናትና የፖሊስ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡

↧

ለአርቲስት አበበ መለሰ ገቢ ማሰባሰቢያ 9 ዘፋኞች በአ.አ የሙዚቃ ኮንሰርት አዘጋጁ፤ ኤፍሬም ታምሩ?

$
0
0

abebe melese(ዘ-ሐበሻ) ለዜማና ግጥም ደራሲው አበበ መለስ መርጃ የሚውል ታላቅ የሙዚቃ ድግስ በአዲስ አበባ እንደተዘጋጀ ታወቀ። በዚህ ሰኔ 8 ቀን 2013 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይደረጋል በተባለው ኮንሰርት ላይ 9 ዘፋኞች ለአርቲስቱ መርጃ በሚውለው ኮንሰርት ላይ በነፃ ለመሥራት ቃል ሲገቡ ኤፍሬም ታምሩ ግን ተጠይቆ ፈቃደኛ ሳይሆን መቅረቱን ከአስተባባሪዎቹ አካባቢ ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመልክቷል።
እንደ ደረሰን መረጃ ከሆነ ለአርቲስት አበበ መለሰ መረጃ፦
1ኛ. ቴዎድሮስ ካሳሆን (ቴዲ አፍሮ)
2ኛ. ግርማ ተፈራ
3ኛ. ሀመልማል አባተ
4ኛ. ፀሐዬ ዮሐንስ
5ኛ. ማዲንጎ አፈወርቅ
6ኛ. ጸጋዬ እሸቱ
7ኛ. ሃይልዬ ታደሰ
8ኛ. ዳዊት መለስ ሥራዎቻቸውን ለማቅረብ ፈቃደኛ ሲሆኑ ድምጻዊ ኤፍሬም ታምሩ ግን በኮንሰርቱ ላይ እንደማይገኝ ተናግሯል። ለኤፍሬም ታምሩ በርከት ያሉ ዜማዎችን መስጠቱን የሚያስታውሱት አስተያየት ሰጪዎች አሁን ይህ ዝነኛ ሰው የሰው እጅ ለማየት በተገደደት ወቅት ኤፍሬም ፊቱን ማዞሩ ብዙዎችን እያነጋገረ መሆኑን ከአዲስ አበባ የመጣው መረጃ ያመለክታል። በዚህ ጉዳይ ድምጻዊ ኤፍሬም ታምሩን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

አበበ መለሰ እስራኤል ሃገር ከሚገኝ አንድ ቲቪ ጋር በቅርቡ ያደረገውን ቃለ ምልልስ ይመልከቱ።

↧

ቆስቁሱት ይጋጋም የአብዮቱን እሳት (ወቅታዊ ግጥም ለግንቦት 25ቱ ሰልፍ)

$
0
0
↧

Breaking News: ሲኖዶሱ አቡነ ፊልጶስን በአቡነ ማቴዎስ፤ አቡነ ሕዝቅኤልን በአቡነ ሉቃስ ተካ

$
0
0
አቡነ ሉቃስ

አቡነ ሉቃስ

(ዘ-ሐበሻ) አዲስ አበባ የሚገኘው ሲኖዶስ በዛሬው የ5ኛ ቀን ጉባኤው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅን እና የቅዱስ ሲኖዶሱን ዋናጸሐፊዎች ምርጫ አካሄደ።  

ሲኖዶሱ በዛሬው የ5ኛ ቀን ጉባኤው ከዚህ ቀደም ለ3 ዓመታት አቡነ ሕዝቅኤል ይዘውት የነበረውን ሥልጣን የሰቲት ሁመራው ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሉቃስ ተክተው እንዲሰሩ እንደመረጣቸው የዘ-ሐበሻ ምንጮች አረጋግጠዋል። በሌላ በኩልም አቡነ ፊሊጶስ ይዘውት የነበረውን መንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅነቱን ሥልጣን ደግሞ  የወላይታ ዳውሮ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ እንዲይዙት መርጧል።

አቡነ ማቴዎስ

አቡነ ማቴዎስ

አቡነ ማቴዎስ ለ6ኛው የፓትርያርክነት ተወዳድረው ‘ተሸንፈዋል’ በሚል ቢነገርም መንግስት አቡነ ማትያስን ከ እየሩሳሌም አምጥቶ መሾሙን የሚያምኑ አስተያየት ሰጪዎች አቡነ ማቴዎስ በምርጫ ተሸንፈዋል ብለው እንደማያምኑ በተለያየ አጋጣሚ አስተያየታቸውን መስጠታቸው ይታወሳል።

አቡነ ፊሊጶስ

አቡነ ፊሊጶስ

ለፓትርያርክነት ምርጫ ተወዳድረው እንደነበር የሚታወሱት  አቡነ ሉቃስ ጋራ ለቅ/ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊነት በዕጩነት የቀረቡት ጳጳሳት አቡነ ሔኖክ እና አቡነ ዲዮስቆሮስ መሆናቸውን የሚናገሩት የዘ-ሐበሻ ምንጮች  አቡነ ሉቃስ ከፍተኛ ድምፅ አግኝተው በመመረጣቸው ለቀጣዩ ሦስት ዓመታት ቅ/ሲኖዶሱን በዋና ጸሐፊነት እንዲያገለግሉ መመረጣቸውን አስታወዋል።

አቡነ እሕዝቄል

አቡነ ሕዝቅኤል

አቡነ ማቴዎስ የተወለዱት ምንጃር፣ አቡነ ሉቃስ ደግሞ ትግራይ ተምቤን የተወለዱ አባቶች ናቸው።

እየተካሄደ ባለው የአዲስ አበባው ሲኖዶስ ጉባኤ ላይ አስተያየት እንዲሰጡን የጠየቅናቸው አንድ የሃይማኖት አባት “ሲኖዶሱ ከዚህ ቀደም የትግራይ አርቲስቶች በመኪና አደጋ ሲሞቱ ታቦት ተሸክመው በመሄድ ለአርቲስቶቹ ፍትሃት እንዳደረጉት ሁሉ፤ በባህርዳር ከተማ ይህ ሁሉ ሰው በጥይትና በተፈጥሮ አደጋ ሲሞት ተመሳሳይ ነገር አልተደረገም። ይልቁንም አንዳችም  መግለጫ አለማውጣቱና አለመወያየቱ፤ የዋልድባ ጉዳይን አልማንሳቱ በጣም የሚያስተዛዝብ ነው” ብለውናል።  እኚሁ አባት ጨምረውም “አዲስ አበባ ያሉት አባቶች ስለሙስና ትኩረት ሰጥተው መወያየታቸው የሚያሳየው ቤተክርስቲያን ምን ያህል እየተመዘበረች እንዳለች ነው። አሁንም እነዚህ አባቶች በሙስና ጉዳይ ላይ የሚነጋገሩት እከሌ ከኔ የተሻለ ሰርቋልና እኔም እንዴት ልሰርቅ እችላለሁ በሚል ነው እንጂ እውነት ሙስናን ከቤተክርስቲያኒቱ ለማጠፋት ቁርጠኝነት ኖሮ አይደለም” ሲሉ አሰታየታቸውን አጠናቀዋል።

↧
↧

የጎሕ መንፈስ (በየነ ሞገስ)

$
0
0

የጎሕ መንፈስ
(በየነ ሞገስ)
Rainbow-Spiritየዕለቱ ውሎዬ አድካሚ ሆኖ ነው ያለፈው፡፡ ጉዳይ ለመከታተል በየመስሪያ ቤቱ መሄድ፤ የማኅበራዊ
ግዴታዎችን መወጣት፤ እንዲሁም ለማተሚያ ቤት የሰጠሁትን ኅትመት የመጨረሻ ይዘቱን ተመልክቶ
ማረምን የሚያካትት ነበር፡፡ ይህ ሁሉ ተዳምሮ ወደ ምሽት ላይ እቤቴ እንደገባሁ ወደ መኝታዬ ለመሄድ
ብዙ ጊዜ አልወሰደብኝም፡፡ ትንሽ የማጋነን ስሜት ቢኖርበትም እንቅልፍ የወሰደኝ አንገቴ ትራሱን ሳይነካ
ነበር፡፡ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ – - -ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

↧

ለተላላ የ”ህዳሴ”ግድብ አቀንቃኞች (ክፍሉ ሁሴን)

$
0
0

በክፍሉ ሁሴን

የኢትዮጲያ ባህር በር ዘጊ

የባድሜ “ሉዓላዊነት”ዘማሪ

ደርሶ የ”ህዳሴ”ግድብ ደራሲ

ይበል!መባሉ ባለ”ራዕይ”መሪ

ከቴም የአባይ “ገዳቢ”

የአገር ልማት ጉዳይ አራጋቢ

እያየነው ውጥኑን

የመሰሪውን

እያፈናቀለ አገሬውን

ባእዱን የሚተክለውን

ግፉ ላፍታም የማያባራውን!

እንዴት ተዘነጋን

የአረብ ምንደኛ ሆኖ እንዳናቆረን?

እንዴትስ ተላላ ሆን

ዛሬ ልገድብ ነው ሲለን

የእኛን የጦር ሃይል በትኖ

በግብፅ ጦር ፊት በመሄድ ላይ ባለው ገኖ?

የከትናንት ወዲያው ይቅር

እንዴት የትናንቱ ይረሳል የባድሜው አሻጥር

አስፈጅቶ ያን ሁሉ ወጣት

ባድሜን ሳናውቃት ሻምፓኝ አጋጭቶ እንደለቀቃት?

አሁንስ ምን ዋስትና አለ

በአባይ ስም የሚያመረቅዝ መርዝ

ዘርቶ እንዳልሆነ እንዳልተከለ?

ከየት ይመጣል ማረጋገጫ ከቶ

ንስሃ በመግባት ፈንታ አንጎሉ ኮስሶ እንደዶሮ

ባልበላውም ልድፋው ላድፋፋው ብሎ

በመጨረሻ ትንፋሹ እንዳልተከለብን የማይነቀል መርዝ

በ”ህዳሴ”ስም ለትውልድ የሚተርፍ መዘዝ?

ካምፓላ፤ዩጋንዳ  ግንቦት 27, 2005 ዓ.ም

↧

ለአንዳንድ ጥያቄዎች መልስ (ከፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)

$
0
0

ከፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

ግንቦት 2005

Pro Mesfinበጽሑፎቹ ላይ የቀረቡት አስተያየቶች በመሠረቱ ሁለት ዓይነት ናቸው፤ አንዳንዶቹ እንደምክር ያለ ነገር፣ አንዳንዶቹ ጽሑፎቹን መውደዳቸውን ወይም አለመውደዳቸውን በመግለጽ ጽፈዋል፤ በነዚህ ላይ ምንም አስተያየት የለኝም፤ መውደድም ሆነ መጥላት፣ መንቀፍም ሆነ ለወደፊት የምሻሻልበትን ምክር መስጠት መብታቸው ነው፤ በግድ እኛ የምንልህን ተቀበል ሲሉኝ ከመብታቸው ያልፋሉ፤ ቢሆንም መልስ አያስፈልጋቸውም።

ሌሎች አስተያየት ሰጪዎች ወደፍሬ-ነገሩ ውስጥ ገብተው ለመሞገት ይሞክራሉ፤ ግልጽ የሆነ የሁነት ግድፈት ሲያገኙ ቢያመለክቱኝ በደስታና በምስጋና እቀበላቸዋለሁ፤ ሁነቱ ለእነሱ በሚጥም መንገድ ባለመገለጹ ወይም ሁነቱን እነሱ የሚወዱት ባለመሆኑ ሙግት ውስጥ የሚገቡ ሲሆን የማይጠቅም መሆኑን ስለተረዳሁ አንድ ዘዴ አቀረብሁ፤ ሁነቱ እኔ ከገለጽሁት ውጭ ሆኖ ከተገኘ አምስት መቶ ብር እከፍላለሁ ብዬ ጻፍሁ፤ እስከዛሬ ብሩን የጠየቀኝ የለም፤ ሊሞግተኝ የሞከረውም አዋቂ ነኝ-ባይ ከዝምታ አልወጣም፤ ፍሬ-ነገሩ ሙግት የሚያቀርቡ ሰዎች ሁለት ዓይነት ይመስሉኛል፤ በቅን መንፈስ በውይይቱ ላይ አስተዋጽኦ ለማድረግ የሚፈልጉ አሉ፤ ሌሎች ደግሞ ሌላ ሰው ሲጽፍ እየጠበቁ ‹‹እኛ የተሻለ አለን›› እያሉ የሚጮሁ አሉ፤ ዓላማቸው ውይይቱን ለማዳበር ሳይሆን ራሳቸውን አብጧል ከሚሉት ሰው እኩል ማሳበጥ ቢቻልም መብለጥ ነው፤ በራሳቸውም ሆነ በሀሳባቸው እምነት ስለሌላቸው የሚናገሩት ራሳቸውን በመቃብር ውስጥ ከትተው ነው፤ በመቃብር ቤት ውስጥ ማበጥ ለምስጦች እንደሆን እንጂ ለሌሎች ‹‹የጭቃ እሾህ›› የሚል ስያሜን ከማትረፍ አያልፍም።

በተከታታይ በቀረቡት ጽሑፎች ላይ ሁለት አንባቢዎች በተቸገሩባቸው ሀሳቦች ላይ አስተያየቴን ልስጥ፤ በመጀመሪያ አርበኛና ባንዳ የሚባሉትን ቃላት የማይወዳቸው አንባቢ ችግሩ አልገባኝም፤ ስገምተው ከቅን መንፈስና ከኢትዮጵያዊ ይሉኝታ ጋር የተያያዘ ይመስለኛል፤ አርበኞችና ባንዶች መኖራቸውን የካደ አይመስለኝም፤ አርበኞች ነበሩ፤ አሁንም አሉ፤ ባንዶችም ነበሩ፤ አሁንም አሉ፤ አርበኛም የለም፤ ባንዳም የለም ለማለት አልችልም፤ ባንዳነት ሲነሣ ኅሊናቸውን የሚቆረቁራቸውና የሚያፍሩ ባንዳዎችና የባንዳ ልጆች ከአሉ፣ ይቆርቁራቸው፤ ይፈሩ፤ የሚያሳፍር ሥራ ውጤት ነው፤ አርበኝነት ሲነሣ ልባቸው የሚያብጥና የሚኮሩ ካሉ፣ ይበጡ፤ ይኩሩ፤ የሚያኮራ ሥራ ውጤት ነው፤  ምንድን ነው ስሕተቱ? የታሪካችን መክሸፍ አንዱ ምክንያት በይሉኝታ ዓይኖችን ሸፍኖ ፍሬውንና አንክርዳዱን ለመለየት አለመፈለግ ነው፤ (በአሥራ ዘጠኝ መቶ አርባዎቹ አጋማሽ ላይ በጾም ጊዜ በምግብ ቤቶች የሚቀርብ የፍስክ ወጥ ነበረ፤ ሽፍንፍን ይባል ነበር፤ ሳይጾሙ የሚጾሙ መስሎ ለመታየት፤) እንክርዳዱንና ፍሬውን እኩል አድርጎ ለማየትና ለማሳየት መፈለግ ነው፤ የኢትዮጵያ አርበኞች ታሪክ ተዳፍኖ የቀረው በአጼ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት ውስጥ ባንዶች ተሰግስገውበት ስለነበረ ነው፤ በዚህም ምክንያት ፍሬና እንክርዳዱ ሳይለይ አንዱ ትውልድ ለሚቀጥለው ትውልድ እያስተላለፈ መማርና መሻሻል ያቅተናል፤ አንባቢው ይህንን ይመኛል ብዬ አልገምትም፤ እውነትን የሚገፋ፣ እውነትን የሚያደበዝዝ፣ እውነትን የሚያጨልም ነገር ሁሉ በአገርም ሆነ በግለሰብ ደረጃ መጨረሻው ገደል ነው።

ሁለተኛው ምንም አንኳን በጎ ፈቃድ ከሌለው ሰው የተሰነዘረ ቢሆንም ሌሎችን ሰዎች ሆን ተብሎ ከሚረጨው መርዝ ለመጠበቅ ባጭሩ በአንድ ሀሳብ ላይ ብቻ የሰውዬውን ጤናማ ያልሆነ ዓላማ ላሳይለት፤— እኔ የሚከተለውን ጻፍሁ፤–

የኢሳት መክሸፍ የኢትዮጵያውያንን ተስፋ ያጨልማል፤ አንፈራጥጠው ከላይ ቤት እታች ቤት እየቀላወጡአካላቸውን፣ አእምሮአቸውንና መንፈሳቸውን የሚያባልጉ ሰዎችን ያበራክታል፤ የድብቅብቆሽ ዓለምን እየፈጠሩየጠራውን ከደፈረሰው፣ የጸዳውን ከአደፈው፣ ሳይለዩ ለሚያወሩት ደካሞች ሜዳውን ያሰፋላቸዋል፤የወያኔ/ኢሕአዴግን ፍርሃት ወደመርበድበድ ይለውጠዋል፤ የጦርነት ጥሩምባ ለሚነፉትም ሜዳውን እያሳየ  የቀረርቶበር ይከፍትላቸዋል፤ ይህ ሁሉ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሰላምንና ስምምነትን፣ እድገትንና ብልጽግናን፣ ኩራትንና ክብርንአያስገኝም።

በነዚህ አምስት መስመሮች ላይ የሰፈረው ሀሳብ አስቸጋሪ አይደለም፤ ማንበብና መጻፍ እችላለሁ ለሚል ሰው ቀላል ነው፤ ዋናውና መሪው ሀሳብ የኢሳት መክሸፍ የኢትዮጵያውያንን ተስፋ ያጨልማል፤ የሚለው ነው፤ አራት የሚሆኑ አጫፋሪ ሀሳቦች ተከታትለው ቀርበዋል፤ የኔን ጽሑፍ ሲያነብ አንጎሉ እያጠናገረ የሚመዘግብለት ሰው ሲጽፍም አንጎሉ አጠናግሮ የመዘገበለትን ስለሚያቀርብለት የተወላገደ መደምደሚያ ላይ ይደርስና ያንኑ ለሌሎች አዋቂ መስሎ ያስተላልፋል፤ ላንዳንዶች ሰዎች ይህ አገላለጼ የከረረ ይመስላቸው ይሆናል፤ በአውነት ይህ አገላለጽ ከበጎ መንፈስ የመነጨ ነው፤ በጎ መንፈስ የሌለበት አገላለጽ ብመርጥ የበለጠ የሚያስከፋ ይሆን ነበር፤ የእውነት ውበት የሚታየው ጨለማውን ሲገልጠው ነው፤ አንዱ አስተያየት ሰጪ እንዳለው ‹‹የጭቃ እሾሁን›› ማየት መቻል ነው፤ እንግዲህ ከላይ የተጻፈውን ሰውዬው እንዴት አወላግዶ እንደተገነዘበውና እንዴት አወላግዶ እንዳወጣው እዩት፤ –

“የኢሳት መክሸፍ የኢትዮጵያውያንን ተስፋ ያጨልማል፤ ………………………………የጦርነት ጥሩምባ ለሚነፉትም ሜዳውን እያሳየ የቀረርቶ በር ይከፍትላቸዋል፤ ይህ ሁሉ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሰላምንና ስምምነትን፣ እድገትንና ብልጽግናን፣ ኩራትንና ክብርን አያስገኝም። ”እኔም ‹ለሃገራችን ችግር መፍትሄው አንድ መንገድ (የእርሶ መንገድ) ብቻ አይደለም› ያልኩት ኢሳት ነጻ ሚዲያ እንዲሆን የምንሻ ከሆነ ከመርህ አኳያ ሁሉንም በእኩል መድረክ መስጠት እንዳለበት ለመግለጽ ፈልጌ ነው፡፡ ከተሳሳትኩ ለመታረም ዝግጁ ነኝ።››

እግዚአብሔር ያሳያችሁ! ከላይ በትክክል የጠቀስሁትና ይህ ተቆራርጦና ተወላግዶ የቀረበው አንድ ናቸው? እኔ ከጻፍሁትስ እንዴት ብሎ ከውልግድግዱ የተሰጠው መደምደሚያ ሊወጣ ይችላል? ‹‹የጭቃ እሾህ›› ለምን ይጠቅማል? ለማን ይጠቅማል? በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ለኢትዮጵያ ችግር መፍትሔው አንድ መንገድ ብቻ ነው (የኔ ብቻ) ያልሁት የት ነው? ተከታታይ ጽሑፎቹን ሁሉ ያነበበ ሁሉ የተለያዩ አመለካከቶች በእኩልነት ይስተናገዱ የሚል እንደሆነ ከዚህ ሰው በቀር የተረዳው ይመስለኛል።

‹‹ከተሳሳትሁ ለመታረም ዝግጁ ነኝ›› የምትለዋ አስቂኝ ነች!  የተሞከረው ማታለል አልሠራ ሲል ወደሌላ ማታለል! አውቆ የተኛ ቢቀሰቅሱት መች ይሰማል!

↧

የኢሕአዴግ መንግስት በጄኔቭ በኢትዮጵያውያን ከባድ ተቃውሞ ገጠመው – Video

$
0
0
↧
↧

ዶክተር በያን አሶባ ለዶክተር ፍቅሬ ቶሎሳ ግልጽ ደብዳቤ የላኩት መልስ (የአማርኛ ትርጉም)

$
0
0

ትርጉም – ይነጋል በላቸው

ዶር. በያን አሶባ

ውድ ዶክተር ፍቅሬ ቶሎሣ /ቶለሣ

(ዶ/ር በያን አሶባ)

(ዶ/ር በያን አሶባ)

በስሜ አድራሻ የላኩት ግልጽ ደብዳቤ በበርካታ ድረ ገፆች በወጣበት ወቀት እኔ ጉዞ ላይ ነበርኩ፡፡ በዚያም ምክንያት ወዲያውኑ መልስ መስጠት በምችልበት ሁኔታ ላይ አልነበርኩም፡፡ በዚህ በምጽፍልዎ የደብዳቤዎ ምላሽ እኔን ስለሚመለከቱ ነጥቦች ብቻ አነሳለሁ፡፡ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግምባር ስለአጠቃላዩ የደብዳቤዎ ይዘት መልስ ይሰጥዎታል ብዬ አምናለሁ፡፡
ውድ ዶክተር ፍቅሬ
አስተያየቴን መጀመር የምፈልገው በዚህ ግልፅ ደብዳቤዎ የአያትዎን ስም እንዴት ሊጨምሩ እንደፈለጉና ይህ ያልተለመደ አካሄድ ያጫረብኝን ስሜት በማስቀደም ነው፡፡ አቅም በፈቀደ በርካታ የጽሑፍ ሥራዎችዎን ለመመልከት ሞክሬ ሁሉም ‹ፍቅሬ ቶሎሣ› እንደሚሉ አረጋግጫለሁ፡፡ ይህም አያትዎን ያለመጨመር የአጻጻፍ ይትበሃል እ.አ.አ በ1983 በብሬመን ዩኒቨርስቲ ለዶክትሬት ዲግሪዎ ማሟያ ያቀረቡትን ጹሑፍ ጨምሮ በሌሎች በርካታ ተከታታይ ጽሑፎችዎ አልተስተዋለም፡፡ በፌስቡክዎም የአያትዎ ስም አልተገለጸም፡፡ .እኔ እስከማውቀው ድረስ የራስዎን ስም ፍቅሬ ቶላሣ (Tolassa, not ከዚህ በፊት ይጠቀሙበት ነበር እንደሚባሉት Tolossa!) ብለው መጻፍ ብቻ ሣይሆን ‹ጂግሣ› የሚለውን የአያትዎን ስም ተጠቅመው የጻፉት በዚህ ግልጽ ደብዳቤዎ ብቻ ነው፡፡
እርስዎም እስካሁን ወደጎን ትተዋቸው እንደነበረው ሁሉ አሁን ‹ጂግሣ›ን ባሉበት እንዲያርፉ ለቀቅ እናድርጋቸውና አዘውትረው በሚጠቀሙበት ቶሎሣ/ቶለሣ በሚለው የአባትዎ ስም ላይ ትኩረታችንን እናውል፡፡ ‹ቶሎሣ› የሚለው ስም ‹ቶሎ› ከሚለው የአማርኛ ቃል ተወስዶ ኦሮምኛ እንዲመስል ‹ሣ›ን በመጨመር የተበጀ ቃል ሊሆን እንደሚችል እገምታለሁ፡፡ በሌላ በኩል ‹ቶላሣ› ከኦሮምኛው ‹ቶላ› የተገኘ እንደሆነ በርግጠኝነት ዐውቃለሁ፡፡ በዚህም ሆነ በዚያ ስምዎን በሁለት መንገድ እየጻፉ ሁለት ተቃራኒ ማንነቶችን ለመላበስ መፈለግዎን መረዳት አይገድም፡፡ ይህን በማድረግ በአማራነትና በኦሮሞነት የማንነት አጥር ላይ ፊጥ ማለት ተመኝተው ከሆነ መንገዱን ጨርቅ ያድርግልዎ፤ በአራዶች አነጋገር ‹ይመችዎ!›፡፡ ሊሆኑት ወይም ሊጠሩበት በሚፈልጉት ስምም ይሁን ማንነት የመጠራት መብትዎን ሙሉ በሙሉ አከብራለሁ፡፡
የኔ ጥያቄ ይሄውልዎ፡- እኔ የርስዎን የፈለጉትን የመሆንና በፈለጉት የመጠራት መብት ሳከብርልዎ ለኔስ ይህን መብት ለምን ይነፍጉኛል? ስሜ Bayyanaa Suba አይደለም፡፡ ስሜን ‹Beyan Asoba› ከሚለው ውጪ በሌላ መልክ በፍጹም ጽፌ አላውቅም፡፡ ይህ የሰጡኝ አዲስ ስያሜ አባል የሆንኩበትን የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግምባርን በአንድ ወይ በሌላ መልክ ለመንካት ካልሆነ በስተቀር እኔን በተመለከተ ያወጡልኝ ስም ሊሆን ይችላል ብዬ መቀበል ያቅተኛል፡፡ በግልጽ እንደሚገባኝ ለፖለቲካዊ ዓላማዎ ሲሉ ይህን አዲስ ስም ፈልስፈው ለኔ የሰጡኝ ይመስለኛል፡፡
ለፍጡሮቻቸው ስም ማውጣት የሚቻላቸው ፈጣሪዎች ብቻ ናቸው፡፡ ለምሳሌ ወላጆች ለልጆቻቸው የተለያዩ ስሞችን እንደሚያወጡ ሁሉ የመኪና ፋብሪካዎችም ለምርቶቻቸው የተለያዩ ስሞችን ይሰጣሉ፡፡
እንደመጥፎ ዕድል ሆኖ ለኛ ለኦሮሞ ሴቶችና ወንዶች ልጆች የስቃይና የውርደት ምክንያት ሆኖ አበሣና መከራ ያሳየን የነበረው የሕይወት መሪር ተሞክሯችን ስማችንን እንድንቀይር ትምክህተኞች (አማሮች?) ያደርጉብን የነበረው ጫና ወይም የማስገደድ ተግባር ነው፡፡ ኦሮሞ የሚለው ብሔራዊ መጠሪያችን ከማንኛውም መዝገብ ተፍቆ በርካታ አንቋሻሽ የፍካሬ ትርጉሞች በተለጣጠፉለት ስያሜ እንድንጠራ ተገድደን ነበር፡፡ ተማሪ ልጆቻችን ሳይቀሩ የተዋጣለት ኢትዮጵያዊ መሆን ይችሉ ዘንድ ስሞቻቸውን (ወደ አማራ ስሞች) እንዲቀይሩ በመምህሮቻቸው የሚገደዱበት ሁኔታም ነበር፡፡
በዚያች ሀገር ውስጥ ዋናው የፖለቲካ ማጠንጠኛ ግለሰቦች በቅድሚያ ኦሮሞነታቸውን፣ ሲዳማነታቸውን፣ ወላይታነታቸውን፣ ከምባታነታቸውን፣ ሃዲያነታቸውን ወዘተ. እንዲገድሉና በውጤቱም ኢትዮጵያዊ የሚባል የጋራ ማንነት መገለጫ እንዲኖራቸው ጥረት ማድረግ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ ኦሮሞነትና ኢትዮጵያዊነት አብረው ሊሄዱ ካልቻሉ ምርጫው ሁለት ነው፤ አንድም የእርስዎን ኢትዮጵያዊነት ባፍንጫችን ይውጣ ብለን መተው፣ አለበለዚያም በነበረው አካሄድ ነጻነትን ተነጥቀን እንደጥንቱ እያለቀስንና እየተሰቃየን መኖር፡፡
ለእርስዎና መሰሎችዎ በሚገባ ግልጥ አድርጌ ልነግራችሁ የምፈልገው አንድ ነገር አለኝ፡፡ ያም ኦሮሞዎች ማንነታቸውን ክደው በሚጣልባቸው የራሳቸው ያልሆነ ማንነት የሚንበረከኩበት ጊዜ አልፏል ወደፊትም አይመጣም፤ በዚህ ዕርማችሁን አውጡ፡፡ ኦሮሞነትን የሚጋፋ ኢትዮጵያዊነት አንቀበልም፤ ይህ ኢትዮጵያን ከኦሮሞ የማስቀደም አካሄድ እስካልቀረ ድረስም ትግላችን ይቀጥላል፡፡ ምርጫው የእርስዎና የቢጤዎችዎ ነው፡፡ እኛን ከነኦሮሞነት ማንነታችንና ከሌሎች ተዛማጅ መብቶቻችን ሙሉ በሙሉ መከበር ጋር ትቀበላላችሁ ወይም ከአደንቋሪ የኢትዮጵያዊነት ስብከታችሁና ከኢትዮጵያ አንድነታችሁ ጋር ጥንቅር ብላችሁ ልትቀሩ ትችላላችሁ፡፡ በኦሮሞዎች መቃብር ላይ፣ በሲዳማዎች መቃብር ላይ፣ በወላይታዎች መቃብር ላይ፣ በከምባታዎች መቃብር ላይ፣ በሃዲያዎች መቃብር ላይ፣ ወዘተ. የኢትዮጵያን አንድነት ለመገንባት ሲቋምጡ አንድ ዓይነት የሞራል ጉድለት አይታየዎትም ይሆን? ይህ ዓይነቱ ጉዞ መጨረሻው የማያምርና ከቆመለት ዓላማ የተለዬ መጥፎ ውጤት ሊያስከትል እንደሚችል መገንዘብ እንዴት አቃተዎት? ይህ ዓይነቱ ኢምክንያታዊና ኢሞራላዊ የጥፋት መንገድ በመጨረሻው ስክነትንና ማስተዋልን ተላብሶ የሁሉንም በግዛቲቷ የሚኖሩ ወገኖች ፍላጎት ባማከለ ሁኔታ ሁሉንም የሚወክል ማንነት እንደሚያብብ ታላቅ ተስፋ አለኝ፡፡
በመጨረሻም በዚህ ራስ ምታት የሚለቅ አስቸጋሪ ጉዳይ ዙሪያ ይህ የአጸፋ መልሴ የመጀመሪያየም የመጨረሻየም እንደሆነ ልገልጽልዎ እወዳለሁ፡፡
በያን ኤች አሶባ (Beyan H. Asoba 5/29/13)

ከ‹ተርጓሚው› የተሰጠ አጭር አስተያየት
1. በአማርኛ ለተጻፈ ግልጽ ደብዳቤ በእንግሊዝኛ መልስ መጻፍ ምን ማለት ነው? ዶክተሩ ከጋና ነው ወይንስ ከእንግሊዝ የተገኙት? እዚሁ ከቅኝ ገዢዋ ኢትዮጵያ ውስጥ አልተፈጠሩ ይሆን? (ኢሣይያስና መለስ ነፍሳችሁ አይማር – ጥቁር ውሻም ውለዱ!) ዶክተር በያን ከአማርኛና ከእንግሊዝኛ የትኛውን አጣርተው ሊናገሩ ዌም ሊጽፉበት እንደሚችሉ በእንግሊዝኛ በጻፉት መልሳቸው በውል ተረድቻለሁ፤ ታዲያ አማርኛ ላይ ያላቸውን ጥላቻ ለመግለጽ አውሮፓና አሜሪካ ድረስ ሄደው ለምን ትዝብት ውስጥ ይገባሉ?

2. የኢሣት የተለያዩ ባንዲራዎችን በኢትዮጵያ ስም ማስተናገድ ምን ማለት ነው? በጣም ይታሰብበት፤ በልክ ያልተያዘ ፍቅርና ጥላቻ መዘዝ አለው፡፡ ስንወድም ስንጠላም፤ ስንቀርብም ስንርቅም በምክንያት ይሁን እንጂ በስሜት አይሁን፡፡ የኢትዮጵያ ባንዲራ እንኳንስ ለአንድ ሕዝብ ለመላው ዓለም በቅቷል – የሌሎች ሀገራትን በተለይም የአፍሪካውያንን ባንዲራዎች ተመልከቱ፡፡ እኛ የምንጸየፋትን አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ቀለማት ባንዲራ ከእኛ እየኮረጁ በተለያየ አቀማመጥ ይጠቀሙባታል፤ ነፈዞች ደግሞ የገዛ ባሏን የጎዳች መስሏት ገላዋን በጋሬጣ እንደሸነተረችው ሞኝ ሚስት እየሆኑ ያስቁን ይዘዋል፡፡ አትለማመጡዋቸው፤ ይልቁንስ የራሳችንን ሥራ እንሥራ፤ እውነትና ግልጽነት ያልተገባ ይሉኝታንና ፍርሀትን ያስወግዳሉ፡፡ እውነቱን ልባችን እያወቀው አንደበታችን በሀሰት ማባበልን ይተው፡፡ ለየትኛው ጊዜ…
የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁንልኝና በዚህ ጉዳይ ሰፋ ባለ ሁኔታ እመጣበታለሁ፡፡ በየወንዙ እንደሚማማል የማይተማን ጓደኛ ለማያዛልቅ ስትራቴጂ አንድ ጠረጴዛ ዙሪያ በአካል የተቀመጡ መስለው በምናብ ግን ተራርቀው መቀመጥ የሚያዋጣ አይደለም፡፡ እያፈረሱ ግንባታ የለም፤ እየጠሉ አንድነት የለም፤ የሚጸየፉህን ልመናና ልምምጥ የለም፡፡ የደነዘ አስተሳሰብ በምንም ዓይነት ሣሙና ቢታጠብ አይነጻም፡ ዐውቆ የተደበቀን ቢጠሩት አይሰማም፡፡ በጠላት ተቀፍቅፎ በበጎች ጋጣ ውስጥ የመሸገ ቀበሮና ተኩላ በልምምጥና እውነትን በመሸፈን በሚደረግ ልመና በረቱን ለቅቆ አይወጣም፤ የነገ ሰው ይበለን፡፡

↧

አዲስ ጉዳይ መጽሔት፡ ማኅበራዊ ሚዲያ ፕሬሱን እየተካ ይሆን?

$
0
0

(ይህ ጽሁፍ በአዲስ አበባ ታትሞ የሚወጣው አዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ ታትሞ የወጣ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን)
የለውጥ ድምፆች
ማኅበራዊ ሚዲያ ፕሬሱን እየተካ ይሆን?

facebook-youtube-twitter“ስለሰው ልጅ ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ ጥቅም ሳስብ ወደአዕምሮዬ የሚመጣው የተወጠረ ፊኛ ነው” ብሎ ይጀምራል የአዲስጉዳይ ዘጋቢ ያነጋገረው ተሾመ ምናላቸው የተባለ ከኢንድራጋንዲ ዩኒቨርሲቲ በሶሲዮሎጂ ሁለተኛ ዲግሪውን ያገኘ ወጣት። “የሰው ልጅ እንደተወጠረ ፊኛ ነው። በአዕምሮው የሚያሰላስለውን ሐሳብ ካልተነፈሰው ይፈነዳል። ማኅበራዊ ተራክቦው ዝቅተኛ ሲሆን፤ ወይም ከነአካቴው ሲዘጋ ‘እኔን መሰል ሌላም አለ’ ብሎ ማሰብ ያዳግተዋል። መሰሉን ማግኘት ያልቻለ ሰው ደግሞ ብቸኝነትና መገለል እንዲሁም ያለመፈለግ ስሜት ያድርበታል። ከፍተኛ ጭንቀትና ድብርት ሲነግሱበት ያለጥርጥር በውስጡ አብዮት ይነሣል። ይህ አብዮት ሰውን እንዲጠላና እንዲርቅ፣ ወይም በራሱ ላይ እስከሞት የሚያደርስ እርምጃ እንዲወስድ ይገፋፋዋል። ይህ በጤናው ላይ የሚከተለው መዘዝ ነው። ከዚህ ጋር ተዛማጅ በሆነ መልኩ ማንም ሰው የፈለገውን የመናገርና በነጻነት የማሰብ ተፈጥሮአዊ መብቱ የተከለከለ ጊዜም ልክ በጤናው ላይ እንደሚፈጠረው ያለ አብዮት ነው የሚያስነሳው። ለለውጥ ይቀሰቀሳል። መተንፈሻ ቀዳዳ ለማግኘት በሚያደርገው ፍትጊያ ቁጣና እልህ የተሞላበት ጥፋት ይፈጽማል። በየትኛውም መንገድ ስሜቱን ለመግለጽ ከመሞከር አይቦዝንም። ይህ የሰው ተፈጥሮአዊ ባሕሪ ነው። ሰውን ከመናገርና ሐሳቡን ከመግለጽ መከልከል ብዙ ጊዜ የሚያስከትለው ውጤት መልካም የማይሆነውም ለዚህ ነው” ይላል።
በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ያለው ሐሳብን በነጻነት የማንሸራሸሪያ መንገድ እጅግ ጠባብ እየሆነ መጥቷል የሚሉ ወገኖች በተለይ የነጻ ፕሬስ መዳከምንና መረጃም ከአንድ ወገን ብቻ በብዛት መፍሰሱን እንደጤነኛ አካሔድ አይመለከቱትም። ኢትዮጵያ ውስጥ አልፎ አልፎ የሚከሰቱትን እንደ 1997 ዓ.ም ዓይነት ግብታዊ ትግሎችም ከሐሳብ በነጻነት አለመንሸራሸርና ልዩነትን በመግባባት ተቀብሎ የመራመድ ባሕል መዳበር አለመቻል ጋር ተያይዞ ከዚህ አፈና ለመውጣት ከሚደረግ ትግል ጋር ያያይዙታል። በሀገሪቱ በአሁኑ ወቅት ያሉት የኅትመትና የብሮድካስት ውጤቶች በአብዛኛው በመንግሥት ቁጥጥር ሥር መሆናቸው፣ ጥቂት የሚባሉት የግል ሚዲያዎችም የብዙኀኑን ሐሳብ ለማንጸባረቅ በሚያስችል መልኩ በኅትመት ሥርጭትም ሆነ በይዘትና ጥራት በሚፈለገው መጠን ያለመደራጀታቸው የሀገሪቱ የፕሬስ ዕድገት ‘እንደካሮት ቁልቁል’ እንዲሰርግ አስገድዶታል ይላሉ። ለዚህ ተጠያቂ የሚያደርጉት ደግሞ መብቱን በወረቀት ሰጥቶ በተግባር የነሣውን መንግሥት ነው። ለዚህም ነው በኢትዮጵያ ዛሬ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ፕሬሱን ተክተው አንዳንዴም ቀዳሚ ሆነው እየመሩ ተመራጭ የሐሳብ መለዋወጫና የአዳዲስ አስተሳሰብ መግለጫ መድረኮች የሆኑት።
የዛሬው ዐብይ ጉዳይ ዓምዳችን “ማኅበራዊ ሚዲያዎች ፕሬሱን እየተኩ ነውን? ለተዘጉት አንደበቶችስ እንደለውጥ ድምፆች አገልግለው ይሆን?” የሚሉትን ጥያቄዎች ይፈትሻል። እግረ መንገዱንም ማኅበራዊ ሚዲያዎች ማኅበራዊ ችግሮቻችንን ተከፋፍለን እንድንሸከማቸው እንዴት እንዳገዙ ማሳያዎችን ያቀርባል።
ኢንተርኔትና ኢትዮጵያ
እንደ አንዳንድ መረጃዎች በኢትዮጵያ የበየነመረብ (ኢንተርኔት) ተጠቃሚዎች ቁጥር በተለይ ባለፉት ሁለት ዓመታት እጅግ ከፍተኛ በሆነ ቁጥር ጨምሯል፡፡ ከሦስት ዓመታት በፊት 500 ሺሕ የማይሞሉ ተጠቃሚዎች የነበሩት በይነመረብ ዛሬ እንደ መገናኛ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ደብረ ጽዮን ገ/ሚካኤል ገለጻ 2.5 ሚሊዮን ደርሷል፡፡ ሆኖም በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የግል ኮምፒዩተር ኖሯቸው ለኢንተርኔት ግልጋሎት በኢትዮ ቴሌኮም ደንበኝነት ከተመዘገቡት ኢትዮጵያውያን የላቀ ቁጥር ያላቸው ኢንተርኔት ካፌ ውስጥ የዚህ አገልግሎት ተጠቃሚዎች መሆናቸውን ጥናቶች ይጠቁማሉ። ጥንቃቄ የታከለበት ሰፊ ጥናት የሚጠይቅ ቢሆንም ቅሉ፤ሚሊዮኖች ኢትዮጵያውያን የበይነመረብ ተጠቃሚ ስለመሆናቸው ግን ‘ወርልድ ኢንርተኔት ስታትን’ ጨምሮ የተለያዩ መረጃዎች ያረጋግጣሉ፡፡
የሁሉም ገጸበረከት
በይነ መረብ /ኢንተርኔት/ ለሰው ልጆች ካበረከታቸው መልካም ዕድሎች መካከል አንዱ ማኅበራዊ ሚዲያ ነው፡፡ ማኅበራዊ ሚዲያ በመላው ዓለም ሰፊ የሆነ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ሌሎችም ለውጦች እንዲከሰቱ መንስኤ ለመሆን የቻለ፣ በሌላ ቋንቋ የዓለምን የመረጃ ቅርጽ እየለወጠ የሚገኝ ድንቅ የዘመኑ ቴክኖሎጂ ገፀ በረከት ነው፡፡ በኢትዮጵያ አዝጋሚ ቢሆንም ሕዝቡ የሱታፌው ተካፋይ እየሆነ ነው። ከሦስት ዓመታት በፊት ከ134 ሺሕ የማይበልጥ የነበረው የኢትዮጵያውያን የፌስቡክ አውታረ መረብ ተጠቃሚዎች ቁጥር የዓለም ሀገራትን የበይነመረብ ተጠቃሚነት በስፋት በመዳሰስ መረጃ በሚሰጠው ‘የሚኒዋትስ የጥናት ግሩፕ’ ሪፖርት መሠረት ከ902 ሺሕ እንደሚልቅ የተገለጸው በታኅሣሥ 2005 ዓ.ም ነው፡፡ በአሁኑ ወቅትም የዚህ የማኅበራዊ ሚዲያ ዓይነተኛ መገለጫ የሆነው ፌስቡክን የተቀላቀሉ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ወደ አንድ ሚሊዮን ገደማ እንደሚጠጋ ይገመታል፡፡ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተፅዕኖ የማሳደር አቅሙ እያደገ የመጣው ማኅበራዊ ሚዲያ በኢትዮጵያ ያለበትን ደረጃ ለመቃኘት የጦማርያንን፣ የቴክኖሎጂ ሙያተኞችን፣ በጥቅሉ የድረ ዜጎችን እና የሌሎችን ምሁራንን አስተያየት መካፈል ግድ ነው፡፡
የማኅበራዊ ሚዲያ ትንግርቶች
ማኅበራዊ ሚዲያ ሰፊ ተቀባይነትን ባገኘው ፌስቡክ ብቻ የተገደበ ባይሆንም፤ባለፈው ዓመት ጥቅምት ወር አንድ ቢሊዮን የሚጠጉ አባላትን ያሰባሰበውን ይህንኑ አውታረ መረብ የሚስተካከለው አልተገኘም፡፡ በአሁኑ ወቅት ትዊተር፣ ማይስፔስና ሊንክድኢንን ጨምሮ ከ500 በላይ ማኅበራዊ ሚዲያዎች እንዳሉ የተለያዩ ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ የጡመራ መድረክ (blog)፣ ዌኪስ (wikis)፣ የበየነ መረብ የውይይት መድረክ (Internet forums)፣ የድምፅና ምስል መጋሪያዎች (podcasts and Utube) ከማኅበራዊ ሚዲያ መገለጫዎች መካከል በጣም ጥቂቶች ናቸው፡፡
የማኅበራዊ ሚዲያ ‘አይ-አዎ’
በተለያዩ ወገኖች የማኅበራዊ ሚዲያ አሉታዊ እና አዎንታዊ ፋይዳ ሁሌም ቢሆን የጦፈ ክርክር እንዳስነሳ ነው፡፡ “ታማኝ የመረጃ ምንጭ ሊሆን አይችልም፤ ሰዎችን ለማታለል ሊውል ይችላል፤ ሰዎች በአካል እንዳይገናኙ እንቅፋት በመፍጠር ላልተገባ የሥነ ልቡና ቀውስ ይዳርጋል” ወዘተ. በማለት ማኅበራዊ ሚዲያው ላይ ያላቸውን ቅሬታ ከሚያሰሙት ጀምሮ አንድሪው ኪንን የመሳሰሉ ጸሐፊያን “The cult of the amateur writing” የሚል መጽሐፍ በማሳተም ማኅበራዊ ሚዲያውን በስፋት ተችተዋል፡፡ ማኅበራዊ ሚዲያን የሚተቹ ወገኖች እንደ ማስረጃ ከሚያወሷቸው ነጥቦች አንዱ በሜሪላንድ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰሮች ይፋ የሆነውንና “ማኅበራዊ ሚዲያን አዘወትሮ መጠቀም ሱስ ያስይዛል፡፡” የሚለውን ግኝት መሠረት ያደረገው ጥናት ነው፡፡ በተለይ በተመራማሪዎቹ ስም የወጣለት “FOMO” (fear of missing out) /በአማርኛው የመረሳት ፍርሃት/ ጥናቱ በተካሔደባቸው ብዙ ተማሪዎች ላይ መታየቱ የማኅበራዊ ሚዲያ አሉታዊ ጎን ጎልቶ እንዲታይ አድርጎታል፡፡
በአንጻሩ በርካቶች ማኅበራዊ ሚዲያን በእጅጉ በማወደስ የብዙ ለውጦች መንስኤ መሆኑን ያወሳሉ፡፡ “መድኃኒት አሉታዊ ጎኖች አሉት ተብሎ አልወስድም እንደማይባለው ሁሉ ማኅበራዊ ሚዲያም ከአጠቃቀም ጉድለት በሚያስከትለው ችግር ሳቢያ በደፈናው መወገዝ የለበትም፡፡” በማለት ይከራከራሉ፡፡
የተጋመሰው የጎርጎርሳውያኑ የዘመን ቀመር ሲገባደድ በመላው ዓለም የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ቁጥር ሁለት ቢሊዮን አካባቢ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ለዚህ ሁሉ ሕዝብ ሰፊ ጥቅምን ያበረክታል ተብሎ የሚጠበቀው ማኅበራዊ ሚዲያም “እልፍ” አዎንታዊ ፋይዳዎች ያሉት መሆኑን የተለያዩ ምሁራን ይጠቁማሉ፡፡ ሰዎች በነጻነት ሐሳባቸውን ለመግለጽ፤ የተደራጀ እንቅስቃሴን በቀላሉ ለማስተባበር፤ የተለያዩ ዕውቀቶችን ለማግኘት፣ የሥራም ሆነ ሌሎች መልካም ዕድሎቻቸውን ለማሳደግና፣ በጣም ጠቃሚ መረጃዎችን በፍጥነት ለመለዋወጥ ማኅበራዊ ሚዲያው የላቀ ጥቅም እንደሚሰጥ የሐርቫርድ፣ ጆን ሆፕኪንስ፣ ኮሎምቢያ እና ስታንፎርድ የመሳሰሉ የአሜሪካ ታላላቅ ዩኒቨርስቲዎች ምሁራንን አሳምኗል። ከዚህም ባሻገር ለተማሪዎቻቸው በማኅበራዊ ሚዲያ ዘላቂ ጥቅምን ሊያገኙ የሚችሉበትን ልዩ ኮርስ አዘጋጅተው የ”ምርጥ ሶሻል ሚዲያ ተሞክሮ” ትምህርትን እንዲሰጡ አድርጓቸዋል፡፡
ከሦስት ዓመት በፊት በሄይቲ የደረሰው እጅግ ከፍተኛ የሆነ የመሬት መናወጽ ለ220,000 ሰዎች ሞት እና 30 ሺሕ ሕንፃዎች መደርመስ ምክንያት ሆኖ እንደነበር ይታወሳል፡፡ በጊዜው የአሜሪካ ቀይ መስቀል ለዚህ ዘግናኝ አደጋ እርዳታ ለማሰባሰብ በማኅበራዊ ሚዲያ፣ በዋነኝነትም በትዊተር ባደረገው ቅስቀሳ በ24 ሰዓታት ብቻ ከ126 ሚሊዮን ዶላር በላይ ለማሰባሰብ በቅቷል፡፡ በግብጽ ለተከሰተው አብዮት ብሎም በዐረቡ ዓለም ለታየው መነሣሣትም ማኅበራዊ ሚዲያ በተለይ ፌስቡክና ትዊተር የላቀ ሚና መጫወታቸው ይታወሳል፡፡ በአሜሪካዋ ቦስተን ከተማ በቅርቡ የተካሔደውን የማራቶን ሩጫ መሠረት አድርጎ የተፈጸመውን የቦንብ ጥቃት አድራሾች ማንነት ለመለየት ከምንም በላይ የላቀ ሚና የተጫወተው የፍሎሪዳው ነዋሪ ዴቪድ ግሪን በማኅበራዊ ሚዲያ ያሠራጨው የፍንዳታውን ክስተት የሚያሳይ የሞባይል ፎቶ ነበር፡፡ ኤፍ ቢ አይም በሶሻል ሚዲያ የተገኘውን ፎቶ ‘የቦንብ ጥቃቱን አድራሾች ለመለየት ያስቻለ ምርጥ መረጃ’ ሲል ዕውቅና ሰጥቶታል፡፡ በዚህ መልኩ በመላው ዓለም ማኅበራዊ ሚዲያ በሰው ልጆች በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ሆነ ሌሎች የሕይወት መስተጋብሮች ውስጥ አቻ የሌለው ሚና በመጫወት ላይ ይገኛል፡፡
ነገረ ፌስቡክ በኢትዮጵያ
ፌስቡክ ከማኅበራዊ ሚዲያዎች ዋነኛው ነው፡፡ ኤሪክ ኩልማን የተባሉት የቴክኖሎጂ ጸሐፊ “ፌስቡክ ሀገር ቢሆን ኖሮ ሦስተኛው የምድራችን ትልቁ ሀገር በሆነ ነበር፡፡” በማለት ፌስቡክን ያካተታቸውን ሕዝቦች ብዛትና በሰው ልጆች ላይ ለማሳደር የቻለውን ተጽዕኖ በአጭሩ አውስተዋል፡፡ በኢትዮጵያም ይህ ማኅበራዊ ሚዲያ ለተለያዩ ኩነቶች በጥቅም ላይ እየዋለ ነው፡፡ ሕይወት ወንድምአገኝ በፌስቡክ ላይ የተለያዩ ሓሳቦችን በመሰንዘር ትታወቃለች፡፡ አንድ ቀን ምሽት ሕይወት አልጋዋ ውስጥ ሆና ዝናቡ ይዘንባል፡፡ ሁለት ብርድ ልብስ ብትለብስም ቅዝቃዜውን መቋቋም አቅቷት ጋቢ ደረበች፡፡ በድንገት በዚያ የምሽት ዝናብ በየመንገዱ የተቀዳደዱ ልብሶችን ለብሰው ለብርድ የተዳረጉ ሰዎች ወደአዕምሮዋ መጡ፡፡ ይሄኔም ሕይወት ካላት ልብሶች ለእነዚህ ወገኖች ልታካፍል ወሰነች፡፡ ነገር ግን የእርሷ ብቻ አስተዋጽዖ በቂ አለመሆኑን በማሰብ የቻሉ ሰዎች ያገለገሉ ጫማዎችንና አልባሳትንም ቢሆን እንዲለግሱ በፌስቡክ ገጿ ላይ ጥያቄ አቀረበች፡፡ በእርሷ ጥያቄ በርካቶች ስለተስማሙ ከሁለት ሳምንት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ከ335 በላይ ለሚሆኑ ችግረኛ ተማሪዎች እና በጎዳና ላይ ለሚኖሩ ሰዎች ልብስን እና ጫማ ለመለገስ ተቻለ፡፡ ባሕር ማዶ ያሉ የፌስ ቡክ ጓደኞቿም ‘እኛ ልብስ መላክ ባንችልም ብር መላክ ይቻለናል’ በማለት የአቅማቸውን ረዷት፡፡ “ወደ 11 ሺሕ ብር እጃችን ላይ ነበር፡፡ በዚህ ብርም ከ35 ለሚልቁ ለደጃዝማች ዑመር ሰመተር ተማሪዎች አዳዲስ ዩኒፎርም፤ አዲስ ጫማና ቅያሬ ሹራብ ገዝተን አስረከብን፡፡” በማለት በአጭር ቀናት ውስጥ በፌስቡክ አማካኝነት ለማሳካት የቻለችውን ፋይዳ ያለው ማኅበራዊ ሓላፊነት ተናግራለች፡፡
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በፖለቲካ ሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪ ያገኘችውና ሁለተኛ ዲግሪዋን በዓለም አቀፍ ግንኙነት የሠራችው ሕይወት ወንድምአገኝ ማኅበራዊ ሚዲያ እንዲህ ላለ በጎ ሐሳብ ጭምር ከፍ ያለ ጠቀሜታ ማበርከት እንደሚቻልበት ትናገራለች፡፡
ኢዮብ ምሕረተአብ በማኅበራዊ ሚዲያ ሰፊ እንቅስቃሴን ከሚያደርጉ የበይነመረብ ተጠቃሚዎች መካከል ይደመራል፡፡ በፌስቡክ ለበጎ ምግባር የተነሳሳበትን አጋጣሚ እንዲህ ሲል ያወሳል፡፡ ‹‹ሁል ግዜ ባገኘሁት ቁጥር አንድ ብር የምሰጠው የአእምሮ ውስንነት ያለበት የኔ ቢጤ አለ፡፡ ብሩን ሲቀበለኝ መንጭቆ ነው፡፡ ቀና ብሎም በቅጡ አያየኝም፤ እኔም ቅር አይለኝም፡፡ ለረጅም ግዜ ከአዲስ አበባ ውጪ ቆይቼ ስመለስ ግን ለዚሁ ሰው እንደተለመደው አንድ ብር ሰጠሁት፡፡ ይሄኔም ቀና ብሎ አየኝና “ጠፋህ በሰላም ነው?” አለኝ ደንግጬ “ሰላም ነኝ” አልኩት፡፡ አሁንም እደጋገመ “ጤናህ ግን ደህና ነው ወይ? በጣም ጠፋህ እኮ?” አለኝ… በዚህ ነገር ልቤ ተነካ! ከተቻለና ፈቃደኛ ከሆነ አማኑኤል ሆስፒታል ወስጄ ላሳክመው፤ ካልሆነም ብርድ ልብስና ለዝናብ ጊዜ የሚሆን የላስቲክ ልብስ ልስጠው ብዬ አሰብኩኝ፡፡” ይላል። ይሄን ክስተት ተከትሎ ኢዮብ ፌስቡክ ላይ ላሉ ጓደኞቹ ጉዳዩን በመግለጽ “የአሥር ብር የሞባይል ካርድ ቁጥር በፌስቡክ ሳጥኔ ላኩልኝ” አላቸው፡፡ ያገኘው ምላሽ ከጠበቀው በላይ ነበር፡፡ ከሀገር ውጪ ያሉ ጓደኞቹ ሁሉ “ብር በኋላ እንላክልህ” ብለውት እንደነበርና ደግነታቸው ከብዶት እንደማይፈልግ ቢያሳውቃቸውም አንዲት ጂዳ የምትኖር ልጅ ግን በግድ 500 ብር እንደላከችለት ይናገራል። “ፌስቡክ በዚህ ሁኔታ በቀላሉ አንድ ሰው መርዳት ያስቻለኝን በጎ ሥራ እንዳከናውን አድርጎኛል” ብሏል።
የፌስቡክ ዘመቻዎች
በሀገራችን ውስጥ በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሕገ መንግሥቱ የተፈቀደው የተቃውሞ ሰልፍ የማድረግ መብት በእጅጉ ተሸርሽሮ ተግባራዊ መሆን አልቻለም። ከወራት በፊት በጣሊያን ሀገር ለግራዚያኒ የቆመውን ሐውልትና ሙዚየም በመቃወም ለተቃውሞ የወጡ ዜጎች አላግባብ መታሰራቸውና በዋስ መለቀቃቸው ይታወሳል፡፡ ራሱን “ዞን 9” ብሎ የሚጠራው የአራማጆች (አክቲቪስት) እና ጦማሪዎች (ብሎገር) ኢ-መደበኛ ቡድንም “የሰላማዊ ሰልፍ መብት ይከበር” በሚል መርሕ ሦስተኛውን የበየነ መረብ ዘመቻ (ካምፔይን) አካሂዷል፡፡ ይህኛው የዞን ዘጠኝ አራማጆች እና ጦማሪዎች ዘመቻ በሀገር ውስጥ እና በውጭ በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ያሳተፈ ሲሆን አልጀዚራን የመሳሰሉ ሚዲያዎችንም ቀልብ ለመግዛት በቅቷል፡፡ ይህ ቡድን ከዚህ ቀደም ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት ይከበር እና ሕገመንግሥቱ ይከበር የሚሉ በከፍተኛ ቁጥር የፌስቡክ ተጠቃሚዎች የተሳተፉባቸው ሁለት ዘመቻዎችንም አካሂዶም ነበር።
በግል ተነሳሽነትን ከ335 በላይ ሰዎችን ለማልበስ ያስቻለው የሕይወት ወንድማገኝ የማኅበራዊ ሚዲያ በጎ አድራጎትም ሆነ የዞን ዘጠኞች የሠላማዊ መብት ይከበር ሦስተኛ ዘመቻ በሀገራችን በአሁኑ ወቅት ያለውን የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም ከእንቶፈንቶ ወደቁም ነገርና የጋራ ጉዳይ መሸጋገሩን ለማሳየት ጥቂቱ ምሳሌ ነው፡፡
‘የዞን ዘጠኝ’ ትግሎች
ዞን ዘጠኝ ለሀገራቸው ጉዳይ ተቆሪቋሪ በሆኑ ዘመኝ ወጣቶች የተመሠረተ ነው፡፡ በቅርቡ አንደኛ ዓመቱን ያከበረው ይህ የአራማጆች እና ጦማሪዎች ኢ-መደበኛ ቡድን ማኅበራዊ ሚዲያን ለፖለቲካ፣ ለማኅበራዊ፣ ለስፖርትም ሆነ ሌሎች ዘርፎች በሚገባ በማዋል እንደ ዓይነተኛ ምሳሌ ሊጠቀስ የሚችል ነው፡፡ የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በምጣኔ ሀብት ላገኘው ኤርሚያስ ታዬ “ዞን ዘጠኝ የፌስ ቡክ አዋዋሌን (አጠቃቀሜን) በጥሞና እንዳስብበት እና ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው ጉዳዮች ላይ እንዳተኩር ያደረገኝ ልዩ ስብስብ ነው፡፡” በማለት አድናቆቱን ሲገልጽላቸው በአንድ መንግሥታዊ ያልሆነ ተቋም ውስጥ ፕሮጀክት ማናጀር ሆና የምትሠራው ኢየሩሳሌም በበኩሏ ‘ወጣቱ ለሀገሩ አያስብም ሱሰኛ ነው’ እየተባለ በሚወነጀልበት በዚህ ወቅት በራስ ተነሳሽነት በተለይ ፖለቲካዊ ርእሶችን በጡመራ መድረካቸው ያለፍርሃት በማንሣት ለውይይት ማቅረባቸው ያስመሰግናቸዋል ትላለች፡፡
የዞን ዘጠኝ አባላት በቀዳሚነት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከኢ- መደበኛ ቡድኑ አባላትም ሆነ ሌሎች ጸሐፍት የደረሳቸውን መረጃዎችና ጽሑፎች በኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይታይ በታገደው ጦማራቸው በየጊዜው ያቀርባሉ፡፡ ከዚህ ውጪም በየሦስት ወሩ የበየነ መረብ ላይ ዘመቻን በማካሔድ የአራማጅነት ሥራ እያከናወኑ ይገኛሉ፡፡ ይህ ቡድን በተመሠረተ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥም በፖለቲካ፣ በማኅበራዊ፣ በምጣኔ ሀብት፣ በትምህርት፣ በመጻሕፍት፣ በሃይማኖት እና በሌሎችም ጉዳዮች ዙሪያ በድምሩ ከ150 በላይ ሰፊ ትንታኔ የታከለባቸው ጽሑፎችን ለንባብ አብቅቷል፡፡ በዞን ዘጠኝ ድረ ዓምባም ሆነ በአባላቱ የፌስቡክ ገጽ ላይ የተለቀቁትን መረጃዎች በአማካይ ከ300 ሺሕ በላይ ሰዎች ጋር ለመድረስ የቻለ ነበር፡፡
ከዞን ዘጠኝ አባላት መካከል አንዷ የሆነችው ማኅሌት ፋንታሁን ከአዋሳ ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ ተመርቃ ሥራ ላይ ትገኛለች፡፡ “በዞን ዘጠኝ ውስጥ የተሰባሰብነው አባላት ከተለያዩ የትምህርትና የሙያ ዘርፎች የተውጣጣን በመሆናችን አንዳችን ከሌላችን የተማማርነው ብዙ ነገር አለ፡፡ በተለይ በግሌ የማላውቀውን ለማወቅ፣ የማልችለውን ለመቻል ምን ማድረግ እንዳለብኝ ተረድቻለሁ፡፡” ትላለች።
ጆማኔክስ ካሣዬ የተባለው ሌላኛው የዞን ዘጠኝ መሥራች በበኩሉ ‹‹ዞን ዘጠኝ በግሌ ምናባዊ የነበረውን ነገር መሬት ላይ እንዳወርደው፣ እንዲሁም በፍርሐት በተጠፈርንበት ሰዓት ከሚደፍሩ ልበ ሙሉዎች ጋር አንድ መሆን፣ ከምንም በላይ ከማንም ጋር ካልወገኑ ነገር ግን ያገባኛል ባዮች ጋር መጎዳኘቴና ይሄም የእኛ ስሜት ወደሌሎች እንዲጋባ ማድረግ መቻሌ ያስደስተኛል” ብሏል።
ሁለተኛ ዲግሪውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዓለም አቀፍ ሕግ በመሥራት ላይ የሚገኘው ሌላኛው የዞን ዘጠኝ አባል ዘላለም ክብረት በበኩሉ “የዞን ዘጠኝ አባል በመሆኔ ሐሳቤን በተደራጀ መንገድ የምገልጽበት መድረክ አግኝቻለሁ፡፡ በተጨማሪም ከቡድኑ አባላት ጋር በማደርገው ውይይት ሐሳቤን አዳብር ዘንድ አግዞኛል” በማለት ያገኘውን ጥቅም ይገልጻል፡፡
የዞን ዘጠኝ እና ሌሎችም ጦማሮች መታገድ
የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ባገኙ እና በመሥራት ላይ በሚገኙ ወጣቶች የተመሠረተው ዞን ዘጠኝ በተቻለ አቅም ጽንፍ የያዙ ሐሳቦችን ላለማስተናገድ ጥረት ቢያደርግም በሀገር ውስጥ እንዳይታይ መታገዱ (block) መደረጉ አልቀረም፡፡ ማኅሌት ፋንታሁን “መንግሥት በሀገራችን እንዲዘጉ የሚያደርጋቸው ብሎጎች ወይም ድረ ዓምባዎች በፖለቲካ ጉዳይ ላይ ብቻ የሚያተኩሩ ናቸው፡፡ ይህ መሆኑም መንግሥት የሀገራችን ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ማኅበረሰቡ በነጻነት እንዲወያይ፣ መረጃ እንዲያገኝና ብሎም እንዲያካፍል አለመፈለጉን ያሳያል፡፡” በማለት ሐሳቧን ስትገልጽ ጆማኔክስ በበኩሉ “በራስ ፍቅር መውደቅ በራስ ብቅል እንደመስከር ነው፡፡ በፕሮፓጋንዳ ከሚያደነቁረው ኢቴቪ ውጭ እንዳይታይና እንዳይሰማ ማድረግ ሕዝብን ከመናቅና በራስ ካለመተማመን የሚመነጭ ነው፡፡” በማለት የመንግሥትን እርምጃ ይኮንናል፡፡ ሌላኛው የቡድኑ አባል ዘላለም ደግሞ “ጦማራችን መዘጋቱ በሀገር ውስጥ ያለንን ተደራሽነት በጣም እንዲቀንስ አድርጎታል፡፡” በማለት የዕገዳውን ቅጽበታዊ ውጤት ካወሳ በኋላ በተለይ በመንግሥት በኩል ድረ ገጾችንና የጡመራ መድረኮችን በምን መልኩ እንደሚዘጋ ግልጽ ፖሊሲ የሌለው መሆኑ “እስከ አሁን ድረስ ወደ አምስት የሚጠጉ የቡድኑ የጡመራ መድረኮች ተዘግተዋል፡፡” በማለት ቅሬታውን ይገልጻል፡፡
በሕግ ሁለተኛ ዲግሪውን የሚሠራው ዳንኤል ብርሃነ የተባለ ጦማሪ ደግሞ ‹‹በየትም ሀገር የጡመራ መድረክን መዝጋት የተለመደ ነው፡፡ የእኛ ሀገሩን የተለየ የሚያደርገው ዘጊው አካል በግልጽ አለመታወቁ ነው፡፡››በማለት ከጡመራ መድረኮቹ መታገድ ይልቅ አዘጋጉ አሳሳቢ መሆኑን ያወሳል፡፡ ለአብርሃም ደስታ ግን የጡመራ መድረኮችን ማገድ ዜጎችን ማፈን ነው፡፡
የ ‘ድምፃችን ይሰማ’ ድምፆች
muslim1ድምፃችን ይሰማ የተሰኘው የፌስቡክ ቡድን በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በበርካታ ክፍለ ሀገራት እና በውጭ ሀገራትም ጭምር ከ20 በላይ ቡድኖች አሉት፡፡ የቡድኑ አባላት “ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የመንግሥትን የሃይማኖት ጣልቃ ገብነትን የምንቃወምበት ድምፅ” በሚል የሚገልጹት ይህ የፌስቡክ ገጽ ከተመሠረተ ከአንድ ዓመት በላይ ሲሆነው፤ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ እንቅስቃሴ ጋር የተያያዙ ሰፊ መረጃዎች እየቀረቡበት ይገኛል፡፡ የተጀመረው የሰላማዊ ተቃውሞ እንቅስቃሴ መረጃዎችና ትእዛዛት በፌስቡክ የሚተላለፉ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በተለይ በክልሎች ሰፊ ቅርንጫፎች አፍርቷል። ድምፃችን ይሰማ ከወልዲያ፣ ድምፃችን ይሰማ ከጅማ አባጅፋር፣ ድምፃችን ይሰማ ከመቂ በሚሉት የፌስቡክ መለያዎች ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በሠላማዊ መንገድ ድምፃቸውን በስፋት በማሰማት ላይ ናቸው መሆናቸውን ይገልጻል፡፡ የቡድኑን አባላት በፌስቡክ ገጻቸው አማካኝነት ለማናገር ያደረግነው ሙከራ ሊሳካልን አልቻለም፡፡ ይሁን እንጂ የቡድኑ እንቅስቃሴ ግን በማኅበራዊ ሚዲያ ለሚካሔዱ የአራማጅነት እንቅስቃሴ ዓይነተኛ ማሳያ ተደርጎ ሊወሳ የሚችል ነው፡፡
ፌስ ቡክ ከእንቶፈንቶ ወደ ቁምነገር
ዳንኤል ብርሃነ የሶሻል ሚዲያ ዋናው ፋይዳ በሀገራችን የሌለውን የመወያየት ባሕል ለማሳደግ መርዳት ነው ይላል፡፡ “በእኛ ሀገር በእኩልነት ላይ የተመሠረተ ዲሞክራሲያዊ መስተጋብር የለም። በሶሻል ሚዲያ አማካኝነት ግን አንድ ተራ የሃይስኩል ተማሪ ትልቅ ማኅበራዊ ቦታ ከሚሰጠው ሰው ጋር በእኩልነት ሲመላለስ ታያለህ፡፡” በማለት በሶሻል ሚዲያው አማካኝነት የመጣውን አዲስ የውይይት ዕድል ይጠቁማል። ‘አንተ አታውቅም ዝም በል’ የሚል ዓይነት ያልተገባ አካሔድ ባለበት ማኅበረሰብ እንዲህ ዓይነቶቹን አካሔዶች በመግታት የባሕል ለውጥ ለማምጣት ማኅበራዊ ሚዲያ የላቀ ሚናን ለመጫወት እንደሚችልም ይናገራል፡፡
አብርሃ ደስታ በመቀሌ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በደቡብ አፍሪካ ዩንቨርስቲ (ዩኒሳ) የሦስተኛ ዲግሪውን (ፒኤች ዲ) እየተከታተለ የሚገኘው አብርሃ በተለይ ህወሓትን በፌስቡክ ገጹ በመተቸት ይታወቃል፡፡ “እኔ ፌስ ቡክን ከመቀላቀሌም በፊት በተለያዩ ስብሰባዎች ላይ የማነሳው ለየት ያለ ሐሳብ አይወደድም ነበር፡፡” በማለት የፌስቡክ ተጠቃሚ ስለሆነ ብቻ በመንግሥት ላይ የተቃውሞ ሐሳቦችን መሰንዘር እንዳልጀመረ የሚናገረው አብርሃ “የማነሳቸው ሐሳቦች የተለዩ በመሆናቸው በውድድር ለጓደኞቼ የሚሰጠውን ዕድልን እኔ ስነፈግ ቆይቻለሁ” ይላል። በፌስቡክ መለያው የሚያንጸባርቃቸው ሐሳቦችም ከዚሁ እውነታ ጋር የተያያዙ መሆናቸውን ይናገራል፡፡ በግሉ ሶሻል ሚዲያው የፈጠረለትን ዕድል ሲያወሳም “እኔ በፖለቲካ ስብሰባ ላይ የማነሳቸው ሐሳቦችን ስለማይወደዱ የመናገር ዕድል እንኳን አይሰጠኝም፡፡ ከዚህ ባለፈም የተለየ ሐሳብ በማንጸባረቄም ‘ተማሪዎችን ያበላሻል’ እየተባልኩ እወቀሳለሁ፡፡ አሁን ግን ያመንኩበትን ሐሳብ የማንንም ፍቃድ መጠየቅ ሳያስፈልገኝ በሶሻል ሚዲያው በነጻነት ለማራመድ ችያለሁ፡፡” ይላል።
የዞን ዘጠኝ አባሏ ማኅሌት በበኩሏም “ማኅበረሰቡ ከሚነቃባቸው መንገዶች አንዱ ሐሳብን መግለጽ እና መወያየት መቻል እንዲሁም መረጃን በወቅቱ ማግኘት ነው፡፡ በሃገራችን ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች በተለያዩ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ እንዲወያዩና ሃሳባቸውን መግለፅ እንዲችሉ አድርጓል፡፡ በተጨማሪም መረጃዎችን በፍጥነት ለኅብረተሰብ በማድረስ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡” በማለት የማኅበራዊ ሚዲያ ጥቅምን ትገልፃለች፡፡
ዘላለም በበኩሉ “ማኅበራዊ ሚዲያ በራሱ ለውጡን ካለበት ይዞልን ይመጣል ማለት ከባድ ቢሆንም እንደ የለውጥ መድረክነት በመሆን ግን ትልቅ አስተዋፅዖ ይኖረዋል ብዬ አስባለሁ፡፡” በማለት የማኅበራዊ ሚዲያውን የለውጥ እርሾነት ይናገራል፡፡ “የተለያዩ የፖለቲካ ጉዳዮችና ብዙ የፖለቲካው ተዋናዮች ፌስቡክን በመሳሰሉ የማኅበራዊ ሚዲያዎች በብዛት መታየታቸውና ንቁ ተሳትፎ ማድረጋቸው ሚዲያው የለውጡ አጋዥ መድረክ በመሆን እንዲያገለገል አድርጎታል የሚል እምነት አለኝ፡፡” ብሏል።
“የመንግሥት እርምጃ አፈና ነው”
በኢትዮጵያ በየነ መረብ ላይ ያለውን የመንግሥት ቁጥጥር በስፋት ያጠናው “ኦፕን ኔት” የተባለው መንግሥታዊ ያልሆነ ተቋም በተለይ ፖለቲካዊ ሐሳቦችን በበይነ መረብ መግለፅ በሀገሪቱ ውስጥ በስፋት የሚገደብ መሆኑን ያትታል፡፡ ኦፕን ኔት ኢኒሺየቲቭ በመስከረም ወር ለጥናቱ ተሳታፊ ፍቃደኞች በልዩ ሁኔታ የተዘጋጁ ሶፍትዌሮች በማከፋፈል ባደረገው ጥልቅና ቴክኒካዊ ተግባራዊ ጥናት በኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ድረ ዓምባዎች ሆን ተብለው እንዲዘጉ መደረጋቸውን ደርሶበታል፡፡ በተለይ እንደ ethiox.com ያሉ ነፃ ሐሳቦችን የሚያንሸራሽሩ ድረ ዓምባዎች መዘጋታቸው ይህን ተቋም በእጅጉ ማስገረሙ አልቀረም፡፡
የግንቦት 7 አባላት ፎቶዎች ለስለላ ሶፍትዌሮች
ginbot 7የኢትዮጵያን መንግሥት በበየነ መረብ ነፃነት ረገድ ክፉኛ እያሳማ ያለው ጉዳይ የተለያዩ የፖለቲካ አስተያየት መሰንዘሪያ የሆኑትን የጡመራ መድረኮችና ድረ ዓምባዎችን መዝጋቱ ብቻ ሳይሆን ባልተጠበቀ መልኩ የግንቦት 7 አባላትን ፎቶዎች በመጠቀም የስለላ ሶፍትዌር (ስፓይዌር) በበየነ መረብ ተጠቃሚ ሰዎች ኮምፒዩተር ላይ በድብቅ ያስቀምጣል ይባላል፡፡ ‘Finspy’ የሚል መጠሪያ ያለው የስለላ ሶፍትዌር በኢትዮጵያ በጥቅም ላይ መዋሉን ይፋ ያደረገው “ሲቲዝን ላብ” የተሰኘው ተቋም ነው፡፡ ነገር ግን በኢትዮጵያ በኩል እንዲህ ዓይነቱ ሶፍትዌር አለመገዛቱ በተደጋጋሚ እየተነገረ ነው፡፡ በጀርመን ሀገር የሚሠራውን ይህንኑ ሶፍትዌር የተቃዋሚ ድምፆችን ለማዘጋት ሆን ተብሎ በጥቅም ላይ መዋሉን የሚናገሩት ቶሮንቶ እና በርክሌይን በመሳሰሉ ታላላቅ ዩኒቨርስቲዎች የሚገኙ ምሁራን ግን ድርጊቱን በጽኑ አውግዘውታል፡፡
በማኅበራዊ ሚዲያ ለውጥ ይመጣ ይሆን?
በሀገራችን የማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ከፍ እያለ መምጣቱ እሙን ነው፡፡ ነገር ግን ማኅበራዊ ሚዲያ ምን ዓይነት ለውጥን ሊያመጣ ይችላል የሚለው ጥያቄ አነጋጋሪ ነው፡፡ ዳንኤል ብርሃነ ‹‹በማኅበራዊ ሚዲያ የሚከሰቱ ለውጦች አሉ፡፡ ነገር ግን እንደ ግብጽ ዓይነት አብዮት በኢትዮጵያ በጭራሽ የሚሆን አይደለም፡፡›› ሲል ይደመድማል፡፡ ማኅሌት ፋንታሁን በበኩሏ ‹‹ማኅበራዊ ሚዲያ በእርግጥም ለውጥ ያመጣል ብዬ አምናለሁ፡፡ እስካሁን የተጠቃሚው ቁጥር አነስተኛ ቢሆንም የተለያዩ ሐሳቦች እየተነሡ እየተንሸራሸሩበትና መረጃዎችም እየተሰራጩበት ነው፡፡ ወደፊት ደግሞ የተጠቃሚው ቁጥር ሲበዛ አሁን ከምናየው የበለጠ የነቃ ማኅበረሰብ መፈጠሩ አይቀሬ በመሆኑ ለውጥ ይኖራል፡፡›› ትለለች፡፡ ጆማኔክስ በበኩሉ ‹‹ከነውጣ ውረዱም ቢሆን በማኅበራዊ ሚዲያ ለውጥ ማምጣት ይቻላል፡፡›› ሲል ይደመድማል፡፡ ‹‹ፌስቡክን ጨምሮ ሌሎች ማኅበራዊ ሚዲያዎች እንደ ተወስኦ መድረክ (Discourse Sphere) በመሆን የለውጡ አካል መሆን እንደሚችሉ አስባለሁ፡፡ ነገር ግን የኢንተርኔት ተጠቃሚነት (Internet Penetration) ደካማ መሆን የዚህ ለውጥ ዋነኛ ማነቆ ሊሆን ይችላል፡፡›› በማለት ሐሳቡን የሚገልጸው ዘላለም በበኩሉ ‹‹አሁን ካለው ትንሽ የተጠቃሚነት ቁጥር ላይ መንግሥት ያለምንም ግልጽ ፖሊሲ ድረ አምባዎችንና ጦማሮችን ሲብስም ማኅበራዊ ድረ ገጾችን መዝጋቱ የለውጡን ሂደት እጅግ ያከብደዋል፡፡ ነገር ግን የማኅበራዊ ሚዲያዎች ተጠቃሚ ቁጥር እየጨመረ መምጣት ሰዎች በተለያየ መንገድ ሐሳባቸውን የሚገልጹበት ሁኔታ በመፍጠሩ ብሎክ በማድረግ ሐሳብን ማሰርና ለውጥንም ማዘግየት እንደማይቻል እያሳየ ነው፡፡›› ሲል ሐሳቡን ደምድሟል፡፡
ማኅበራዊ ሚዲያው የመተንፈሻ ቀዳዳ በመሆን ፕሬሱን እየተካው ነው የሚለው የሚዲያ ባለሙያው መስፍን ኅሩይ “በሀገሪቱ የሚታተሙ ጋዜጦችና መጽሔቶች በመንግሥት ጫናና በኅትመት ዋጋ ውድነት ከገበያው ሲወጡ አዘጋጆቹን ጨምሮ ብዙዎቹ በዚያ ያጡትን መድረክ በማኅበራዊ ሚዲያው በማግኘት በተሻለ ተደራሽነት ስሜታቸውን እንዲገልጹ አስችሏቸዋል” ብሏል። እንደመስፍን ገለጻ መንግሥት ጠንከር ያሉ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾችን እየተከታተለ መዝጋቱ የምትከፈተዋን ማንኛዋንም የመተንፈሻ ቀዳዳ በመድፈን ውጥረቱን ከማባባስና ከማፈንዳት በተለየ የሚያመጣለት ጥቅም የለም” ይላል።
በማኅበራዊ ሚዲያ አማካኝነት በሀገሪቱ በልማት፣ በማኅበራዊም ይሁን በፖለቲካ ረገድ በጎ ለውጦችን ማምጣት ይቻላል፡፡ አሁን አሁን የእነዚህ ለውጦች ምልክቶች በአደባባይ እየታዩ ነው፡፡ ይሄን መልካም ዕድል በሚገባ ለመጠቀም በነጻ ሐሳብ መንሸራሸር የሚያምን መንግሥት ያስፈልጋል፡፡ እንዲያ ካልሆነ ግን የተገፉት የለውጥ ድምፆች የመጨረሻ ማረፊያቸው አይታወቅም፡፡

↧

“ጦርነት እንኳን ገና በልቶ ላልጠገበ ሕዝብና ለጥጋበኞቹም አይመችም” ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም

$
0
0

ከሰሞኑ መነጋገሪያ እየሆነ የመጣው የግብጽና የኢትዮጵያ በአባይ ጉዳይ እየተሰጣጡ ባለው እሰጥ አገባ ዙሪያ ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም በፌስቡክ ገጻቸው ላይ እንዲህ ብለዋል፦
“ጦርነት እንኳን ገና በልቶ ላልጠገበ ሕዝብና ለጥጋበኞቹም አይመችም፤ የተራበ ሕዝብ በጠገቡ መሪዎች ሲነዳ ግን ጦርነት ለአጉል ጀብደኛነት ዝና የሚጠቅም መስሎ ይታያቸዋል፤ ከኤርትራ ጋር ጦርነት ለመግጠም በሚያሰፈስፉበት ጊዜ በርቱ እያሉ የሚያቅራሩ ሞልተው ነበር፤ ዛሬ አቀራሪዎቹም ሆኑ ጀብደኖቹ በኤርትራ ጦርነት ያለቀባሪ Pro Mesfinስለቀሩት ሰዎች፣ ጠዋሪ ስላጡ እናቶችና አባቶች፣ አሳዳጊ ስለሌላቸው ልጆችና አካለ-ጎደሎ ለሆኑት የሚያስብላቸው አለ ወይ? የአቡነ ጴጥሮስ ሐውልት መነሣትና በኢጣልያ የግራዚያኒ ሐውልት እንዳይሠራ የተጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ ከልክሎ ለሰልፍ የወጡትን አስሮ ያሳደረ አገዛዝ ለአገራቸው ለሞቱት ኢትዮጵያውያን የሚሰጠውን ዋጋ በመጠኑም ቢሆን ያሳያል፤ ስለዚህም ኢትዮጵያውያን አገራቸውን ሲወዱ ራሳቸው በልጽገው ለልጆቻቸው ብልጽግናን እንዲያወርሱ ሕይወታቸውን ቢጠብቁ ለአገራቸውም ክብር ይሆናሉ፡፡

ለፍቅር መተዋወቅ እንደሚያስፈልግ ሁሉ ለጠብም መተዋወቅ ያስፈልጋል፤ የተሟላ መረጃ ቢኖረን የጥንት ታሪክ እየጠቀስን ሰዎችን ለጦርነት እንቀሰቅስም ነበር ብዬ አምናለሁ፤ ስለዚህም አንዳንድ አስፈላጊ መረጃዎችን ላቅርብ፤ —

1. የግብጽ የጦር ኃይል በዓለም አሥረኛ ነው፣ በአፍሪካና በመሀከለኛው ምሥራቅ የሚወዳደረው የለም፤ አንድ ሚልዮን ተኩል ያህል የጦር ኃይል አለው፤ በዓየር ኃይልም ከዓለም አሥራ አራተኛ ነው፤ በታንክ ብዛት አራተኛ ነው፤ በባሕር ኃይል ሰባተኛ ነው፤ በጦር በጀት አርባ ሦስተኛ ነው፤
2. በኢትዮጵያ ዙሪያ ጂቡቲ፣ ሶማልያ፣ ሱዳን የአረብ ማኅበር አባሎች በመሆናቸው ለግብጽ ማኅበረተኞች ናቸው፤ በወያኔ ፈቃድ የተገፋችው ኤርትራም የዚሁ ማኅበር ታዛቢ አባል ነች፤ ከቀይ ባሕር ማዶ ያሉት አገሮች ሁሉ ሀብታሙንና ኃይለኛውን ሳኡዲ አረብያንም ጨምሮ የግብጽ ማኅበርተኞች ናቸው፤ በዚህ ሁሉ መሀከል የተከታተፈች ኢትዮጵያ ብቻዋን ነች፤
3. የቤንዚን ሀብትና ከሀብቱም ጋር የሚገኘውን ወዳጅና ጡንቻ አንርሳ፤

ይህ ማስታወሻ ለማስፈራራት አይደለም፤ ማስፈራራትን አላውቅበትም፤ እንዲያውም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ‹‹አትፍሩ›› ብሏቸዋል ተብዬ ተከስሼ ታስሬአለሁ፤ ስለዚህ አላስፈራራም፤ ጦርነት ከመጣብን ልናስቀረው እንሞክር፤ ሌላው ቢቀር እንድንዘጋጅ ጊዜ እናገኛለን፤ ገፍቶ ከመጣ ግን እንቋቋመዋለን፤ ለጦርነት አንቸኩል፤ ለኤርትራም ጊዜ ተናግሬ ነበር፤ የሰማኝ የለም፤ ጥጋብ ላይ ያሉ የሚርባቸው ዝና ነው፤ የሚያገኙት ግን ውርደትን ነው፡፡”

↧
Viewing all 13695 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>