Quantcast
Channel: Amharic News & Opinion
Viewing all 13695 articles
Browse latest View live

ጋዜጦች ባሳለፍነው ሳምንት

$
0
0
ኢትዮ-ምኅዳር ማክሰኞ ነሐሴ 8/2005 ዓ.ም
  • በእነ ኤልያስ ክፍሌ መዝገብ በሽብርተኝነት ክስ ተፈርዶባቸው በማረሚያ ቤት ከሚገኙት አራቱ ኢትዮጵያውያን መካከል ይቅርታ ጠይቀው የነበሩት ሶስቱ፤ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣ ወ/ሮ ሂሩት ክፍሌ እና አቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር፤ ጥያቄያቸው ከቀረበ ከአንድ ዓመት ቆይታ በኋላ ሐምሌ 25/2005ዓ.ም የይቅርታ ቦርድ ጽ/ቤት ማህተም አርፎበት ለወ/ሮ ሂሩት ክፍሌ በተላከ ደብዳቤ የይቅርታ ጥያቄቸው ለፕሬዝዳንቱ ቀርቦ ውድቅ መደረጉን እንደተገለፃለቸው ነገር ግን የጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ እና የአቶ ዘሪሁም ገ/እግዚአብሔር ግን ምላሽ እንዳልደረሳቸው
  • የአምስት ፓርቲዎች ጥምረት የሆነው የኢትዮጵያ ፌደራላዊ አንድነት መድረክ ቅዳሜ ነሐሴ 1 ቀን 2004ዓ.ም ባካሄደው ጉባዔ ዶ/ር መራራ ጉዲናን ሊቀመንበር አድርጎ መምረጡን እና ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት መድረክን እንደሚመሩ
  • አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የፀረ ሽብር ህጉን እንዲሰረዝ የሚያካሂደውን የ3ወር የሚሊዮኖች የነፃነት ድምፅ ንቅናቄ የመጀመሪያው ምዕራፍ ማጠናቀቂያ አስመልክቶ መስከረም 5 ቀን 2006ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ሊያደርግ እንዳቀደ
  • ሁለት የሬድዮ ቢላል ጋዜጠኞች ክስ ሳይመሰረትባቸው ከሣምንት በላይ ታስረው መቆየታቸው እንዳሳሰበው የጋዜጠኞች ተንከባካቢ ቡድን (CPJ) ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ ማሳወቁን
 
የኛ ፕሬስ ማክሰኞ ነሐሴ 8/2005 ዓ.ም
  • ነሐሴ 14/2004ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት የተነጠሉት የጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በሥላሴ ካቴድል ቅጥር ግቢ ውድ በሆነ የእምነበረድ አይነት የታነፀው የተቀማጠለ መካነ መቃብር ተጠናቆ በመጪው ሳምንቶች ይመረቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ
  • የወሲብ ድረገፆችን በማሰስ ኢትዮጵያ፤ ስሪላንካን ተከትላ ሁለተኛ መውጣቷን ጎግል የተሰኘው እውቅ ዓለም አቀፍ ተቋም ይፋ ማድረጉን እና ኢትዮጵያ ከቀዳሚዎቹ ተርታ እንድትቀመጥ በዘንድሮ ኣመት በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ ባለው የቢግ ብራዘር አፍካ ውድድር ተሳፊ የነበረችው ቤቲ አበራ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳበረከተች
  • ከስምንት ወር በፊት ለተለያዩ ስልጠናዎች ወደ ደቡብ ኮሪያ ካመሩ 59 ኢትዮጵውያን መካከል 38 ኢትዮጵያውያን የኮርያን መንግስት ጥገኝነት መጠየቃቸውን


ሪፖርተር ነሐሴ 8/2005 ዓ.ም
  • ነሐሴ 2 ቀን 2005 ዓ.ም. 1434ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በእስልምና እምነት ተከታዮች በተለይ በአዲስ አበባ ብሔራዊ ስታዲየም ሲከበር፣ ከፖሊሶች ጋር በተፈጠረ ግጭት በቁጥጥር ሥር ውለው ከነበሩ በርካታ ሰዎች መካከል፣ አብዛኛዎቹ በምክርና በከባድ ማስጠንቀቂያ መለቀቃቸውን ፖሊስ ማታወቁን እና ፍርድ ቤት የቀረቡት የምርመራ ጊዜ እንደተጠየቀባቸው
  • እስከ ነሐሴ 17 ድረስ የሚቆየው የ40/60 ቤቶች ምዝገባ ባለፈው ሰኞ ነሐሴ 6 ቀን 2005 ዓ.ም. አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ 116 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎችና መገናኛ አካባቢ ከአምቼ ፊት ለፊት በሚገኘው የአዲስ አበባ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት መጀመሩን

ሠንደቅ ነሐሴ 8/2005 ዓ.ም
  • የመብት ጥያቄ ያነሱ የሙስሊሙ ማኀበረሰብ አካላት ላይ መንግሥት እየወሰደ ያለው የኃይል እርምጃ አጥብቀው እንደሚቃወሙት ሶስት የተቃዋሚ ፓርቲዎች ማለትም የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ)፣ የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ እና የመላ ኦሮሞ ሕዝብ ድርጅት ነሐሴ 5 እና 6 ቀን 2005 ዓ.ም በተናጠል መግለጫ መስጠታቸውን (እና የመግለጫቸውን ሙሉ ቃልም ተካቷል )
  • በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር የሆኑት፤ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ፓርቲ (ኦፌኮ)ሊቀመንበር እና በቅርቡ መድረክ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ የመድረክ ሊቀመንበር ሆነው የተመረጡት ዶ/ር መረራ ጉዲና “የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምስቅልቅል ጉዞና የህይወቴ ትዝታዎች” በሚል ርዕስ አዲስ መፅሐፍ ማሳተማቸውን እና ገበያ ላይ መዋሉን 

አድማስ ነሐሴ 11/2005 ዓ.ም

  • ድምፃዊ ኢዮብ መኮንን፣ “ስትሮክ” ተብሎ በሚታወቀው ህመም ቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል ስለመግባቱ እና ለተጨማሪ ህክምና ወደ ኬንያ ስለሚኖረው ጉዞ (ይህ ዜና በአድማስ ጋዜጣ ከወጣ በኋላ ትላንት ማታ ላይ ድምፃዊ እዮብ ኬንያ ሄዶ ህክምናውን እየተከታተለ እያለ ከዚህ ዓለም በሞት  መለየቱ ተሰምቷል፡፡ ነፍስ ይማር!)
  • የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ መምህራን በተማሪዎችና በአስተዳደር መካከል የነበረው ውጥረት እንዲረግብ ጥረት በማድረጋችን በኮሌጁ ቅጽር ግቢ ከሚገኙ መኖርያዎቻችን አለአገባብ ልቀቁ ስለመባላቸው
  • በሳምንት አንድ ቀን ውሃ ማግኘት ብርቅ የሆነባቸው ሰፈሮች፣ በውሃ እጦት አካባቢያቸውን በመጥፎ ጠረን የሚበክሉ የኮንዶሚኒየም መኖሪያዎች፣ ለተደጋጋሚ አቤቱታ ምላሽ ሳያገኙ በርካታ ወራት እየተቆጠሩ  ስለ ሚማረሩ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች
  • አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ፣ በመቀሌና በወላይታ ሶዶ ከተሞች ሠላማዊ ሠልፍና ህዝባዊ ስብሠባ ለማካሄድ የነበረው እቅድ በተለያዩ ጫናዎች መጨናገፉን የፓርቲው ሊቀ መንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ መግለፃቸውን

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሽመልስ ከማል ከአድማስ ጋዜጠኛ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ ተካቷል፡፡
ለአቶ ሽመልስ ከማ የቀረቡት ጥያቄዎች እና ከምላሹ ውስጥ የተወሰዱ በጥቂቱ፡-

በተቃዋሚ ፓርቲዎች እየተካሄዱ ስላሉ ሰላማዊ ሰልፎች የመንግስት አቋም ምንድነው?

“ተቃዋሚዎች ባይቃወሙና ባይሰባሰቡ ነው እንጂ የሚደንቀው ይህን ማድረጋቸው ብዙም የሚያስደንቅ አይደለም፡፡ ነገር ግን ከሚያነሷቸው ጉዳዮች ውስጥ የበርካታ ዜጐች ስጋት የሆኑ ጉዳዮችም አሉ፡፡ በተለይ ከአክራሪ ጽንፈኛ ሙስሊም ቡድኖች ጋር አንዳንድ ፓርቲዎች የፈፀሙት ያልተቀደሰ ጋብቻ አሳሳቢ ነው፡፡ በሀገራችን ህገመንግስትም ፖለቲካ እና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው፡፡ የፖለቲካ ስብሰባዎች፣ የፖለቲካ ሰልፎች እንኳን ሃይማኖተኞችን ሊቀላቅሉ፣ የሃይማኖት ተግባራት ከሚፈፀምባቸው ቦታዎች በተወሰነ ርቀት መሆን አለባቸው፡፡ አሁን ግን ሁለቱ መቀያየጥ የሌለባቸውን ነገሮች ሲያካሂዱ እያየናቸው ነው፡፡”

“በየአደባባዩ የጠሩትና ሚሊዮኖችን እናስከትላለን ብለው የለፈፉለት ሰላማዊ ሰልፍ፣ በመቶዎችና በአርባዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ይዞላቸው ሲመጣ ያዩ ተቃዋሚዎች፣ ሌላ ሃይል እናገኝበታለን ብለው የገቡበት ስሌት አደገኛ ስሌት ነው፡፡ ከሽብርተኝነት ጋር የተፈጠረ ድሪያ ነው የሚሆነው፡፡ እንዲህ አይነቱን ነገር ሊጠነቀቁ ይገባቸዋል፡፡ መጥፎ አካሄድ ነው፡፡ ካለፈው ስህተታቸው ትምህርት መውሰድ አለባቸው፡፡ ህገመንግስቱ ሲጣስ ዳር ቆሞ የሚመለከት መንግስት አይደለም ያለው፡፡”

በሠልፎቹ ከሚጠየቁት ጉዳዮች መካከል መንግስት ምላሽ ያሻቸዋል ብሎ የተቀበላቸው የሉም? በተለይ ከሰብአዊ መብት አያያዝ ጋር    የሚነሱ ጥያቄዎች ላይ?

“ዝም ብሎ ለፕሮፖጋንዳ ፍጆታ የሚያነሷቸው ካልሆነ በቀር፣ በሰብአዊ መብት አያያዝ በኩል መንግስት የዜጐችን የሰብአዊ መብት አያያዝ አተገባበር በጣም በተጠናከረ መልኩ እያሻሻለና አድማሱን እያሰፋ በመሄድ፣በቅርቡ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት አያያዝ መተግበሪያ (አክሽን ፕላን) ያወጣ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚያ ላይ የእያንዳንዱን ዜጋ ዲሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብት ጥበቃ ለማስተግበር የሚያስችሉ ዝርዝር መርሃ ግብሮችን ነው ያወጣው፡፡”

በተለያዩ ከተሞች እየተካሄዱ ያሉት ሰላማዊ ሰልፎች እና ህዝባዊ ስብሰባዎች በመንግስት ላይ ጫና የመፍጠር አቅም የላቸውም?
“እንዴት ነው የሚፈጥሩት! ጐንደር በጠሩት ሰልፍ ላይ 200 የሚሆን ሰው ነው የተገኘው፡፡ በሌሎችም ቦታዎች ተመሳሳይ ነው፡፡ እነሱ “ለምንድነው ስብሰባችን ባዶ የሆነው?”፣ “አዳራሻችን ባዶ የሆነው?” ብለው መጠየቅ አለባቸው፡፡ ጣታቸውን ወደ ውጪ ከመደንቆር ይልቅ የህዝቡን ፍላጐት ማየትና ወደ ውስጣቸው መመልከት አለባቸው፡፡”

“ነገር ግን ይህን ለመሸፋፈን መንግስት ጫና በማድረጉ ሰው ሊወጣልን አልቻለም ሲሉ ነው የሚደመጡት፣ ይሄ መሠረት የሌለው ውንጀላ ነው።”

አንድነት ፓርቲ የፀረ ሽብር አዋጁን በማሰረዝ የሚሊዮኖችን ድምጽ እያሰባሰበ ነው፡፡ የሚሰባሰበው ድምጽ አዋጁን ሊያሰርዘው ይችላል?

“የፀረ ሽብር ህጋችን ከተለያዩ የአለም ሀገራት ተጠንቶ የተቀረፀ ነው፡፡ የዜጐቻችንን ደህንነት ከሽብር ጥቃት ለመከላከል የህግ ከለላ ያስፈልግ ነበር፡፡ በዚህ መሠረት ህጉ ተቀርጿል፡፡ በህጉም እስካሁን ሊከሰቱ ይችሉ የነበሩ አያሌ ሙከራዎችን ማክሸፍ ችለናል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ስጋት የሚገባቸው ወገኖች እነማን እንደሆኑ ጥርጥር የለውም፣ ዜጐች ግን ስጋት ላይ አይወድቁም፡፡ ህጋዊ ፓርቲዎችንም ስጋት ላይ አይጥልም፡፡ ተገቢ የሆነውንና ያልሆነውን አጣቅሶ ለመሄድ ያሰበ ካለ ግን ድንጋጌው ስጋት ላይ ሊጥለው ይችላል፡፡ ዜጐች ግን ሙሉ ድጋፍ የሰጡት ህግ ነው፡፡”

ህጉን ድምጽ በማሰባሰብ ማሰረዝ አይቻልም ማለት ነው?

“ህግ የሚወጣው በህግ አውጪ አካላት ነው። እነዚህ አካላት ከማውጣቱ ባሻገር ህጉን መሻርም ማሻሻልም ይችላሉ፡፡ እነዚህ ድርጅቶች የህግ የበላይነት ለማክበርና ለህገመንግስታዊ ስርአት እውቅና ለመስጠት የሚያንገሸግሻቸው ተቋማት እንደሆኑ እናውቃለን፡፡ ህገመንግስታዊ ተቋማትንና ህጋዊ አሠራሮችን ለመቀበል የማይፈልጉ ፓርቲዎች ናቸው ይህን የሚያደርጉት፡፡”

ሪፖርተር ነሐሴ 12/2005
  • የአክሰስ ሪል ስቴት የቦርድ ሊቀመንበርና ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ኤርሚያስ አመልጋ በዚህ ወር መጨረሻ ስለመምጠታቸው እና ለአክሰስ ሪል ስቴት 40 ከመቶ ድርሻውን የሰጠውና 60 በመቶ የሚሆነው ከፍተኛ ባለድርሻ የሆነው ፓስፊክ ሊንክ ኢትዮጵያ ሪል ስቴት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ‹‹ከአክሰስ ሪል ስቴት ጋር በመሆን ቪላና አፓርትመንት እገነባላችኋለሁ በማለት ውል ካስገባን በኋላ ውላችን ሳይፈጸምልን ገንዘባችንን ከወሰደ አንድ ዓመት ሞልቶታል፤›› በሚል፣ 137 ደንበኞች የ73,388,844 ብር ከ50 ሳንቲም ክስ መመስረት 
  • የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በቅርቡ በሕግ በተፈቀደለት የፋይናንስ ኪራይ (ፋይናንስ ሊዝ) አገልግሎት መሠረት፣ የካፒታል ዕቃ ፋይናንስ አገልግሎት ወይም ለምርትና ለአገልግሎት የሚውሉ ማሽኖችንና ተሽከርካሪዎችን ለማከራየት ለሚፈልጉ ኩባንያዎች ፈቃድ ለመስጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን
  • የህንዱ ኩባንያ ካራቱሪ አግሮ ፕሮዳክትስ፣ የሼክ መሐመድ አል አሙዲ ሳዑዲ ስታርን ጨምሮ ሰፋፊ የግብርና መሬት ወስደው ያላለሙ ኩባንያዎችን መሬት መንግሥት መንጠቅ ሊጀምር መሆኑን

UTC 16:00 የዓለም ዜና 19.08.2013

ኤርትራዊው ስደተኛና መከራው

$
0
0
ኤርትራዊው ስደተኛ ለተሻለ ህይወት ከሀገሩ ጠፍቶ ወደ ሱዳን እንደሄደ ይናገራል።…

የ«ኢቲዮ ቴሌ-ኮም» ና የቻይና ኩባንያዎች ስምምነት

$
0
0
ኢቲዮ ቴሌኮም ፣ ከፊል የቴሌኮሙዩኒኬሽን ማስፋፊያ ዕቅድ ማስፈጸሚያ የሚሆን 800 ሚሊዮን ዶላር የሚያስወጣ ውል፣ ZTE በሚል ምህጻር ከታወቀው የቻይና ኩባንያ ጋር ተፈራረመ። ቀደም ሲል፣ ከሌላው «ሁዋዌ» በሚል መጠሪያ ከታወቀው…

የግብፅ እልቂትና ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ

$
0
0
ግብፅ ጥይት፥ አረር፥ እየዘራች፥ አስከሬን-አጭዳ በእሳት ታጋያለች።ያቺ አስከሬን ለዝንታ-ዓለም የሚቀመጥባት ሐገር ዛሬ የሰዉ አካል ይተለተልባታል።ያቺ የጥንታዊ ሥልጣኔ ጎተራ፥ ያቺ የታሪካዊ የቅርስ ቋት፥ ያቺ ሥልታዊት ሐገር ታወረች? ወይስ አበደች? እዉሩ ወይም እብዱስ ማነዉ?…

የኢትዮጵያዉያኑ አትሌቶች ድል

$
0
0
ሞስኮ ውስጥ በመካሄድ ላይ ባለዉ በ14ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያዉያኑ አትሌቶች ድል ቀንቶአቸዋል።…

የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና

$
0
0
ሞስኮ ላይ ሲካሄድ የሰነበተው 14ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ትናንት ከሞላ ጎደል በስኬት ተጠናቋል።…

Amharic News 1800 UTC –ኦገስት 19, 2013

$
0
0
News, Sports, African Topics and Health…

የአሸንድዬ በዓል በላሊበላ ከተማ በድምቀት ይከበራል

$
0
0
  • በዓሉን የአካባቢው ተጨማሪ የቱሪስት መስሕብ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው
  • መንፈሳዊ ይዘቱ እንዲጠፋ የሚሹ ግለሰቦች በበዓል ኮሚቴ መካተታቸው ቅር አሰኝቷል
  • በበዓሉ አጋጣሚ ለቅ/ላሊበላ ደብር አስተዳደራዊ ችግር ትኩረት እንዲሰጥ ተጠይቋል

Ashenda Shadey00የጾመ ፍልሰታ ለማርያምን ፍጻሜ ተከትሎ የሚከበረው የአሸንድዬ በዓል ከነገ ጀምሮ የዓለም አቀፍ ብርቅዬ ቅርስ ማእከልና የውብ ባህል መድረክ በኾነው ላሊበላ ከተማ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ይከበራል፡፡

የቅዱስ ላሊበላ ደብርን ጨምሮ የወረዳ ቤተ ክህነቱን በበላይነት በሚመራው የቅዱስ ላሊበላ ደብር አስተዳደር ካህናት የሚሳተፉበት ያሬዳዊ ዝማሬና ቅኔ የበዓል ዝግጅቱ አካል ሲኾን የበዓሉ መክፈቻ ሥነ ሥርዐት በሚካሄድበት ነሐሴ ፲፮ ቀን ምሽት የላስታ – ላልይበላ ሕዝባዊ ባህል የኾነው የአሸንድዬ ልዩ ልዩ ባህላዊ ጨዋታዎችም ይቀርቡበታል፡፡

በዓሉን መሠረት ያደረጉ ጥናታዊ ጽሑፎች በባለሞያዎች ቀርበው የፓናል ውይይት እንደሚካሄድ ለበዓሉ አከባበር ከወጣው መርሐ ግብር ለመረዳት ተችሏል፡፡ ከነሐሴ ፲፭ – ፲፯ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም በሚቆየው ክብረ በዓል ከክልልና ከፌዴራል መንግሥት የተውጣጡ ከፍተኛ ባለሥልጣናትን ጨምሮ 200 ያህል ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙበት ተዘግቧል፡፡

ከዓመት ወደ ዓመት ለበዓሉ አከባበርና ክብረ በዓሉ ለሚያስገኘው ፋይዳ የሚሰጠው ትኩረት የሚመሰገን ነው ያሉ አስተያየት ሰጭዎች ውስጥ በዓሉን ከሃይማኖታዊ መሠረቱ አሰናብቶ ዓለማዊ ገጽታ ብቻ ለማላበስ በማሤር የሚታወቁ በእምነታቸው ልዩ የኾኑ አንዳንድ ግለሰቦች በበዓል አከባበር ኮሚቴ ውስጥ መካተታቸው ቅር እንዳሰኛቸው ገልጸዋል፡፡ በዓሉ ባህላዊና መንፈሳዊ ይዘቱን ጠብቆ ተጨማሪ የቱሪስት መስሕብ እንዲኾንና የባህል ገጽታ ግንባታን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ በከተማው አስተዳደርና በክልሉ መንግሥት ትኩረት በተሰጠበት ኹኔታ በእንዲህ ዐይነቱ ተንኮል የተለከፉ ግለሰቦች ሊነቃባቸውና ሊጋለጡ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡

አስተያየት ሰጭዎቹ አክለውም በሁሉም ገጽታው ጠንካራ ሃይማኖታዊ መሠረት ባለው የአሸንድዬ ክብረ በዓል አጋጣሚ የዞኑ አስተዳደር የልማት ጉብኝቶችንና ሌሎች አገራዊ አጀንዳዎችን ማካተቱ በራሱ ባይነቀፍም፣ በከፍተኛ የቱሪስት መስሕብነቱና በእምነት ማእከልነቱ ለከተማው ህልውናና ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ግንባር ቀደም ሚና ለሚጫወተው የቅዱስ ላሊበላ ደብር አስተዳደር መቃናትም ትኩረት እንዲሰጠው አመልክተዋል፡፡

የደብሩ አብያተ መቅደስ የሕዝብ ሀብትና የዓለም ቅርስ መኾናቸውን በማስታወስ የሚገኙበት ኹኔታ አሳሳቢና ጊዜ የሚሰጠው እንዳልኾነ ያስረዱት አስተያየት ሰጭዎቹ፣ የክብረ በዓሉ አጋጣሚ የደብሩ አስተዳደር ከሙሰኛና ዐምባገነን አሠራር ነጻነቱን አግኝቶ በሕግ እንዲመራ፣ ቅርሱ እንዲጠበቅና በገቢው መጠን የበለጠ እንዲለማ የሚያስችል ተጨባጭ ርምጃ እንዲወሰድ ግፊት የሚደረግበት እንዲኾን ጠይቀዋል፡፡

ላለፉት ስምንት ዓመታት የደብሩንና የወረዳ ቤተ ክህነቱን አስተዳደር ደርበው የያዙት መ/ር ቆሞስ አባ ገብረ ኢየሱስ መኰንን ሐሰተኛ ሰነድ በመፍጠርና ኾን ብሎ ቅርስን በማፍረስ ወንጀል ተጠርጥረው የተጠርጣሪነት ቃላቸውን እንዲሰጡ የሚፈለጉ ቢኾንም በፈቃድ ዕረፍት ሰበብ በአዲስ አበባ ተቀምጠው እንደለመዱት አንዳንድ ድሉል የፍትሕ አካላትን ለማማሰን እየማሰኑ መኾናቸው ተጠቁሟል፡፡

በሰሜን ኢትዮጵያ ክፍል ማለትም በትግራይ፣ ዋግና ላስታ ከሚከናወኑ በርካታ ሃይማኖታዊ ባህላዊ ጨዋታዎች መካከል እንደ እሽውላሌ፣ ጊጤ፣ ገና ጨዋታ፣ አሸንድዬ፣ ሙሻሙሾ እና ሆያ ሆዬ የመሳሰሉት በዐበይትነት ይጠቀሳሉ፡፡ በነሐሴ ወር አጋማሽ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዐለ ዕርገት/ፍልሰታ/ ጾም ፍች ጋራ ተያይዞ የሚከበረው የአሸንድዬ በዓል ማራኪና ልዩ ባህላዊ ጨዋታ ነው፡፡

በቀድሞዋ ሮሃ በኋላ ላሊበላ የሚከበረው በዓሉ÷ በላስታ አሸንድዬ፣ በትግራይ አሸንዳ፣ በዋግ ሻደይ፣ በራያ ቆቦ ስለል በይ በመባል ተቀራራቢነት ባላቸው ስያሜዎች ይጠራል፡፡ በሁሉም አካባቢዎች በተመሳሳይ ወቅት ልጃገረዶች ከወገባቸው ላይ ሣር መሰል ቅጠል በማሰር ከቤት ቤት በመዘዋወር የተለያዩ ጣዕመ ዜማዎችን በማሰማት የሚጫወቱት ጥንታዊ፣ ሃይማኖታዊና ባህላዊ ጨዋታ ነው፡፡ ዘንድሮም ከላሊበላ በተጨማሪ በላስታ እና በመቐለ በደማቅ ኹኔታ ይከበራል፡፡

በላሊበላና አካባቢው የቱሪስት ፍሰቱ ከፍተኛ የሚኾነው በታኅሣሥና ጥር ወር ሲኾን ይህም በአብያተ መቅደሱ (በቋሚ ቅርሱ) የሚከበሩ በዓላትን ማእከል ያደረገ ነው፡፡ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ቅርስ የኾነው የአሸንድዬ በዓል በአግባቡ ታቅዶና ተደራጅቶ ለቱሪስቶች ቢተዋወቅ ደግሞ በነሐሴና በመስከረም ወር የቱሪስት ፍሰቱን በመጨመርና የጎብኚዎችን ቀልብ በመሳብ የቱሪስቶችን ቆይታ ያራዝማል፡፡ ይህም እንደ ቻይና የውኃ በዓል፣ እንደ ስፔን የበሬ ውጊ፣ እንደ ብራዚልና አርጀንቲና የጎዳና በዓል ለመልካም ገጽታ ግንባታ ሊውል፣ ኢንቨስትመንትን ሊያስፋፋና የሥራ ዕድል ሊጨምር ይችላል፡፡

*        *       *

የፍልሰታ ጾምና በዓል ከአሸንድዬ ላስታ – ላልይበላ ባህላዊ ክንዋኔ ጋራ ያለው መስተጋብር

በኢትዮጵያ ከፍ ብሎ የሚታየው በብዛት ልጆች ተሳትፎ የሚያደርጉበት የፍልሰታ ጾምና በዓል ነው፡፡ ፍልሰታ የሚለው ቃል የእመቤታችን ሥጋ ከጌቴሰማኒ ወደ ገነት መፍለሱን፣ ኋላም በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር ከነበረበት መነሣቱን ለማመልከት የሚነገር ቃል ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረተ ቃሉ÷ ‹‹ተነሥአ እግዚኦ ውስተ ዕረፍትከ አንተ ወታቦተ መቅደስከ፤ አቤቱ ወደ ዕረፍትኽ ተነሥ፤ አንተና የመቅደስኽ ታቦት፡፡›› /መዝ.፻፴፩÷፰/፡፡ ‹‹ተንሥኢ ወንዒ ቅርብትየ እንቲአየ ሠናይት ርግብየ ውስተ ጽላሎተ ኮኵሕ ቅሩበ ጥቅም፤ አቅራቢያዬ መልካማ ርግቤ ተነሽ ነዪ በግንብ አጠገብ ወዳለው ወደ ዋሻው ጥላ፡፡›› /መኃ. ፪÷ ፲ – ፲፬/ የሚለው ነው፡፡

ኢትዮጵያ ይህን ጽሑፍ ካገኘችበት ጊዜ ጀምሮ ‹‹ለሐሴቦን ንጉሥ ልጅ ሁሉ ክብርዋ ነው፤ በወርቀ ዘቦ ልብስ ተሸልማለች፤ በኋላዋም ለንጉሡ ደናግልን ይወስዳሉ፤ ባልንጀሮችዋንም ይወስዱልሃል፡፡ በአባቶች ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ፤ ወንዶች ልጆችሽንም በዕቅፋቸው፣ ሴቶች ልጆችሽንም በትከሻቸው ያመጡልሻል፤›› ተብሎ በተነገረው የነብያት ቃል መሠረት ልጆችም፣ ወላጆችም በመተባበር የእመቤታችንን የፍልሰታ ጾምና በዓል ሲጠብቁ ይኖራሉ፡፡

ከቀደሙት ሰዎች ታሪክ ከእስራኤል መሳፍንት አንዱ ለኾነው የዮፍታሔ ልጅ መታሰቢያ ልጆች ወይም ደናግል በየዓመቱ በዓል ሲያከብሩ እንደ ነበረ ተናግሯል፡፡ /መጽ. መሳ.፲፩÷፵/፡፡ እንዲህ ከኾነ ዘንድ ኢትዮጵያውያት ቆነጃጅትና ሕፃናት፣ ኢትዮጵያውያን ጎልማሶች የእናታችንን የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን መታሰቢያ በየዓመቱ ሲያከብሩ የበለጠ ነገር ፈጽመዋል ማለት ነው፡፡

የጾመ ፍልሰታን መታሰቢያ ለመፈጸም ልጆችም ወላጆችም ይተባበራሉ፤ ጾሙ በፍትሐ ነገሥት በአንቀጽ ፲፭ ከተዘረዘሩት አጽዋም አንዱ ነው፡፡ ጾሙ ከፍቅር ጋራ የሚፈጸም ስለኾነ ልጆችም ወላጆችም የሚጾሙት በጉጉት ነው፡፡ ወላጆች ከባድ ምክንያት ካላጋጠማቸው በስተቀር ከአልጋ ወርደው፣ ከመሬት ላይ ተኝተው ወይም ከቤታቸው በቤተ እግዚአብሔር ዙሪያ ማረፊያ አሰናድተው ከነሐሴ ፩ – ፲፭ ድረስ ጥሬ በመብላት፣ ውኃ በመጠጣት፣ ሌሊት በሰዓታት፣ ቀን በጸሎት ውዳሴ ማርያም፣ ቅዳሴ ማርያም በመስማት፣ በምጽዋት፣ ቅዳሴ በማስቀደስ በከፍተኛ ሥነ ሥርዐት ይጾሙታል፡፡

ልጆችም በረኀብ ሳይሰማቸው፣ ውኃ ጥም ሳያሸንፋቸው ከ፯ ዓመት ዕድሜ ጀምሮ ያሉ ወንዶችና ሴቶች ሕፃናት እየጾሙ ይቆርባሉ፡፡ በመጨረሻ ነሐሴ ፲፮ ቀን ወላጆች በዓሉን በሥነ ሥርዐት ሲያከብሩ ልጆችም በልዩ ሥነ ሥርዐት ያከብሩታል፡፡

የረጅም ዘመን ታሪክ ባለጸጋ በኾነችው ሀገራችን ኢትዮጵያ የሚከበሩ በዓላት ጥንታዊነቷን፣ ታሪካዊነቷን፣ የነባር ሥልጣኔ ባለቤትነቷን ከሚገልጹ ቅርሶቿ መካከል ይመደባሉ፡፡ ቅዱስ ላሊበላ ኢትዮጵያ በውስጧ አቅፋ ከያዘቻቸው የሃይማኖት፣ የታሪክና የመካነ ቅርስ ማእከላት መካከል አንዱ ነው፡፡ ‹‹መላእክት በልደተ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማይ ወርደው በላሊበላ ይዘምራሉ›› ከተባለለት የቤዛ ኲሉ ክብረ በዓል ጀምሮ ባህላዊና ሃይማኖታዊ በዓላት ሞቅና ደመቅ ብለው ይከበሩበታል፡፡ ዘመናትን አቆራርጦ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ ከጊዜያችን የደረሰውና በፍልሰታ ለማርያም ጾም ፍጻሜ የሚከበረው የአሸንድዬ በዓል አንዱ ነው፡፡

*        *       *

የአሸንድዬ ባህላዊ ጨዋታ መገለጫ የኾነው አሸንዳ እንደ ቄጤማ ረጅምና እንደ ቅጠል ሰፋ ያለ ነው፡፡ ቁመቱ ከ80 – 90 ሣ.ሜ ይኾናል፡፡ ለምለም ነው፡፡ በወገብ እንደ ሽብሽቦ ኾኖ ይታሰርና ከግጥሙና ከዜማው ጋራ ተዋሕዶ በዳሌያቸው ላይ ይዞራል፤ ይሽከረከራል፡፡ በተለይ፡-

እቴ አይዞርም ወገብሽ

ባቄላን ነው ቀለብሽ

እያለች የበለጠ ወገባቸው እንዲዞር በግጥምና በዜማ አውጭዋ ስታዜም ተቀባዮቹ ደግሞ አባባሉን ለማስተባበል በኃይልና በዘዴ ወገባቸውን ሲያዞሩ ቅጠሉ ርግፍ እያለ ከወገባቸው ጋራ ይሽከረከራል፡፡

አሸንዳዬ አሸንዳ አበባ

እሽርግፍ እንደወለባ

ሲሉና ሲዞሩም አብሮ በኃይል ይዞራል፤ ከወገባቸው ላይ ርግፍ ይልና ዞሮ ተመልሶ ያርፋል፡፡ አሸንድዬ በተለያዩ የሰውነት አካላት (በአንገት፣ በትክሻ፣ በወገብ፣ በእጅ፣ በእግር ወዘተ) እንቅስቃሴ ይከወናል፡፡Ashenda Shadey02

አንዳንድ ምሁራን አሸንድዬ ገና ቅድመ ልደተ ክርስቶስ ጀምሮ የክረምቱን (ጨለማው፣ ጭቃው፣ ጎርፉ፣ ዶፉ፣ ብርዱ) መውጣትና የበጋውን (ብርሃኑ፣ ፀሐዩ፣ የወንዙ ጥራት፣ የአዝዕርቱ ማሸት፣ የአበባው ማበብ) መግባት ምክንያት በማድረግ ደናግል (አዋልድ) ቅድመ ዕንቊጣጣሽ ሁለት ሳምንት ሲቀረው ጀምሮ አዲሱን ዘመን በደስታና በሐሤት ለመቀበል በብሩህ ተስፋ ውስጥ ኾነው ይጫወቱት እንደነበር ይናገራሉ፡፡ እውነትም፡-

አሸንዳዬ አሸንዳ አበባ

እሽርግፍ እንደወለባ

አደይ አበባ አደይ አበባ

ነሽ ውባ ውባ

አደይቱ፣ መስከረሚቱ

መውደድ እንደሌሊቱ

እያሉ አበባንና መስከረምን ሲያነሡና ሲያወድሱ፣ የታጠቁትንም ቅጠል ሲያወሱ እውነትም ከአዲሱ ዘመንና ከዕንቊጣጣሽ በዓል ጋራ ግንኙነት እንደነበረው ያሳያል፡፡

አንዳንድ ሊቃውንት ደግሞ ከሊቀ ነቢያት ሙሴ ጋራ ያይዙታል፡፡ ከሕግ ባለቤት ከልዑል እግዚአብሔር ሕግን ተቀብሎ ያስተላለፈው ሙሴ እስራኤላውያን በግብጽ በባርነት በነበሩበት ጊዜ ዕብራዊት እናቱ በዚያ ስለወለደችውና ማንኛውም ወንድ ዕብራዊ ሲወለድ እንዲገደል በግብጽ ዐዋጅ መውጣቱ እናቱ እግዚአብሔር እንዳደረገ ያድርገው ብላ ከዐባይ ወንዝ ዳርቻ በቄጤማ ውስጥ አስቀምጣዋለች፡፡ ኋላ የፈርዖን ልጅ ገላዋን ልትታጠብ ወደ ወንዝ (ዐባይ) ስትሄድ ደንገጡሯን ልካ አውጥታ በእናቱ ሞግዚትነት አሳድጋው እስራኤልን ከተገዙበት የ430 ዓመት ባርነት ነጻ አውጥቷቸዋል፡፡

ይህን መሠረት በማድረግ፡-

አሸንድዬ አሸንዳ ሙሴ

ፍስስ በይ በቀሚሴ

የሚለው ባህላዊ ጨዋታ መነሻው ልጃገረዶች በጀርባቸው አሰውረው ከሚወዘውዙት ቄጤማ መሰል ሣር ስያሜ የመጣ ሲኾን ይህ ሣር(ቅጠል) ሙሴ የተጣለበትን ቄጤማ ስያሜ ወስዶ አሸንዳ ሙሴ ተብሎ ይጠራል፤ አበ ሙሴ፣ ወርቃበ ሙሴ እያሉ ደጋግመው ማንሣታቸው ለዚህ ማስረጃ ነው ይላሉ፡፡

በሌላ በኩል የአሸንድዬን ባህላዊ ጨዋታ ከመጥምቁ ዮሐንስ በሄሮድያዳ ልጅ ዘፈን (የሄሮድስ ልደት ዕለት) ምክንያት አንገት መቆረጥና ከአዲስ ዓመት ብሥራት ጋራ ያያይዙታል፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ በዓሉም መስከረም ፩ እና ፪ በየዓመቱ ይከበራል፡፡ መስከረም ፪ ምትረተ ርእሱ ተብሎ በቅዱስ ላሊበላ በቤተ ማርያም በጋለ ስሜት በማሕሌት በውዳሴና በቅዳሴ ይከበራል፡፡

ከዚሁ ጋራ በተያያዘ የአሸንድዬ ቅጠል ሔዋን ዕፀ በለስን በልታ ራቁቷን በኾነች ጊዜ ያገለደመችውን ቅጠል ሲያስታውስ፣ አረንጓዴ (ሐምራዊ) መኾኑም የድንግል ማርያምን ልብስ ያስታውሳል፤ በየሥዕለ ማርያሙ እንደምንመለከተው ልብሰ ቅድስት ድንግል ማርያም ሐምራዊ መልክ አለውና፡፡ አንድም ቅጠሉ ለምለም ነው፡፡ የዐዲሱ ዓመት በልምላሜ መምጣት የሚበሠርበት ነው፡፡

አሸንድዬው የሚታሰረውና የሚያርፈው በጀርባቸው እንጅ በፊታቸው አይደለም፤ ጀርባቸውን እንጂ የፊታቸውን አካል አይሸፍንም፡፡ የሰው ልጅ ጸጋው በበደል ቢገፈፍም መሐሪው እግዚአብሔር ፈጽሞ ሳይተወው ኋላ ከድንግል ተወልዶ የተገፈፈውን ጸጋ ልብስ እንደሚመልስላቸው ተስፋ የገባላቸው መኾኑን ያዘክራል፡፡

ይኹን እንጂ አሁን እየጎላ የመጣውና ዋና በዓል የኾነው ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፍልሰት ጋራ እየተያያዘ የመጣው የአከባበር ሥነ ሥርዐት ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ይከበሩ የነበሩ በዓላትና ሥርዐታት በሐዲስ ኪዳን ዘመን ሥርዐታቸውና ትርጉማቸው ተጣጥሞ መዘዋወራቸው አዲስ ነገር አይደለም፡፡ የአሸንድዬ ቅጠል ለጨዋታ የሚታሰረው በጒንጒን ታስሮ ተጠላልፎ ነው፡፡ ይህም መላእክት እመቤታችንን ክንፍ ለክንፍ ገጥመው ተያይዘው ማሳረጋቸውን ያጠይቃል፡፡Ashenda Shadey01

ይኸውም ቀደም ሲል እንደተገለጸው ‹‹አሸንዳ›› የሚባለው ሣር ዐይነት ቅጠል ኹኔታው ቀጭን ቢኾንም ቁመቱ ረዘም ያለ ኾኖ ቅርጹ ፊላ ዐይነት ነው፤ ሲነቅሉት ሥሩ ነጭ ነው፤ ዛጎል ይመስላል፡፡ ልጃገረዶች በልዩ አሠራር ሠርተው በቀሚሳቸው ላይ ይታጠቁታል፤ እንደ ዘርፍ ኾኖ ወደታች ይወርዳል፤ በሚጫወቱበትና በሚዘፍኑበት ጊዜ ዙሪያውን ሲነሣ ክንፍ ይመስላል፡፡ በዚህ ዐይነት ሥርዐት በዓሉን ሲያከብሩ ይውላሉ፤ በተለይ በገጠር ላሉ ሴቶች ሕፃናት ቆነጃጅት ልዩ በዓላቸው ነው፡፡

አሸንዳ ከሚባለው ሣር ዐይነት ቅጠል በልዩ ዐይነት አሠራር ሠርተው የሚታጠቁትና ሲጫወቱ፣ ሲዘፍኑ ዙሪያውን የመነሣቱ ኹኔታም መላእክት እመቤታችን ክንፍ ለክንፍ ገጥመው እያመሰገኑ ማሳረጋቸውን ያሳስባል፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ በትንቢቱ ምዕራፍ ፮ ላይ ባየው ራእይ ሱራፊ መልአክ በሁለት ክንፍ ፊቱን፣ በሁለት ክንፍ እግሩን ሲሸፍን፣ ሁለት ክንፉን በግራ በቀኝ ዘርግቶ ረብቦ ይታያል የሚለውን ያመለክታል፡፡ በዓሉንም የአሸንድዬ በዓል ይሉታል፡፡

በእውነት፣ ‹‹ደናግልን ለንጉሥ በኋላዋ ይወስዳሉ፤›› ሲል በቅዱስ ዳዊት የተነገረው ቃል ልጆች በእመቤታችን ፍቅር እየተኮተኮቱ አድገው ለእግዚአብሔር ቤተሰብ መኾናቸውን ያሳያል፡፡ በዚህ ሥርዐት ያደጉ ልጆችን እስከ ሕይወታቸው ፍጻሜ ከእመቤታችን ፍቅር የሚለያቸው የለም፡፡

*        *       *

የበዓሉ ቅድመ ዝግጅት

የአሸንድዬ ባህላዊ ጨዋታ ወቅት ክረምቱ አልፎ በጋው የሚደርስበት ነው፡፡ ‹‹ቡሄ ካለፈ የለም ክረምት፣ ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት›› እንዲሉ ብሩህ ሰማይ ሊታይ፣ አበባ በምድር ሊገለጥ፣ ፀሐይ ብርሃንዋን ልትሰጥ፣ ከዋክብት እንደፈርጥ ሊንቦገቦጉ፣ ጠቢቡ ንጉሥ ሰሎሞን እንዳለው ክረምቱ ሊያልፍ፣ የቁርየው ቃል በምድራችን ሊሰማ፣ በለሱ ሊጎመራ፣ ወይኖች ሊያብቡ፣ መዓዛቸውንም ሊሰጡ የሚቃረብበት ወቅት ነውና በሕዝበ ክርስቲያኑ ዘንድ በተለይም በልጃገረዶች ደስታን ያጭራል፡፡

ቅድመ ዝግጅቱ የሚጀመረውም የፍልሰታ ጾም ሲገባ ጀምሮ ነው፡፡ ነጫጭ ልብሱን ለብሶ ከማስቀደሱና ከመቁረቡ በተጨማሪ በዚሁ ሰሞን ለአሸንድዬ በዓል አከባበር የሚኾኑ ባህላዊ አልባሳት ማለት ትፍትፍና ጥልፍ ቀሚስ፣ መቀነት፣ ልዩ ልዩ ጌጣ ጌጥ ለምሳሌ፡- ያንገት መስቀል፣ የጆሮ ጉትቻ፣ የእጅ ድኮት፣ የእግር አልቦ፣ ድሪ ካሎስ (ማተብ) አምባር፣ ጉርሽጥ (እንሶስላ) ማሰባሰብና ማዘጋጀት፣ ልብስ ማጠብ፣ ፀጉር መሠራት. . .ወዘተ ከቅድመ ዝግጅት ውስጥ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

በዓሉ ሲደርስ አለቃ ይመርጣሉ፤ አለቃዋ በመልካም ባሕርይዋ የተመሰገነች፣ የመምራትና የማስተባበር ችሎታ ያላት፣ በአካልና በዕድሜ ላቅ ያለች፣ የታወቀችና ልምድንም ያካበተች መኾን ይኖርባታል፡፡ ገንዘብ ያዥም ይመርጣሉ፤ የታመነች፣ ገንዘቡን በጥንቃቄ ይዛ ለተፈለገው የምታውል መኾን ይጠበቅባታል፡፡ አውጭም ታስፈልጋለች፤ እንደ አቀንቃኝ ማለት ናት፡፡ ምንም እንኳ የድምፅና የግጥም ተሰጥዖ ያላቸው በብዛት ሊኖሩና አንዷ ሲደክማት ሌላዋ እየተተካች ማስኬዱን ቢያውቁበትም የበለጠ ችሎታ ያላቸው ይመደባሉ፡፡

በበዓሉ ዋዜማ ነሐሴ ፲፭ ወደ ዱር በመሄድ ከወንዝ ዳር የሚበቅለውንና አሸንድዬ የተባለውን ለባህላዊ ጨዋታው አመች የኾነውን ረጅም ቄጤማ መሰል ለምለም ሣር (ቅጠል) ቆርጠው ያመጣሉ፡፡ በዕለተ በዓሉ (ነሐሴ ፲፮) ማለድ ብለው ተነሥተው ይተጣጠባሉ፤ ይወላወላሉ፡፡ አምረው ተውበው፣ ለብሰው አጊጠው፣ በነጫጭ ባህላዊ ልብሳቸው ላይ አሸንድያቸውን በጀርባቸው ታጥቀው ብቅ ይላሉ፡፡ አጊያጊያጣችንንና አዋዋባችንን፣ አለባበሳችንንና አጨዋወታችንን በጠቅላላው የአኩሪ ባህል ባለቤትነታችንን ቁልጭ አድርገው ያሳያሉ፡፡

ነሐሴ ፲፮ ልጃገረዶች በየአጥቢያቸው በቡድን ይሰባሰቡና በመጀመሪያ ወደ ቤተ ክርስቲያን ይሄዳሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያኑን ሦስት ጊዜ እየዞሩ በመዘመር እዚህ ላደረሳቸው አምላክም ምስጋና ያቀርባሉ፡፡ ዝማሬያቸውም እንደሚሄዱበት ቤተ ክርስቲያን ሊለያይ ይችላል፡፡ ለምሳሌ መድኃኔዓለም ከኾነ፡-

እስከ በስመ አብ ብዬ ልጀምር ሰላምታ

ለመድኃኔዓለም ለአዳኙ ጌታ

ዐይነት ሊኾን ይችላል፡፡ የብልባላ ጊዮርጊስ አሸንድዬ ባዮች ጥንታዊውን ውቅር ቤተ መቅደስ እየዞሩ፡-

ቤተ ክርስቲያኑን ሁሉ ዐየነው በሰፊው

ብልባላ ጊዮርጊስ በልክ የተሠራው

በድንጋይ ላይ ድንጋይ ከዚያም በላይ ቤት

ብልባላ ጊዮርጊስ ትልቁ ታቦት

ይላሉ፡፡ በላሊበላ አሁንም፡-

አሸበረቀች ጨረቃ          ተወረወረች ኮከብ

በጊዮርጊስ ጫንቃ           በዐማኑኤል ክበብ

በሚካኤል ጫንቃ           በገብርኤል ክበብ

በእመብርሃን ጫንቃ         በሊባኖስ ክበብ

እያሉ ይዘምራሉ፡፡ በጣም የሚወዱትንና የበዓሉና የደስታቸው መግለጫ ከኾነው አሸንዳም በየቤተ ክርስቲያኑ ደጃፍ ላይ ያስራሉ፤ ይጥላሉ፤ ይጎዘጉዛሉ፡፡

ከቤተ ክርስቲያን መልስም በቆየው ዘመን መጀመሪያ ታላላቅ ከሚባሉና ከሹመኞች ቤት በመሄድ የደስታ መግለጫቸውን ያሰማሉ፡፡ ከዚያ ወደ ሌላው ሰው ቤት ያመራሉ፡፡ ሁሉንም በስድስቱ ቀናት ውስጥ ያደርሳሉ፤ እስከ ዕንቊጣጣሽ ድረስም የሚቆዩ አሉ፡፡ ሀብታም ነው፤ ድኻ ነው ብለው የሚተዉት ሰው አይኖርም፡፡ የመንገድ (የጉዞ) ዜማም አላቸው፤ አጀባዬ ይባላል፡፡

አጀባ ኾኗል ጅብጀባ      አጀባ ኾኗል ፈረሱ

በየት ልንገባ            ወዴት ነው እሱ

እያሉ በመቀባበል ካዜሙና ዜማውን ተከትለው ርግፍ ርግፍ እያሉ ወደላይም እየዘለሉ ከጨፈሩ በኋላ ካባወራው ወይም እማወራውጋ ሲደርሱ ከግቢው ውጭ ኾነው፡-

አስገባኝ በረኛ

  አስገባኝ ከልካ

እመቤቴን ላ

ጌታው አሉ ወይ አሉ ወይ

አሉ እንጂ ግቡ ይላሉ እንጂ

አሉ እንጂ፣ ተዘንብሏል ጠጂ

እያሉ በጨዋ መልክ አወድሰውና አስፈቅደው በር ካስከፈቱ በኋላ ወደ ግቢው ይገባሉ፡፡ ከዚያም በጥዑም ዜማ በሠናይ ቃና ይጫወታሉ፡፡ የጨዋታቸው ስንኞች ፍቅርን፣ ጀግንነትን፣ የሥራ ክቡርነትን፣ ሞያን፣ ውበትን. . .ወዘተ የሚያወድሱበት፣ በተለያየ ጣዕመ ዝማሬ የሚያሸበሽቡበት ነው፡፡ ባለቤቱ ሞቅ ያለ ስጦታ እንዲያበረክትላቸው ሲገፋፉትም፡-

ጌታው ስም ይሻል፤ ስም ይሻል

አንድ ብር እንኳ ጠፍቶ ያመሻል

በሬ ከጋጡ ሞቶ ያመሻል

እያሉ አመስግነው፣ ተመስግነው፣ ተሸልመው ከቤት ይወጣሉ፤ ወደ ሌላ ቤት ይሄዳሉ፡፡ ሽልማቱ ቀደም ሲል እህል፣ ዳቦ፣ ጠላ፣ እንጀራ፣ በግ፣ ፍየል፣ እርጎ ነበር፤ ይህ አሁንም በገጠሩ ይኖራል፡፡ በከተማው ግን እንየዐቅሙ በብር ነው፡፡ ምርቃቱንም ቢኾን እንደቀላል ነገር አይቆጥሩትም፡፡ እንደዚሁ እያሉ ቀኑን ያገባድዱና ወደማታው ወደ ሜዳ ይወጣሉ፡፡ በየቡድናቸው ተሰባስበው በተለይ አዲ ሻዶች ከላይ ሰባት ወይሮች ከታች ይኾኑና በግጥምና በግጥምና በዜማ ሲተቻቹ አምሽተው እንደተነፋፈቁ ቀኑ መሽቶ ጨለማው ይገላግላቸዋል፡፡ በዚህ ዐይነት ሰንብተው በዓሉ ነሐሴ ፳፩ ቀን ያበቃል፡፡ በመስቀል ከሆያ ሆዬ ባዮች ጋራ ደግሰው የሰጧቸውን ሰዎች አብልተው አጠጥተው ተጫውተው ተፍጻሚተ በዓል ይኾናል፡፡

በአጠቃላይ ዓመታዊው የአሸንድዬ ክብረ በዓል በትግራይ፣ በዋግና በላስታ በደመቀ ኹኔታ ይከበራል፡፡ የቅርብ ቤተ ዘመድና አንድ ናቸው፤ በጊዜ ብዛትና በቦታ መራራቅ የተነሣ በቋንቋና በአንዳንድ ባህላዊ ልዩነት ቢኖረውም፡፡ ዋናው ነገር ሲኒማው፣ ዘፈኑ ከባህላችንና ከኛነታችን እየራቀ በመጣበት ወቅት አሸንድዬ ሃይማኖታዊ(ባህላዊ)፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ያለው አኩሪ ባህል ነውና ጠብቆና አስፋፍቶ መያዙ ነው፡፡

ወንፊቱ ሰፌዱ እያለ በጃችን

ያልተነፋ ዱቁት ምነው መብላታችን

እንዳሉት ሊቁ ለብዙ ነገር ምንጭና መነሻ የሚኾን ብዙ ርእሳነ ነገር÷ ለምሳሌ ለሥነ ጽሑፍ፣ ለሥነ ጥበብ፣ ለኪነ ጥበብ የሚኾን ጥሬ ነገር የምናገኝበት ነውና ጠብቀንና አክብረን እንያዘው፡፡ በሌላ በኩል ይህ በዓል ክርስቲያናዊ በዓል ከኾነ ለምን በአንዳንድ የሰሜን አካባቢ ብቻ ተወስኖ ቀረ? ለምን በመላው ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ዘንድ አይከበርም? በቂ መልስ ለመስጠት ጥናቱ መቀጠል ይኖርበታል፡፡

*          *          *

ምንጭ፡- ዓለሙ ኃይሌ፣ የአሸንድዬ ባህላዊ ጨዋታ በላስታ ላሊበላ፣ ነሐሴ ፳፻፬ ዓ.ም

             አለቃ አያሌው ታምሩ፣ ወላዲተ አምላክ በኢትዮጵያ፣ ፲፱፻፸፱ ዓ.ም

    

ባህላዊ የሆያ ሆየ – ቡሄ ጨዋታ በላስታ ላሊበላ

የኢትዮጵያን ጥንታዊነትና የሕዝቧን ተጠባቢነት ቁልጭ አድርገው ከሚያሳዩን ኁልቆ መሳፍርት የሌላቸው ባህሎች መካከል አንዱ ሆያ ሆዬ የሚባለው ባህላዊ ጨዋታ ነው፡፡ ይህ ባህላዊ ጨዋታ በማንኛውም ጊዜ የሚዘወተር ሳይኾን ወቅቱን ጠብቆ በየዓመቱ የሚመጣ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ በአንዳንድ አካባቢ እየተረሳና እየቀዘቀዘ ብቅ ጥፍት እያለ፣ ዜማውና ግጥሙም አራምባና ቆቦ እየኾነ፣ ተራነትም እየታየበት የመጣ ይመስላል፡፡

ይህም የሚኾነው ማንኛውም ባህላዊ ኢንታንጀብል ቅርስ የመወለድ(የመፈጠር)፣ የመዳከምና የመጥፋት ባሕርይ ስላለው ወይም እንደ ታንጀብሉ ቅርስ ትኩረት ሳይሰጠው እየቀረ ሊኾን ይችላል፤ ወይም የባሕር ማዶውን ነገር ሁሉ ጠቃሚ፣ የእኛ የኾነ ነገር ኋላ ቀር እንደኾነ አድርገን በማሰብና የውጩን ስናከብርና ስንከተል የእኛን በመተዋችን፣ ከእጃችንም እያመለጠ ሲሄድ በመርሳታችን፣ ጥቅሙን ባለመገንዘባችን፣ በመንፈሳዊ ሀብት የበለጸገ የአበው ቅርስ፣ የሀገር ውርስ መኾኑን ባለማስተዋላችን ወይም በሌላም በሌላም ምክንያት ሊኾን ይችላል፡፡

ያም ኾነ ይህ የሆያ ሆዬ ሥነ ሥርዐት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ይከበራል፤ በላስታ ላሊበላም አንድ ጊዜ ሞቅ ሌላ ጊዜ ቀዝቀዝ እያለ ይከወን እንጂ እስከ አሁን ድረስ ቀጥሎ የሚገኝ ባህላዊ ጨዋታ ነው፤ በአብዛኛው በቡሄ ሰሞን፡፡ እንደሚታወቀው ቡሄ የሚከበረው የደብረ ታቦር ዕለት ነው፡፡ ደብረ ታቦር ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኰቱንና ክብረ መንግሥቱን በቅዱሱ ተራራ የገለጠበት ታላቅ ዕለት ነው/ማቴ.፲፯፣ ማር.፱፣ ሉቃ.፱/፡፡ ፍጹም አምላክነቱ የተገለጠበትንና የእግዚአብሔር ልጅ መኾኑ በአባቱ የተመሰከረበትን ዕለት ለማዘከር ሕዝበ ክርስቲያኑ ሆያ ሆዬ በማለት፣ ችቦ በማብራት፣ ቡሄ በመጋገርና በመብላት፣ ጅራፍም በማንጓትና በመጋረፍ ያከብረዋል፡፡

ችቦው በደብረ ታቦር ተራራ የተገለጠውን ብርሃነ መለኰቱን እንዲሁም የኃጢአትን ጨለማ ሊገፍ ወደዚህ ዓለም የመጣውን፣ ብርሃናትን የፈጠረውንና እርሱም እውነተኛ የዓለም ብርሃን የኾነውን ኢየሱስ ክርስቶስን ይወክላል፡፡ ቡሄው (ቡቼው) ያኔ ከብቶቻቸውን ይጠብቁ የነበሩ እረኞች በደብረ ታቦርና በአካባቢው በተገለጠው ብርሃን ጨለማ ጠፍቶላቸው ሐሤት በማድረግ ዘንግተው ስለቆዩባቸው ቤተሰቦቻቸው ለምግብ የሚኾን ዳቦ ጋግረው በሐ (ሰላም) እያሉ የወሰዱላቸውን፣ እንደ አንዳንድ ሊቃውንት አባባልም ከሰማይ የወረደውን እውነተኛ ኅብስት ኢየሱስ ክርስቶስን ለማስታወስ፣ የጅራፉ ድምፅ ከሰማይ ከእግዚአብሔር አብ የተሰማውን ‹‹ይህ የምወደው የምወልደው ልጄ ነው፤ እርሱን ስሙት›› የሚለውን ነጎድጓዳማ ድምፅ ለማሰብ፣ ግርፊያው ክርስቶስ ዓለምን ሊያድን ሲመጣ በአይሁድም 6666 ጊዜ መገረፉን ለማዘከር ነው፡፡ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በዊሕ (ቦሓ) መታየት፣ መገለጥ፣ መጉላት፣ ብሩሕ፣ ጽዱል፣ ጸዐዳ ብለው ቡሔ ከዚህ የወጣ ነው ይሉታል፡፡

በነገራችን ላይ ቅዱስ ላሊበላ ሕንጻዎቹን የሠራው በቅድስት ኢየሩሳሌም አምሳል ነውና ደብረ ሮሐም አዲሲቱ ኢየሩሳሌም ትባላለችና ኢየሩሳሌም የያዘችውን ሁሉ ዳግማዊት ኢየሩሳሌም ላሊበላም ይዛለች፡፡ በዚህም መሠረት የደብረ ታቦር ተራራ ስሙንና ግብሩን እንደያዘች ከከተማው በስተደቡብ ከቤተ ገብርኤል በስተምዕራብ ጉብ ብላ ትታያለች፡፡ የደብረ ታቦር ዕለት ነሐሴ ፲፫ በዚያ ተራራ ወንዶች ጅራፍ በማስጮኽ ሲያስቧት፣ ሌሊቱን ደግሞ ችቦና ጧፍ ኋላም ማሾ ሲበራባት ያድር እንደነበር የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ያስታውሳል፡፡ ማሕሌቱ ግን ከነዋዜማው በመድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በደመቀ ኹኔታ ተቁሞ እንደተዘመረ እንደተወረበ ይታደራል፤ ይዋላል፡፡ የቆሎ ተማሪው ዝክርና አከባበርም ልዩ ነው፤ ለደቀ መዛሙርት ምስጢረ መለኰት የተገለጠበት በዓል ነውና ለተማሪውም ምስጢር የሚገለጥበት ነው ተብሎ ይታመናልና፡፡

ሆያ ሆዬ በቅዱስ ላሊበላ የሚከበረው ግን ከመስከረም ፩ – ፲፯ ቀን ነው፡፡ በአንዳንድ የሀገሪቱ ክፍሎች ለምሳሌ በወረዒሉ ከቡሄ ጀምሮ እስከ መስቀል ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ እንደሚከናወን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ በትግራይ በተለይም ‹‹አውርስ›› በሚል ስም ከነሐሴ ፲፮ ቀን ጀምሮ መስቀል ማጠናቀቂያው መኾኑን የሀገር ተወላጆች ለዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ነግረውታል፡፡ በመስከረም ላስታ ላሊበላ ዙሪያዋ ሁሉ ያምራል፤ አበባው ያብባል፤ እኽሉ ያሸታል፤ አዝመራው ይደርሳል፤ ወንዙ ይጠራል፤ ፏፏቴው ይወርዳል፡፡

በዚህ ጊዜ ዝናም ይቆማል፤ ጭቃ ይደርቃል፤ ጨለማው ይወገዳል፤ ብርሃን ይፈካል፤ ሰማይ በከዋክብት ይደምቃል፤ ምድር በአበባ ያጌጣል፤ ሜዳው በአበባ ያሸበርቃል፤ መስኩ በአደይ ይንቆጠቆጣል፤ መሬት ታሸብርቃለች፤ ፍጥረት ትሥቃለች፤ ምድር ትፈነድቃለች፡፡ የወጣቱ ልብም ይደሰታል፡፡ ፊቱ ያብባል፤ ገጹ ይፈካል፤ መንፈሱ ይረካል፤ ነፍሱ ሐሤት ታደርጋለች፤ ሕይወቱ ትለመልማለች፤ መንፈሱ ትደሰታለች፡፡

ይህን ስሜቱን ከሚገልጽበት፣ ሕይወቱን ከሚያስደስትበትና ደስታውን ከሚያካፍልበት አንዱና ዋናው ሆያ ሆየ ነው፡፡ በዓሉ የሚከበረው በዓመት አንዴ በዚህ ሰሞን በመኾኑ እስከደርስለት ይቸኩላል፡፡ ትውልድ አልፎ ትውልድ እየተተካ ዘመናትን አቆራርጦ ከሱ የደረሰውን ይህን ባህላዊ ሥርዐት እርሱም በተራው ሊያከብረው ይናፍቃል፡፡

በላስታ ላሊበላ የሆያ ሆየ በዓል ቅድመ ዝግጅት የሚጀመረው በዓሉ ከመከበሩ አንድ ቀን አስቀድሞ ነው፡፡ ከጳጉሜ አንድ ጀምሮ ወጣት ወንዶች ወንዝ እየወረዱ ገላቸውን ያጸዳሉ፤ ልብሳቸውን ያጥባሉ፤ ለጭፈራው ዋና መሣርያ የሚኾናቸውን ዱላም ያዘጋጃሉ፤ ለጨዋታ የሚያስፈልጋቸውን ግጥምም ያጠናሉ፡፡ በአንዳንድ አካባቢ አለቃና ገንዘብ ያዥ ይመርጣሉ፡፡ የዘመን መለወጫ ዕለት ሁሉም በየቤቱ የተገኘውን ሲበላ ሲጠጣ ይውልና ወደ ማታው ጅራፍ በማጮኽ ይሰበሰባሉ፡፡ ያልወጣውን ለማስወጣት፣ ያልመጣውን ለማስመጣትም እየተቀባበሉ፤

እሆይ ሲራራ

እገሌ ሲፈራ

ከምድጃው

እናቱ ተነሺ

ያንን አብሺ

እሱ በመፍራቱ

ከኛ መለየቱ

እያሉ በረጅም ዜማ በጩኸት በየዐደባባዩ እየዞሩ ይጣራሉ፡፡ ይህን ጊዜ እኔ ወንዱ እንዴት ፈሪ እባላለሁ በማለት ዱላውን እየያዘ፣ ከየቤቱ እየተመዘዘ ወጥቶ ጀማውን (ስብስቡን) ይቀላቀላል፤ ያልተገናኘ ይገናኛል፤ የተነፋፈቀ ይሳሳማል፡፡

የጭፈራ ሰዓቱ ማታ ማታ ነው፡፡ ምናልባት አብዛኛው ገበሬና ከብት ጠባቂ ስለሚኾን ከየሥራ ስምሪቱ ውሎ ሲመለስ አመቺ ኾኖ ያገኘው ምሽቱን በመኾኑ ይኾናል፡፡ ወጣቱ በሥራ የደከመውን አካሉንና አእምሮውንም የሚያሳርፍበት፣ የሚዝናናበትና ሕይወቱን ደስ የሚያሰኝበትም ነው፡፡ ጨዋታው የበዓሉን ድባብ ሞቅ ደመቅ ያደርገዋል፡፡ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር፣ የብልጽግና እንዲኾን ብሩህ ተስፋን ይሰንቃል፡፡

ወጣቶቹ እየጨፈሩና እየፈነደቁ የሚያስተላልፉት መልእክትና የአከናወን ስልት ከቅርጽና ይዘት አኳያ በአራት ሊከፈል ይችላል፡፡ በተለይ የግጥሙ ዐይነት የጉዞ(የመንገድ)፣ የቤት፣ የምስጋና፣ የቅሬታ በመባል በአራት ይከፈላል፡፡ የሆያ ሆዬ ባህላዊ ጨዋታ በወጣት ወንዶች ብቻ የሚከናወን ነው፡፡ ወቅቱም ከዘመን መለወጫ ጀምሮ እስከ መስቀል ድረስ ብቻ ነው፡፡ መስቀል የበዓሉ ማጠናቀቂያ ወቅት ነው፡፡ ከነሐሴ 16 -21 ቀን ደግሞ የአሸንድዬ ባህላዊ ጨዋታ ይከናወናል፡፡ ሆያ ሆዬ የወጣት ወንዶች እንደኾነ ሁሉ አሸንዳየ ደግሞ የወጣት ሴቶች ብቻ ነው፡፡

ሴቶቹም ኾኑ ወንዶቹ በበዓል ሰሞን ያገኙትን ገንዘብ በአንዳንድ ከተሞች ዛሬ ዛሬ እንደሚታየው ተከፋፍለው ለግል ጥቅማቸው አያውሉትም፤ ሰቶቹ ገበያ ወጥተው አስፈላጊውን ነገር በመግዛት የሚበላና የሚጠጣ ያዘጋጁበታል፡፡ ወንዶች ድሮ እስከ ሰንጋ አሁን ሙክት ይገዙበታል፡፡ ተባብረው ይደግሱበታል፡፡ ዳስ ጥለውና ድንኳን ተክለው በጋራ ኾነው የሰጣቸውን ሁሉ ይጠሩና ያበሉበታል፤ ያጠጡበታል፡፡ ላልመጣም ተሸክመው ይወስዱለታል፡፡

ይህ ሁሉ ኾኖ ድግሱ ሲያልቅ በመጨረሻ ለመጪው ዓመት በሰላምና በጤና እንዲያደርሳቸው ተመራርቀው፡-

ከርሞ እንገናኝ ባመት

እናንተም ሳትሞቱ እኛም ሳንሞት

ተባብለው ይለያያሉ፤ በዓሉም እንደተናፈቀ በዚሁ ይጠናቀቃል፡፡ በአጠቃላይ ከነሐሴ እስከ መስከረም ፲፯ ድረስ ላስታ ላሊበላ በዓል በዓል ትሸታለች፤ ሞቅ ደመቅ ትላለች፡፡ ጧት ጧት አዕዋፍ ይዘምራሉ፤ ማታ ወጣት ወንዶች ሆያ ሆዬ ይላሉ፤ ቀን ቀን ሴቶች አሸንዳየ ይጨፍራሉ፤ ሌሊት ሌሊት ካህናት ሰዓታት ይቆማሉ፤ ስብሐተ ፍቁር ያደርሳሉ፤ ነጋ ለኪዳን ጠባ ለቁርባን ይተጋሉ፤ ቀን ቀን መዘምራን(ደባትራን) በማሕሌት ይቆማሉ፤ ይወርባሉ፤ ያሸበሽባሉ ማለት ይቻላሉ፡፡ የዜማ ዐይነት እዚህ ይሰማል፤ እግዚአብሔር ይመሰገናል፡፡

 

የሆያ ሆዬ ፋይዳ

ሆያ ሆዬ በየዓመቱ በፌስታ በደስታ ተከብሮ የሚያልፍ ባህላዊ ጨዋታ ብቻ አይደለም፡፡ የተሰባሰቡ ወጣቶች የማኅበራዊ ሕይወት ትስስር መሠረት የሚጥሉበት በዚሁ በሆያ ሆዬ ሰሞን ነው፤ በተለይ በገጠሯ ላስታ የሆያ ሆዬ ስብስብ በሂደት ወደሚዜነት ያድጋል፤ ቃል ኪዳን ይገባቡታል፤ አግብተው ሲጨርሱም ማኅበራዊ ቁርኝት የሚዳብርበት፣ የጽዋ ማኅበርም የሚጠጡበት፣ ቅዱሳንን የሚዘክሩበት፣ አብረው የሚበሉበት፣ የሚጠጡበት የሚደሰቱበት፣ በደቦና በወንፈል ተሰባስበው እያንዳንዳቸውን ሥራ እየተረዳዱ የሚተገብሩበት(በቤት ሥራ)፣ በግብርና (በእርሻ፣ በአረም፣ በአጨዳ፣ በውቂያ)፣ በኀዘን በደስታ የሚገናኙበት(የሚካፈሉበት) እስከ መጨረሻይቱ ሕቅታም የሚጓዙበት ይህም ሂደት ከእነርሱ ሕይወት ጋራ የሚያከትምበት ሳይኾን በልጆቻቸውም የሚቀጥልበት ነው፡፡

ሆያ ሆዬ የማኅበራዊ አገልግሎት ሚና በልጅነት ሙከራ የሚደረግበት ማለት መሪ ለመኾን የሚችል አለቃ፣ ታማኝ ገንዘብ ያዥ፣ ድምፃዊ፣ አቀንቃኝ፣ ያነጋገር ለዛ ያለው ውሕደቱን አድማቂ፣ ጨዋታ አሟቂ ኾኖ አቅምን በማሳየት በወደፊቱ ለአንድ ቁም ነገር የሚታጭበት ነው፡፡ ይህም እየተኮተኮተ ያድጋል፡፡ በጨዋታዎቹ በግጥም ሞያ የሚወደስበት፣ ፍርሃት፣ ስንፍና፣ ደግነት፣ ሞያ ቢስነት፣ ሥራ ፈትነት፣ ጊዜውን አልባሌ ሥፍራና ቦታ ማሳለፍ የሚነቀፍበት ወዘተ ነው፡፡ በጠቅላላው የኋላው ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለዘላቂው ኑሮ መሠረት የሚጥልበት፣ ከፍተኛ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ባህላዊ፣ አስተዳደራዊና ሃይማኖታዊ ጥቅምና እርባና የሚገኝበት በመኾኑ ባህሉ መጠበቅ መከበር ይገባዋል፡፡

ምንጭ፡- ዓለሙ ኃይሌ፣ ባህላዊ የሆያ ሆዬ ጨዋታ በላስታ ላሊበላ፣ ነሐሴ ፳፻፬ ዓ.ም


የነሱ ድፍረት የኛ ፍርሀት ነው

$
0
0

 ሉሉ ከበደ (ደራሲና ጋዜጠኛ)

ሙስሊም ወንድሞቻችን ሁለት አመት ለሚጠጋ ጊዜ እየተገደሉ ነው።  በጽናት፤ በጀግንነትና በብልሀት እናም በመስዋእትነት የመብት ትግላቸውን ቀጥለዋል። በለተ - አውዳመት ኢድ አልፈጥርም የመስዋእትነት ደማቸውን፤ …ኢትዮያን የተቆጣጠራት የትግራይ ዱር አራዊት መንጋ አፍሷል። የሞቱትን ሁሉ አላህ በጀነት ነፍሳቸውን ያኑር ከማለት በቀር ምን ይባላል ?  ለሁሉም ወገኖቻችን ለቤተሰቦቻቸው፤ ለዘመዶቻቸው አላህ ጥናቱን ይስጥ እላለሁ። በከንቱ ለፈሰሰ ደማቸውም እሱ በማያልቅበት ስልጣኑ ፍርዱን ይስጥ። ሳይውል ሳያድር።...አላህ ሁ አክባር!!!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ድምጻዊ እዮብ መኮንን ከዚህ አለም በሞት ተለየ።

$
0
0

ነሃሴ ፲፫(አስራ ሦስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-  ታዋቂው ድምጻዊ እዮብ መኮንን በብስክሌት ላይ ሆኖ ሲጓዝ በመውደቁ ሆስፒታል ከገባ በሁዋላ በህክምና ሲረዳ ቆይቷል።

አርቲስት እዮብ በባልደረቦቹ እርዳታ  ወደ ኬንያ በመሄድ ለአጭር ቀናት በህክምና ሲረዳ ቆይቷል።

ኢሳት በአርቲስት እዮብ ሞት የተሰማውን ሀዘን ለመግለጽ ይወዳል።

በአዲስ አበባ በሳምንት እንድ ቀን ውሀ ማግኘት ብርቅ የሆነባቸው ሰፈሮች መኖራቸው ተዘገበ

$
0
0

ነሃሴ ፲፫(አስራ ሦስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-  “በሳምንት አንድ ቀን ውሃ ማግኘት ብርቅ የሆነባቸው ሰፈሮች፣ በውሃ እጦት አካባቢያቸውን በመጥፎ ጠረን የሚበክሉ የኮንዶሚኒየም መኖሪያዎች፣ ለተደጋጋሚ አቤቱታ ምላሽ ሳያገኙ በርካታ ወራት እየተቆጠሩ የሚማረሩ ነዋሪዎች የአዲስ አበባ የዘመኑ ገጽታ ሆነዋል” ሲል አዲስ አድማስ ዘገበ

የውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ” በቂ ውሃ ስለሌለ በራሽን ለማከፋፈል እየሞከረ” መሆኑን ገልጿል። ባለስልጣኑ ”  የኤሌክትሪክ መቆራረጥና የአንዳንድ ሰራተኞች እንዝህላልነት፣ ለመንገድ ግንባታ የሚቆፈሩ ቧንቧዎች እንዲሁም በከንቱ የሚባክን ውሃ መብዛቱ የውሃ እጥረትን እንዳባባሱ ይናገራል።

የአገሪቱ እንዲሁም የአህጉሪቱ መዲና በሆነችው ከተማ፣  በርካታ ነዋሪዎች የዝናብ ውሃን ደቅኖ ለማጠራቀም ሲሯሯጡና በጀሪካን ተሸክመው ውሃ ሲያመላልሱና የፎቅ ደረጃዎችን ለመውጣት ሲውተረተሩ ማየት የተለመደ ሆኗል የሚለው የአድማስ ዘገባ ፣ በገርጂ፣ አየር ጤና፣ ጀሞ፣ እንቁላል ፋብሪካ፣ አዲሱ ገበያ፣ እንዲሁም በየአቅጣጫው የተገነቡ ኮንዶሚኒየሞችን ጨምሮ በርካታ የከተማዋ ሰፈሮች፣ በውሃ እጥረት የተቸገሩ ነዋሪዎች “አወይ ስልጣኔ” በማለት መላ እንደጠፋባቸው ሲገልጹ ይሰማል ብሎአል።

” ውሃ የሚጠፋበትን ቀን ዘርዝሮ ከመናገር ይልቅ ውሃ የሚመጣበትን ቀን መናገር ፣ በሳምንት አንዴ ውሃ ከመጣ ፌሽታ ነው፤ ብርቅ ይሆንብናል ሲል የአዲሱ ገበያ ነዋሪ የሆነው ልዩነህ አያሌው መናገሩ ተዘግቧል።

አዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሃላፊ ወ/ሮ እፀገነት ተስፋ  በአዲስ አበባ የውሃ ችግር መኖሩን አምነው  ዋናው ምክንያትም የውሃ እጥረት ነው  ብለዋል።

ቴሌ ኮሚኒኬሽን ከቻይናው ዜድ ቲ ኢ ጋር የ 800 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈራረመ

$
0
0

ነሃሴ ፲፫(አስራ ሦስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-  ስምምነቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ሞባይል ስርጭት ተጠቃሚ ወደ 50 ሚሊዮን ለማሳደግ የተደረገ ነው ተብሎአል።

መንግስት ለዘርፉ ከመደበው 1 ቢሊዮን 600 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ ከፊሉን ለሌላው የቻይና ኩባንያ ሀዋይ መስጠቱ ታውቋል።

ሁለቱም የቻይና ኩባንያዎች የመንግስትን የስልክና የሌሎች የመገናኛ መንገዶች ጠለፋ አቅም እንደሚያዳብሩለት ኢሳት ምንጮችን በመግለጽ መዘገቡ ይታወሳል።

የኢህአዴግ ልሳን የሆነው ዋልታ በሰራው ዜና ለ80 ሚሊዮን ህዝብ አንድ ብቻ የስልክ አገልግሎት የሚጠጥ ኩባንያ መኖሩን እንዲሁም በአፍሪካ የቴሌኮሚኒኬሽን አገልግሎትን በመንግስት ቁጥጥር ስር ካደረጉ ጥቂት አገሮች መካከል ኢትዮጵያ አንዷ መሆኑን ዘግቧል።

በቁጫ ወረዳ የሚታሰሩ ሰዎች ቁጥር ጨምሮአል

$
0
0

ነሃሴ ፲፫(አስራ ሦስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-  በወረዳው የተነሳውን ከማንነት ጋር የተያያዘ ጥያቄ ለማፈን መንግስት የጀመረውን ዘመቻ በማጧጧፍ ለውጭ አገር ሚዲያ መረጃ ይሰጣሉ የተባሉትን የቁጫን ህዝብ በመወከል ሲከራከሩ የነበሩት መቶ አለቃ ማሴቢ ማዳልቾ፣ ባለፈው ቀድሜ ተይዘው ዛሬ ወደ አርባምንጭ ተልከዋል።

በአጠቃላይ እየታደኑ ካሉት መካከል 12 አንጋፋና ታዋቂ ሰዎች ሲታሰሩ፣ 9ኙ የገቡበት  አልታወቀም።

በወረዳው የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ የፌደራል ፖሊስ ወደ አካባቢው እንዲሰማራ መደረጉ ይታወሳል።

ለአቶ መለስ ሙት አመት መታሰቢያ የመንግስት ሰራተኞች በግድ እንዲገኙ ታዘዙ

$
0
0

ነሃሴ ፲፫(አስራ ሦስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-  የቀድሞ ጠ/ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ሙት ዓመት በነገው ዕለት በአዲስ አበባ ጉለሌ ዕጽዋት ማዕከል በልዩ ልዩ
ፕሮግራም ታስቦ እንደሚውል ለማወቅ የታቸለ ሲሆን፣ በዛሬው እለት ደግሞ  የተለያዩ የመንግስት ሰራተኞች ምሽትና ነገ  ሻማ በማብራት እንዲዘክሩት ታዘዋል።

አንዳንድ የመንግስት ሰራተኞች  ኢቲቪ አቶ መለስ ዜናዊ ከተናገራቸው ንግግሮች መካከል እያለ ሲያቀርብ መሰንበቱ እንዳሰለቻቸው ተናግረው፣ የፓርቲው ካድሬዎች በየመስሪያ ቤቱ የሚገኙ ሰራተኞች በግድ ተገኝተው እንዲዘክራቸው ማስፈራሪያ አዘል ቅስቀሳ በማካሄድ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ነሃሴ 7 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስአበባ የመለስ ዜናዊ የአረንገዴ ልማት ማዕከል የመሰረት ድንጋይ  በአድዋ
ፓርክ የተጣለ ሲሆን የዚህን ፕሮጀክት ወጪ የአዲስአበባ ከተማ አስተዳዳር ለመሸፈን ቃል መግባቱን መዘገባችን ይታወቃል።

ከሃያት ሆስፒታል ፊት ለፊት ማረፊያውን የሚያደርገው ማዕከሉ ከ100 ሄክታር በላይ ስፋት ሲኖረው ፥  በተለያዩ
የአረንጓዴ ዕፅዋት በመሸፈን በውስጥ ትላልቅ የመዝናኛ ስፍራዎችን ያካትታል ተብሏል።

ባለፉት 15 ቀናት የአዲስአበባና የክልል ከተሞች ነዋሪዎች እና የመንግስት ሰራተኞች ዕለቱን ለማሰብ የችግኝ
ተከላ ማካሄዳቸው የሚታወስ ሲሆን መንግስትም በዚህ አጋጣሚ የመለስን ሌጋሲ ለማስቀጠል የገባውን ቃል ዳግም
ያደሰበት አጋጣሚ መሆኑን በመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሲናገር ከርሟል።

አቶ መለስ ዜናዊ ታምመው በሕክምና ሲረዱ መቆየታቸው በከፍተኛ ሚስጢር ተይዞ ከቆየ በኃላ ነሃሴ 14 ቀን 2004
ዓ.ም መሞታቸውን መንግስት በይፋ ማመኑ የሚታወስ ነው፡፡

ገዢው ፓርቲ የአቶ መለስን ሞት ለፖለቲካ ድጋፍ ማስገኛ እየተጠቀመበት ነው በሚል ሲተች ቆይቷል። አቶ መለስ በኢኮኖሚው ዘርፍ መጠነኛ ለውጥ እንዳመጡ ቢነገርላቸውም፣ የኢትዮጵያን ህዝብ አንድነት በማዳከም፣ አገሪቱን ወደብ አልባ በማድረግና የሰብአዊ መብቶችን በመጣስ ይወቀሳሉ። በህይወት በነበሩበት ጊዜ በተለይም ኢፈርት የተባለ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ተቆጣጥሮ ዬያዘ የንግድ ኩባንያ እንዲቋቋም በማድረግ አንድን ብሄር ብቻ ለመጥቀም ተንቀሳቅሰዋል እየተባሉ በተቃዋሚዎቻቸው ይተቹ ነበር።

ባለቤታቸው ወ/ሮ አዜብ መስፍን የመለስን ፋውንዴሽን በበላይነት እየመሩ ይገኛሉ።


የሽብርተኝነት አዋጁ፤ የጠሉትን መምቻ?

$
0
0


ተመስገን ደሳለኝ

ኢህአዴግ ባለፉት ሃያ ሁለት ዓመታት በስራ ላይ ካዋላቸው አዋጆች መካከል የ‹‹ፀረ-ሽብር ህጉ››ን ያህል ያጨቃጨቀ የለም ቢባል ከእውነቱ ብዙም አልራቀም፡፡ በርግጥ ከተቃውሞ አቅራቢው አብዛኛው በደፈናው ‹‹ህጉ አያስፈልግም›› የሚል አልነበረም፡፡ ህጉ ‹‹ሽብርተኝነት››ን የገለፀበት መንገድና አንዳንድ አንቀፆቹ ለትርጉም አሻሚ በመሆናቸው ከስርዓቱ ባህሪ አኳያ ለፖለቲካ ጥቅም የሚውሉበት ዕድል መኖሩ አይቀሬ ነው የሚል ስጋት ነበር፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አባይ ወልዱ እና አስገደ ገብረሥላሴ በሃገር ጉዳዮች ላይ –ኦገስት 19, 2013

$
0
0
Abbay Woldu, President of Tigray and Asgede Gebreselassie, Founde of TPLF and Medrek Exec. Committee member on National issues.…

Hiber Radio: ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ትናንት በቨርጂኒያ ስለተደረገው ሃገራዊ የውይይት መድረክ ተናገረ

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ ዕሁድ ነሐሴ 12 ቀን 2005 ፕሮግራም

<<...የኢትዮጵያ ወዴት እያመራች ነው ምንስ መውጫ ቀዳዳ አላት ፓርቲዎች ምን ያስባሉ ? ሲቪክ ተቋማት ምን ያስባሉ በሚል ለምክክር የተጠራ ስብሰባ ነው። ...አሁን ያለውን የሁሉንም ሀሳብ ሰብስበን ለሕዝብ የምናቀርብበት ነው። ሕዝብ እያንዳንደን ነገር ይከታተልና ከዚያ በሁዋላ አንድ አቋም ወይ አንድ የትግል ስትራቴጂ የሚነደፍበትን መድረክ እናዘጋጃለን ይሄ አይን ገላጭ ነው። የአቋም መግለጫ ባይጠበቅም...>>

ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ኢሳት የጠራውን በአገር ውስጥና በውጭ ያሉ አብዛኞቹን የዲሞክራሲ ሀይሎች ያሳተፈውን አገራዊ የውይይት መድረክ አስመልክቶ ከህብር ሬዲዮ ተጠይቆ ከሰጠው ማብራሪያ (ሙሉውን ያዳምጡት)

<<...ቤሄ ሃይማኖታዊና ባህላዊ መልክ አለው።ለመሆኑ የቡሄ ሀይማኖታዊ መሰረት ምንድነው? የሆያሆዬው ጭፈራስ? ለመሆኑ ችቦ ማብራቱስ? ...ቡሄን አስመልክቶ ከብጹ አቡነ ዮሴፍ የኔቫዳ፣የአሪዞናና የዩታ አገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ም/ዋና ጸሐፊ ጋር ተወያይተናል። ሙሉውን ያዳምጡ

<<...በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን፣የሲቪክ እና የፖለቲካ ድርጅቶች በግብጽ የምንገኝ ኢትዮጵያውያን ያለብንን ችግር አስመልክተው ድምጻችንን ጄኔቭ ለሚገኘው ለዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር ጽ/ቤት ሊያሳውቁልን ይገባል...አሁን መንቀሳቀስም አልቻልንም ከፍተኛ ስጋት አለን ትልቅ መድልዎም በዩ.ኤን በኩል ይደረግብናል...>>

አቶ አስናቀ ሞላ በግብጽ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ማህበር የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ

<<...አስቸጋሪ የሚሆነው መንግስት በሙስና ላይ ዘመቻ ይዟል የሚለው አይደለም።በተግባር በሚታይበት ጊዜ ማን የሙስና ወንጀል ይመለከተዋል? ከፍተኛ የፓርቲውና የመንግስት ባለስልጣኖችን ይመለከታል አይመለከትም? ቤተሰቦቻቸውን ይመለከታል አይመለከትም? የጦር ሀይሉን አዛዦች ይመለከታል አይመለከትም? የሚለውን ማየት ይኖርብናል ለፖለቲካ ተብሎ የሚወሰደው እርምጃ ዝቅተኛ ሙሰኞቹን እንጂ ከፍተኞቹን አይነካም...>>

ዶ/ር አክሎግ ቢራራ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከህብር ሬዲዮ ጋር ካደረጉት ቃለ ምልልስ(ክፍል አንድ የተወሰደ.) ሙሉውን ያዳምጡት (ሌሎችም ቃለ መጠይቆች አሉን)

ዜናዎቻችን
- የሙስሊሙ ትግል አስተባባሪዎች የአገዛዙን <<ሼህ ኑሩን ማን ገደላቸው ድራማ አወገዙ

- በሼሁ ሞት የመንግስት እጅ እንዳለበት ጥርጣሬ ማጫሩን ገለጹ

- ቦሌን ከፈንጂ አደጋ አዳንነው ሲሉ የአገዛዙ የጸጥታ ሰዎች ገለጹ

- ሕዝቡ ኢቲቪ ድራማውን ጀመረ እያለ ነው

- በሳዑዲ አጎቴን ገድያለሁ ያለው ኢትዮጵያዊ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ

- ድምጻዊ እዮብ መኮንን አረፈ

- የግብጽ የሽግግር መንግስት የሙስሊም ወንድማማቾችን በሕግ ለማገድ ማሰቡን ገለጸ

ሌሎችም ዜናዎች አሉን

ESAT Radio: Aug 19

$
0
0
  ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ ለምን አያስፈራ?

$
0
0

ግርማ ሠይፉ ማሩ

"የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ ለምን ያስፈራል?" በሚል ርዕስ ሪፖርተር ጋዜጣ በእሑድ ነሓሴ 5 ህትሙ ረጅም ፅሁፍ አሰነበቦናል። ፀሐፊው በቦነያ ሰ. በሚል አቶ/ወሪት/ወሮ ይሁን በማይታወቅ ስም ነው ያወጡት። ይዘቱን ሳነበው የምናውቃቸው የኢህአዴግ ሹሞች በብዕር ስም ልከውት ያው የኢህአዴግ አቋም ነው ብዬ ለመውሰድ ዝግጁ ሆኜ ንባቤን ሳጠናቅቅ፤ ፀሐፉው የሕግ ባለሞያ እንዲሁም በተለያየ የመንግሥትና መንግታስዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ውስጥ በሙያቸው ሰርተዋል የሚለው የአዘጋጁ ማስታወሻ መልስ እንድሰጥ ጋበዘኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

Viewing all 13695 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>