Quantcast
Channel: Amharic News & Opinion
Viewing all 13695 articles
Browse latest View live

የኛ ሰው በካንጋሮ ምድር

$
0
0
7, 617, 930 ስኩዌር ኪሎ ሜትር በምታካልለው ሰባተኛ አህጉር፣ በስፋቷ የዓለማችን ስድስተኛ ሀገር በሆነችው አውስትራልያ ውስጥ እገኛለሁ፡፡  አንድ አህጉር አንድ ሀገር ሲሆን አውስትራልያ በዓለማችን ብቸኛዋ ትመስለኛለች፡፡ የሚገርመው ግን ይህንን የሚያህል ሰፊ ሀገር ውስጥ የሚኖሩት ሃያ ሁለት ሚሊዮን ሰዎች ብቻ መሆናቸው ነው፡፡ ‹አይሆንም እንጂ ቢሆንማ› እንደሚባለው ቢቻል ኖሮ ከአውስትራልያ ይዤ ወደ ሀገሬ የምገባው የቤት መሥሪያ መሬት ነበር፡፡ እዚያ የወባ ክኒን የምታክል መሬት ለማግኘት የቀበሌ መታወቂያ፣ 10/90፣ 20/80፣ ባንክ ቤት፣ ወረፋ፣ ምዝገባ፣ ዕጣ፣ መከራ እያሳየን እዚህ መሬት የካንጋሮ መጨዋቻ ሆኖላችኋል፡፡ ‹አስወስጄ መጣሁ አስወስጄ› የሚለው ዘፈን ባህል ነውና እኛ የባሕር በራችንን አስወስደን ትንሷን ጅቡቲ ስንለማማጥ እንኖራለን፤ የዓለማችን ትልቋ ደሴት የምትባለው አውስትራልያ 34,218 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የባሕር ጠረፍ ባለቤት ናት፡፡ አውስትራልያ የሚለው ስም ከላቲኑ ‹‹አውስትራሊስ› የመጣ መሆኑንና ትርጉሙም ‹ደቡባዊ› ማለት እንደሆነ ይነገራል፡፡

በስድስት ክልሎችና በሁለት ልዩ ግዛቶች የተመሠረተችው ይህች ፌዴራላዊት ሀገር ራሳቸውን ‹አውሴ› ብለው የሚጠሩት የዛሬ ዋነኛ ነዋሪዎቿ ከመምጣታቸው በፊት ‹አቦርጅን›[አዳሙ ተፈራ የሚባል አውስትራልያ የሚኖር ደራሲ - ‹ኑር ተገኝ› ብሎ ጠርቷቸዋል፡፡] የተባሉ ጥንታውያን ሕዝቦች ይኖሩባት የነበረች ሀገር ናት፡፡ እነዚህ ከእስያ መጥተው ከብዙ ሺ ዓመታት በፊት የኖሩት ባላገሮቹ ዛሬ በሰሜናዊ አውስትራልያ በሚገኘው ‹የሰሜን ግዛት› በሚባለው ልዩ ክልል ውስጥ በብዛት ይገኛሉ፡፡ እንግሊዞች ወደዚች ሀገር ሲመጡ ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጋ ቁጥር ነበራቸው የሚባሉት አቦርጅኖች በደረሰባቸው ግፍና መከራ የተነሣ ቁጥራቸው መንምኗል፡፡ ለመሬታቸው ሲባል ተሰድደው፣ ተገድለውና በበሽታ እንዲያልቁ ተደርገው ሀገራቸውን አጥተዋል፡፡ በ1787 ዓም የተነሣውና መጤዎቹ ሆን ብለው ወደ አቦርጅኖች እንዲደርስ አድርገውታል የሚባለው ፈንጣጣ ብቻ ‹ዳሩግ› ከሚባሉት የአቦርጅን ጎሳዎች መካከል ዘጠና በመቶውን ፈጅቷቸዋል፡፡ [የኡጋንዳው ዩዌሪ ሙሴቪኒ ነጮች በአፍሪካ ላይ በመድኃኒት ጥቁሮችን እንዳይጨርሱ ያደረጋቸው ከብት አርቢ መሆናችን ነው፡፡ ብዙውን በሽታ ከብቶቹ ወስደውታል፡፡ ከከብት ጋር በመኖራችንም የመቋቋም ውሳጣዊ ዐቅም ገንብተናል ብለው ነበር፡፡] ልጆቻቸውን ለጉልበት ሥራ አስገድዶ በመውሰድ፣ እንዳይወልዱ የማምከኛ መድኃኒት በመስጠት፣ የመጠጥ ሱሰኞች ሆነው እንዲቀሩ በማድረግ አቦርጅኖች ከሀገር እንዲጠፉና ቁጥራቸው እንዲቀንስ ተደርጓል፡፡ በዚህ ምክንያት በሁለት መቶ ዓመታት ውስጥ እየጠፉ መጥተው በ1900 ዓም አካባቢ ቁጥራቸው ወደ 96 ሺ ወርዶ ነበር፡፡ አሁን ከጠቅላላው ሕዝብ 2 በመቶ ብቻ ናቸው፡፡ እሥር ቤት ስሄዱ ግን 25% እሥረኞች እነርሱ ሆነው ታገኛላችሁ፡፡ ልክ በአሜሪካ አፍሪካ አሜሪካውያን ከጠቅላላ ሕዝቡ 30 በመቶ ቢሆኑም እሥር ቤት ግን 60 ከመቶ እንደሆኑት ዓይነት ማለት ነው፡፡ 
አንዳንድ ጊዜ ለነጻነታችን ለተዋጉት አርበኞች ክብር የምትሰጡት ይህን መሰል የመከራ ታሪኮችን ስትሰሙ ነው፡፡ ‹በኋላ የመጣ ቀንድ በፊት የመጣን ጆሮ በለጠው› እንደተባለ በኋላ ሀገር የወሰዱት ዜጎች ክብሩንም፣ ነጻነቱንም፣ ኢኮኖሚውንም፣ ሥልጣኑንም ነጥቀውት ባላገሩን ሁለተኛ ዜጋ ሲያደርጉት ስታዩ ‹ነጻነት ሆይ ዋጋሽ ምን ያህል ነው?› ትላላችሁ፡፡ አንዳንድ ወገኖቼ ‹ጥቂት ቅኝ ብንገዛ ኖሮ እንሠለጥን ነበር፣ እናድግም ነበር› ብለው ይቆጫሉ፡፡ በእሳት የሚጫወት የአበራሽን ጠባሳ ያላየ ብቻ ነው፡፡ ባይሆን እኛ ‹ነጻነትን አላግባብ በመጠቀም ወንጀል›› ልንቀጣ የሚገባን ሕዝቦች ነን፡፡ ነጻነታችንን ለዕድገትና አንድነት፣ ለብልጽግናና ለመልካም አስተዳደር ከመጠቀም ይልቅ ለጦርነት ተጠቅመንበታል፡፡ የውጭ ወራሪዎችን ተከላክለን ራሳችን በራሳችን ስንዋረር ኖረናል፡፡ ነጻነትን ለጦርነት የመጠቀም ልማዱ አልለቀን ስላለም በአንጻራዊነት የመብት ነጻነት ተከብሮባቸዋል ወደሚባሉት ሀገሮች ስንገባ እንኳን ‹የዘሬን ያንዘርዝረኝ› ብለን ጦርነቱን ቀጥለነዋል፡፡ በሀገር ቤትም ሆነ በውጭው ዓለም ያሉ የፓርቲና የኮሙኒቲ፣ የሚዲያና የኪነ ጥበብ፣ የቤተ እምነትና የማኅበራዊ ተቋማት አደረጃጀቶቻችን ሁሉ የጦርነት አደረጃጀቶች ናቸው፡፡ የህልውናችን መሠረቱ ጠላት ነው፡፡፡ ያለ ጠላት ህልው መሆን ስለማንችል ጠላት ካጣን ጠላት እንፈጥራለን፡፡
‹እንግዳ ሆነሽ ትመጭ ባለቤት ሆነሽ ትቆጭ› እንደሚባለው በኋላ ዘመን የመጡትና ባለቤትነቱን የወሰዱት እንግሊዞች እነዚህን ነባር ሕዝቦች እንዳይድኑ አድርገው ሰብረዋቸዋል፡፡ ዛሬ ምንም እንኳን ችግሩ የተቀረፈ፣ መንግሥትም ለተፈጸመው ግፍ ይቅርታ የጠየቀ፣ እነርሱን የሚደግፍ ሕግም ያወጣ ቢሆን አካላዊ፣ ባህላዊና ሞራላዊ ህልውናቸውን እንዲያጡ በመደረጉ የተነሣ ወደ ጥንቱ ክብራቸው ለመመለስ አልቻሉም፡፡ እንግሊዞቹ እነዚህን ሕዝቦች ከምቹ የመኖርያ ሥፍራዎች በማስለቀቅ ወደ በረሃማውና ለኑሮ አስቸጋሪ ወደሆነው አካባቢ ገፍተዋቸዋል፡፡ ለብዙ ዘመናት ትምህርትና ሥልጣኔ እንዳይቋደሱ ተደርጓል፡፡ ከዚህ ይልቅ መጠጥና አደንዛዥ ዕጽ በአካባቢያቸው እንዲስፋፋ አድርገዋል፡፡ የቤተሰብን ማኅበራዊነት በመበተን ወላጆችና ልጆች እንዲለያዩ አድርገዋል፡፡ እነዚህ ሁሉ ተደምረው ዛሬም የአውስትራልያ አቦርጅኖች በሀገራቸው ሙሉ በሙሉ የሚያዝዙ አልሆኑም፡፡
ከአውሮፓውያን መካከል አውስትራልያን ለመጀመሪያ ጊዜ የጎበኛት ሆላንዳዊው አሳሽ ዊልያም ጃንስዘን ነው፡፡ ዊልያምስ በሰሜን አውስትራልያ የረገጠውን መሬት ‹አዲሲቷ ሆላንድ› ብሎ ሰየመና የሀገሩ ግዛት አደረጋት፡፡ እርሱን ተከትሎ ወዲያው የመጣ አውሮፓዊ ሠፋሪ ግን አልነበረም፡፡ ከእርሱ በኋላ ዊልያም ዳምፐር የተባለ እንግሊዛዊ በሰሜናዊ ምዕራብ አውስትራልያ በ1688 ደረሰ፡፡ እንግሊዞች ወደ አውስትራልያ እግራቸውን መስደድ የጀመሩት ከዚያ ጊዜ በኋላ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ በ1770 ጄምስ ኩክ በተባለ መቶ አለቃ አማካይነት ወደ ምሥራቃዊው አውስትራልያ ክልል በመምጣት በእንግሊዙ ንጉሥ ጆርጅ ሦስተኛ ስም አካባቢውን ያዙና ‹ኒው ሳውዝ ዌልስ› ብለው ጠሩት፡፡
እንግሊዞች ወደ አውስትራልያ ፊታቸውን እንዲያቀኑ ያደረጓቸው ብዙ ምክንያቶች ነበሩ፡፡ በአንድ በኩል የአሜሪካ ግዛታቸው ነጻ መውጣት የእርሻ ቦታቸውን ነጥቋቸዋል፡፡ ስለዚህም ሌላ ቦታ በማፈላለግ ላይ ነበሩ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ወንጀለኞቻቸውን ያሥሩባት የነበረችው አሜሪካ ነጻ መውጣቷ ሌላ የወንጀለኞች ማሠሪያ እንዲያፈላልጉ አስገድዷቸው ነበር፡፡
እንግሊዞች ወታደሮቻቸውንና ወንጀለኞችን ይዘው በ1788 ዓም ወደ አውስትራልያ በመምጣት በሲድኒ በኩል አካባቢውን እያጸዱ መቆጣጠር ጀመሩ፡፡ በአሜሪካ የባሮችን ጉልበት ያጡት እንግሊዞች በአውስትራልያ የእሥረኞችን ጉልበት መጠቀም ጀመሩ፡፡ እየቆዩም ከተለያዩ ሀገሮች የመጡ ስደተኞች ተቀላቀሏቸው፡፡  
ዛሬ በአውስትራልያ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ከ220 በላይ ሀገር ሰዎች ይኖሩባታል፡፡ ምንም እንኳን ዋናው ኦፊሴልዊ ቋንቋዋ እንግሊዝኛ ቢሆን ከ224 ቋንቋዎች በላይም ይነገሩባታል፡፡ የፌዴራል ሥርዓት የምትከተለው አውስትራልያ የሀገሪቱ ርእሰ ብሔር የእንግሊዟ ንግሥት ናት፡፡ (በነገራችን ላይ ንግሥቲቱ ካናዳን ጨምሮ የ16 ሀገሮች ርእሰ ብሔር ናት) የ2006 ዓም የሀገሪቱ የቆጠራ ውጤት እንደሚገልጠው ከሕዝቡ ቁጥር ሩብ ያህሉ ከተለያየ ሥፍራ መጥቶ የሚኖር ነው፡፡ ጣልያኖች፣ ቻይናዎች፣ ቬትናሞች፣ ሕንዶችና ፊሊፒኖች ከስደተኞቹ መካከል ከፍተኛውን ቁጥር ይይዛሉ፡፡ ከአፍሪካ አህጉር ብቻ ከ48 ሀገሮች የመጡ ስደተኛ ነዋሪዎች በአውስትራልያ ይገኛሉ፡፡
በ2006 ዓም የተደረገው የአውስትራልያ ሕዝብ ቆጠራ በሀገሪቱ 7516 ኢትዮጵያውያን እንደሚኖሩ ይገልጣል፡፡ ነባር ነዋሪ ኢትዮጵያውያን ግን ቁጥሩን የዚህ ሦስት እጥፍ አካባቢ ያደርጉታል፡፡ ኢትዮጵያውያኑ ለቆጠራው ቅጽ ትኩረት ባለመስጠታቸው እንደማይሞሉት፣ አንዳንዶቹም የቋንቋው ችግር ሳይረዱት እንዲቀሩ እንደሚያደርጋቸው፣ ሌሎቹም ከቆጠራው በኋላ በብዛት መምጣታቸውን እንደ ምክንያት በመውሰድ የኢትዮጵያዊውን ቁጥር እስከ ሃያ ሺ ያደርሱታል፡፡ የአውስትራልያ መንግሥት ቆጠራ እንደሚያሳየው 26 በመቶዎቹ የሀገሬ ልጆች በሹፍርናና ማሽኖችን በማንቀሳቀስ፣ 24.3 በመቶዎቹ በጉልበት ሥራ፣ 16.3 በመቶዎቹ በአገልግሎት ዘርፍ፣ 33.5 በመቶዎቹ ደግሞ በአስተዳደር፣ በጸሐፊነት፣ በቴክኒክ ሥራ፣ እንዲሁም በሌላ ሞያ ነክ ሥራ መሠማራታቸውን ያሳያል፡፡ በሀገሪቱ ከሚኖሩት ኢትዮጵያውያን መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት እዚህ እኔ ያለሁበት ቪክቶርያ ግዛት፣ ሜልበርን ከተማ ውስጥ የሚኖሩ ናቸው፡፡
አዳሙ ተፈራ ‹ገመናችን በሰው ሀገር› ብለው በጻፉት መጽሐፍ ላይ እንደገለጡት ወደ አውስትራልያ ለመጀመሪያ ጊዜ የገቡት ኢትዮጵያዊ አቶ አዲስ ታምሩ ይባላሉ፡፡ እኒህ በ1965 ዓም ወደ አውስትራልያ የገቡት የኢትዮጵያ አየር ኃይል ባልደረባ ለትምህርት መጥተው ነው በዚሁ የቀሩት፡፡ ዛሬ ከሀገሩ ነባር ነዋሪ (አቦርጅን) ጋር ተጋብተው ይኖራሉ፡፡
እዚህ የሚኖሩ የሀገሬ ልጆች ብዙ አስገራሚ፣ ብዙ አስቂኝ፣ ብዙም አሳዛኝ ገጠመኝ አላቸው፡፡ እድሜና ጤና ከሰጠን አብረናቸው እናዝናለን፣ እንስቃለን፣ እንሳቀቃለንም፡፡
ሜልበርን፣ አውስትራልያ

ESAT News 21 August 2013

ዋ! እዮብ መኮንን! – ‹‹እግዚአብሔርን ባገኘው የምጠይቀው የዘላለም ሕይወት እንዲሰጠኝ ነው››

$
0
0

eypbበአቤል ዓለማየሁ

ጊዜው ከአምስት ዓመት በፊት ነው፤ በሚሊኒየሙ፣ ሚያዚያ ወር የመጀመሪያ ሳምንት፡፡ ሠራበት በነበረው ጐግል ጋዜጣ ‹‹ጥበብ›› አምድ ላይ እንግዳ ላደርገው ረፋድ ላይ ወደ እዮብ መኮንን የእጅ ስልክ መታሁ፡፡ መልካም ፈቃዱን ገለጾ… አንጃ ግራንጃ ሳያበዛ ‹‹ከተመቸህ ዛሬ መገናኘት እንችላለን›› አለኝ፡፡ ትንሽ መዘጋጀት እንዳለብኝ ነግሬው ዛሬ ከሆነ ምሽት ላይ መገናኘት እንደምንችል ነገርኩት፡፡ ጥያቄዎች ሳሰባስብ እና ሳሰላስል ዋልኩ፡፡ የቀጠሮ ቦታ ስላልቆረጥን ከመገናኘታችን በፊት ልደውልለት ተስማማን፡፡ ደወልኩለት!

‹‹ፒያሳ አካባቢ ነኝ፡፡ እዚህ መምጣት ትችላለህ?›› (እዮብ)
‹‹መልካም ግን ትንሽ እንዳልቆይብህ መገናኛ አካባቢ ነኝ፡፡ መሀል ላይ መገናኘት ከቻልን መልካም ነው፡፡ አለበለዚያ ግን ልምጣ››
‹‹እሺ! የት እንገናኝ? መኪና ይዘሀል?››
‹‹መኪና? ይሄ አራት ጎማ ያለው ነገር?››
‹‹ይስቃል››
‹‹አለኝ ግን butter fly ነው፡፡ (የልብስ ስፌት መሆኑን ልብ ይሏል፡፡) ከቤት ውጪ አልነዳውም››
እየሳቀ ‹‹እሺ! የት ልምጣልህ››
‹‹ዑራዔል አካባቢ አማካይ ስፍራ ነው፡፡ ፕላዛ ሆቴል እንገናኝ?›› እውነት ለመናገር እኔ የነበርኩት ፕላዛ አካባቢ ይገኝ የነበረው ቢሯችን ውስጥ ነበር፡፡ የጀመርኩትን ሥራ ሳጠናቅቅ፣ ኮምፒውተር ስዘጋጋ፣ እንዳልቆይበት ብዬ ግርጌዬ ላይ እንዲመጣ ጨከንኩበት፡፡ የሚገርመው እኔ ቢሮ ስድበሰበስ እሱ ቀድሞ ፕላዛ ደረሰ፡፡ ሮጥ ብዬ ስደርስ ሆቴሉ ግቢ ውስጥ ጥቁር ቪታራ መኪናውን እየዘጋጋ ነበር፡፡ ሆቴሉ ምግብ አዳራሽ ውስጥ ገበታ ሳይቆርሱ መስተናገድ ባይፈቀድም ቃለ ምልልስ ለመስራት ሳስፈቅድ ይሁንታ አገኘሁ፡፡ የሆቴሉ ባልደረቦች ድሬድ ጸጉሩን የተሸለተውን እዮብን እያዩ ‹‹እሱ ነው/አይደለም›› እየተባባሉ ነበር፡፡
አማርኛ፣ ትግሪኛ፣ ኦሮምኛና ሱማሊኛ ቋንቋዎችን አቀላጥፎ እንደሚናገር የነገረኝ እዮብ ቃለ ምልልሱን ከመጀመሬ በፊት ማስጠንቀቂያ አስቀመጠ፡፡
‹‹በድምጽ መቀዳት ስለማልፈልግ፣ ወረቀት እና እስክሪብቶ አውጣ››
‹‹ለምን››
‹‹ከዚህ በፊት ያላልኩትን ብለው መጽሔት ላይ ስላወጡ ይሄን ስህተት መድገም አልፈልግም፡፡ ስለዚህ እየጠየቅከኝ መልሱን ጻፍ!››
‹‹እኔ እንዲህ እንደማላደርግ ከመቶ ፐርሰንት በላይ ቃል ልገባልህ እችላለሁ››
‹‹ኖ! አይሆንም››
ላሳምነው ሞከርኩ፡፡ ሊዋጥለት አልቻለም፡፡ በዚያው ሰሞን አንድ መጽሔት ያልዘፈነውን ራጋ ‹‹የራጋ ስልት ያለው እንትን የተሰኘ ዘፈኑ›› እያለ አልበሙን ጥንብ ርኩሱን አውጥት ስለነበር ፕሬሱ ላይ ያለው እምነት የበለጠ እንዲሸረሸር አድርጎታል፡፡ የመጨረሻ አማራጭ ልሰጠው ጉሮሮዬን ጠረግኩ፡፡
‹‹እውነት ለመናገር መልስህን በቃል እየጻፍኩ አልዘልቀውም፡፡ በዚህ ላይ እኔ እስክፅፍ ስትጠብቅ ሃሳብህ ይቆራረጣል፡፡ ለዛ ቢስ ቃለ ምልልስ ይሆናል፡፡ ማድረግ ያለብኝ [ተገቢ ነው ብዬ ባላምንም] እስከዛሬም ለማንም አድርገነውም ባናውቅም ድምጽህን ወደ ወረቀት ከገለበጥኩ በኋላ (After transcription) አምጥቼ ላሳይህ እችላለሁ፡፡ አለበለዚያ ግን በቃል…››
አመነታ፡፡ እንደምንም አሳመንኩትና ‹‹ሽጉጤን›› ተረክ አደረግኳት [ለእንደ እኔ አይነት ጋዜጠኛ ተብዬ ሽጉጡ ድምጽ ማስቀሪያው ነች፡፡] አወራን፡፡ በቀጣዩ ቀን ምሽት ላይ ይሰራበት የነበረው ፋራናይት ክለብ (ልምምድ ላይ የነበረ ይመስለኛል) ወስጄ አሳየሁት፡፡ አነበበውና ምንም ሳያንገራግር በደስታ ሸኘኝ፡፡ ከዚያም የሚያዚያ 10/2000 ዓ.ም ጐግል ጋዜጣ ላይ ጨዋታውን ዳርኩት፡፡ ካወራናቸው ውስጥ ጥቂቱን እንካችሁ፡፡

የተለያዩ አይነት የሬጌ ስልቶች አሉ፡፡ አንተ የምትጫወተው የትኛውን አይነት ነው ትክክለኛ (Pure የሆነውን) ሬጌ ትጫወተዋለህ
ሬጌ የተለያየ አይነት ስታይል አለው፡፡ ሩትስ፣ ስካ፣ ዋን ድሮፕና ሌሎችም አሉ፡፡ የምቱ ሁኔታ ነው ሩት፣ ስካ… ሊያስብለው የሚችለው፡፡ እኔ ሁሉንም የሬጌ ቶን እጫወታለሁ፡፡ ስለ እኔ መናገር ቢከብደኝም ሙዚቃ የሚያውቁ ሰዎች በአብዛኛው በትክክል እንደምጫወተው ይናገራሉ፡፡

‹‹ይዞ የመጣው ለአገራችን አዲስ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሊያሰልፈው የሚችል አዘፋፈን ነው፡፡ ሬጌ የሚፈልገው ነገር አለው፡፡›› ተብሎ ስለ አንተ የተጻፈ ጽሁፍ አንብቤያለሁ፡፡ በዚህ ትስማማለህ?
ጸሐፊው ያመነበትን ጽፏል፡፡ እኔ ከምናገር አድማጭ ቢፈርድ ጥሩ ነው፡፡

በሙዚቃ ስራህ ላይ ተጽዕኖ ያሳደረብህ ሰው አለ?
አሊ ቢራ እና ቦብ ማርሌይ በጣም የምወዳቸው ድምጻዊያን ናቸው፡፡ የእነሱ ተፅዕኖ አለብኝ፡፡ የሁለቱንም ዘፋኞች ዘፈን ከልጅነቴ ጀምሮ እሰማም፣ እዘፍንም ነበር፡፡

ሬጌ ሙዚቃ መጫወት ያለበት ሰው ምን ማሟላት አለበት?
መጀመሪያ ሙዚቃውን ማፍቀር አለበት፡፡ ከዚያም በደንብ መስማትና ደጋግሞ ልምምድ መሥራት ይኖርበታል፡፡

በአልበምህ ላይ የሰራሀቸው ዜማዎች ተመሳሳይነት አላቸው ይባላል፡፡
በፍጹም አይመሳሰሉም፡፡ ለአንድ የውጪ አገር ዜጋ የትግሪኛ ዜማ ብታሰማው ሁሉም አንድ ዓይነት ነው የሚመስለው፡፡ የእኔም እንደዚያው ነው፡፡ አሰማማችን ነው እንጂ ዜማዎቹ አይመሳሰሉም፡፡

አልበምህ ያሰብከውን ያህል ተደምጧል?

ገና ነው ብዬ ነው የማስበው፡፡ ሰውም በበቂ ሁኔታ የሰማው አይመስለኝም፡፡ የተወሰነ ሰው ግን ሰምቶታል፡፡

ለምሳሌ የሚካያ በኃይሉ አልበም ከወጣ ጀምሮ (1999 ዓ.ም.) የወደዱት ቢሆንም ይበልጥ የተሰማው እየቆየ ሲሄድ ነው፡፡ ያንተም አልበም እንደዚያ…
እመኛለሁ ግን እንደዚያ ይሆናል ብዬ አላስብም፡፡ አምላክ ነው የሚያውቀው፡፡

‹‹እዮብ በአብዛኛው የሚጫወተው የሬጌ ዘፈኖችን ስለሆነ ጸጉሩ መለያው ነበር፡፡ ሲቆረጠው ዘውዱን የተገፈፈ ንጉስ መስሏል ያሉኝ አሉ፡፡

ለእነሱ የሚታያቸው እንዳልከው ሊሆን ይችላል፡፡ እኔ ግን በመቆረጤ ደስተኛ ነኝ፡፡

መቼና ከማን ጋር ስትሆን ደስ ይልሀል?

ለብቻዬ፣ ከጓደኞቼ ጋር ስሆንና መጽሐፍ ቅዱስ ሳነብ ደስ ይለኛል፡፡ ሁሌም አዲስ ስለሆነ ባነበብኩት ቁጥር ይገርመኛል፡፡ ያነበብከውን መተግበር ስትጀምር ይበልጥ አዲስ ይሆንብሀል፡፡ ሌላ መጽሐፍ ማንበብ ትቼያለሁ፡፡

eyob mekonen 2ትልቁ ራዕይህ ምንድን ነው?
አላውቀውም፡፡ ዛሬን ብቻ መኖሬን ነው የማውቀው፡፡ በፕሮግራም ነገ እንዲህ አደርጋለሁ አልልም፡፡ አስተማሪና መካሪ ዘፋኝ ብሆን ደስ ይለኛል፡፡ ስለ ነገ የሚያውቀው እግዚአብሔር ነው፡፡

አሁን የምትኖረው ሕይወት እና ያለህበት ደረጃ የምትፈልገውን ዓይነት ነው?

ኑሮዬ ይበቃኛል ማለት ትልቅ ነገር ነው፡፡ ደስተኛ ነኝ፡፡ ሕይወት ደግሞ የምትጣፍጠው አማራጭ ስታጣ ነው፡፡ በሕይወቴ ከዚህ በላይ ብሆንም ካለሁበትም ዝቅ ብልም ምንም አይመስለኝም፡፡ አማራጩ እግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡

በቆይታችንየእግዚአብሄርንስምደጋግመህአንስተሀል፡፡ብታገኘውበቀዳሚነትየምታነሳለትጥያቄምንድንነው?
የዘላለም ሕይወት እንዲሰጠኝ ነዋ!

በደረሰበት ደንገተኛ ህመም ቅዱስ ገብርዔል ሆስፒታል ሲታከም የነበረው ከዚያም ለተሻለ ሕክምና ወደ ናይሮቢ አቅንቶ ሳይነቃ በሳምንቱ መጨረሻ ሕይወቱ ያለፈው ተወዳጁ ድምጻዊ እዮብ መኮንን ጋ ያኔ በተገናኘንበት ወቅት አልበሙ እንዲህ ይገናል ብሎ አላሰበም፡፡ ‹‹ታያለህ እንደ ሚካያ አልበም ነው የሚሆነው›› ብዬ ‹‹ስጠነቁል›› አልመሰለውም ነበር፡፡ ሥራው ከገነነ በኋላ ‹‹አላልኩህም ነበር!›› ብዬ ከመፎከር አልቦዘንኩም፡፡ አንድ ቀን አጋጣሚ ቦሌ አካባቢ አግኝቼው አንድ ካፌ ትንሽ ተቀምጠን አወራን፡፡ አወራን ከማለት ይልቅ መጽሐፍ ቅዱስ ሲሰብከኝ ነበር ማለት ይቀላል፡፡ ልቡ ተሰብሮ፣ ግንኙነቱ ከአምላኩ ጋር ብቻ ይመስል ነበር፡፡ ዛሬ በ9 ሰዓት በሥላሴ በተፈጸመው የቀብር ስነ-ስርዓቱ ላይ ጥቅምት 12/1967 ዓ.ም. መወለዱ የተነገረው እዮብን ሁኔም በማይሰለቹ ዜማዎቹ እናስታውሰዋለን፡፡ በርካታ ሰውም በቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በመገኘት ሀዘኑን ገልጿል፡፡ እንደተመኘውም በላይኛው ቤት ‹‹የዘላለም ሕይወት እንዲሰጠው›› እመኛለሁ፡፡ ዋ! እዮብ! ከልቤ አዝኛለሁ! ነፍሱን ይማረው!

መለስና ደሃ ዘመዶቹ

$
0
0

ክፍሉ ግርማ

ሰሞኑን የቀድሞውን የዲክታትር መለስ ዜናዊ የሞተበትን አንደኛ ዓመት በማስመልከት በየድረገጹ የተለያዩ የተቃውሞም የድጋፍም ጽሁፎች እየወጡ ነው ከሁሉ ግን አውራምባ ታይምስ በተሰኘው ድረገጽ ላይ አንድ ስለ መለስ ወንድምና እህት የሚገልጽ ፊልም አየሁ ነገሩ ሁሉ በጣም ገረመኝ ብዙ አስተያየቶችንም አነበብኩ ለእኔ ግን የማይውጥ ነው!! በጣም ስለድሃ ይሚያስብ ታላቅ መሪ…. ዘመዶችን እንኳን ለሃገሩ ሲል የረሳ መሪ…..ወ.ዘ.ተ እነዚህን የመሳሰሉ ውደሳዎችን የሚወዱት ኮሚኒስቶች ብቻ ናቸው

አንድ ሃይማኖት ያለው ወይም በትክክል የሚያስብ ሰው እንዴት ዘመዶችን ይረሳል በክርስትናም ሆነ በሙስሊሙ እምነት እናትና አባትን ከዚያም ወንድምና እህትን ማክበር መረዳዳትም እንዳለብን ያስተምራል.. አሁን እስቲ ይታያችሁ የመለስ እህት ጠላ መሸጥ ማለት መለስ ታላቅ መሪ ማለት ነው ? እዚህ አሜሪካን ሃገር በቀን 16 ሰዓት ከባድ ስራ እየሰሩ ወይም በአረብ አገር እህቶቻችን 24 ሰዓት በሰው ሰራተኛነት እይተቃጠሉ ወንድምና እህቶቻቸውን የሚስተምሩ ከቻሉም በብዙ ሺ የሚቆጠር ብር እየከፈሉ ከሃገር ወጥተው ራሳቸውን እንዲችሉ የሚያደርጉት ቤተሰባቸውን ለመቀየር አይደለምን? በሃገራችንም አንዱ ከቤተሰብ የተሻለ ቦታ ካለ ሌላውን መርዳትም የተለመደ ባህላችን ነው ወደ ቁም ነገሩ ለመለስና በእኔ እምነት መለስ እነዚህን ደሃ ወንድምና እህቱን አይውዳቸውም ወይም ያፍርባቸዋል ያልተማሩና ደሃ ስለሆኑም ይሆናል ወይም ሌላ ሚስጢር አለ እንጂ ለነዚህ ሚስኪን ሰዎች መለስ ትንሽ ቦታ አጥቶ አይደለም ለመሆኑ እነዚህ ወንድምና እህት ቤተመንግስት ለቅሶ ለመቀመጥ ተፈቅዶላቸው ይሆን በቀብር ስነ ስረአቱ ላይስ….ወ/ሮ አዜብስ ኤፈርት ካሰራቸው ብዙ ፋብሪካዎች በአንዱ ተቀጥረው ትንሽ ከጠላ ሻጪነት ብትገላግላቸው ጥሩ ነበር ኤፈርት የትግራይ ህዝብ ሀብት አይደለም እንዴ? ለመለስ እህት ያልሆነ ለማን ሊሆን ነው?

ከክፉ ውንድም ይጠብቅዎ

ፍልሙን ለማይት

ታንዛንያና ባህሏ

$
0
0
ምሥራቅ አፍሪቃዊቷ ሀገር ታንዛንያ በተለይ በአገር ጎብኚዎች ዘንድ ፣ እንጎሮንጎሮ እና ሴሬንጌቲ በተባሉት ቦታዎች በሚገኙት የዱር እንስሳትና ዓራዊት ክልሎች ትታወቃለች። ከዛ ባለፈስ የታንዛንያን ባህል ምን ይመስላል?…

ሙጋቤ ቃለ መሐላ ፈጸሙ

$
0
0
የ89 ዓመቱ ሮበርት ሙጋቤ በዛሬዉ ዕለት ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሀገሪቱ ፕሬዝደንት ሆነዉ ቃለ መሃላ ፈጸሙ።…

የካንሰር ምርምር በኢትዮጵያ

$
0
0
የሞት ምክንያት የሚሆኑ ነገሮች ሲዘረዘሩ በተለይ በአፍሪቃ የሚጠቀሱት ጦርነትና ተላላፊ በሽታዎች እንደሆኑ ይነገራል።…

የግብፅ ቀውስና የአውሮፓ ሕብረት

$
0
0
በግብጹ ግጭት መንስኤ አስቸኳይ ጉባኤ ያካሄዱት የአውሮፓ ህብረት አባል ሃገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ባሳለፉት ውሳኔ መሰረት ሕብረቱ ለግብፅ ጦር የሚውሉ የጦር መሣሪያዎችና ወታደራዊ ቁሳቁሶች ሽያጭ አግዷል ። «በሀገር ውስጥ ህዝብን ለመጨቆን የሚውል የማንኛቸውም የጦር መሣሪያዎች የውጭ ንግድ ፈቃዶች» ታግደዋል ።…

220813 ዜና 16:00 UTC

ሕዝባዊ ስብሰባ በሲያትል በአካባቢው ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ

Amharic News 1800 UTC –ኦገስት 22, 2013

$
0
0
News, Cultural Mosaic, Kebele Lives and Environment or Tech…

ሕዝባዊ ስብሰባ ፤ በሲያትል እና በአካባቢዋ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ

ሆስኒ ሙባረክ ተፈቱ

$
0
0

ነሃሴ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የቀድሞው የግብጽ ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሙባረክ ከእስር ተፈተው በሄሊኮፕተር ወደ ጦሩ ሆስፒታል ለምርመራ ተወስደዋል፣ ጊዚያዊው መንግስት ከቤታቸው እንደማይወጡ አስታውቋል።

ፕሬዚዳንቱ ከቀረረበባቸው የሙስና ክስ ነጻ በመሆናቸው መፈታታቸው ተገልጿል። ይሁን እንጅ ከሁለት አመት በፊት በግብጽ ከተካሄደው አብዮት ጋር በተያያዘ አሁንም ሌሎች ክሶች ቀርበውባቸዋል።

ደጋፊዎቸቻቸው ደስታቸውን ቢገልጹም፣ የሙስሊም ብራዘርሁድ ደጋፊዎች ደግሞ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።

ግብጽ አሁንም በመስቀለኛ መንገድ ላይ እንደምትገኝ ብዙ የፖለቲከኛ ተንታኞች ይናገራሉ።

በአማራ ክልል በአንድ ሰምንት ጊዜ ውስጥ በጎርፍ ከ45 ሰዎች በላይ ሞቱ

$
0
0

ነሃሴ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአካባቢው በሚጥለው ከባድ ዝናም የተነሳ በክልሉ በሚገኘው ኦሮሚያ ዞን ባለፈው ሳምንት ከ30 ያላነሱ ሰዎች የተገደሉበትን ክስተት ጨምሮ ፣ በደቡብ ወሎ ዞን በአንባሰል ወረዳ አንዲት ሚኒ ባስ በጎርፍ በመወሰዷ የ15 ሰዎች ህይወት አልፏል። በጎርፍ የተወሰዱ ሰዎችን አስከሬን ለማግኘት በተደረገ ጥረት የ14 ሰዎች አስከሬን ተገኝቷል። የአካባቢውን ፖሊስ አዛዥ ለማግኘት ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም።

በክልሉ እየጣለ ያለው ሀይለኛ ዝናብ ከፍተኛ ጉዳት እያመጣ መሆኑን ከክልሉ የሚደረሱን ዘገባዎች ያመለክታሉ። በአንዳንድ አካባቢዎች ትራንስፎርመሮች በመቃጠላቸው መብራት ለሳምንታት መቋረጡም ታውቋል።

ሰላሳ ሶስቱ ፓርቲዎች -ሰማያዊ ፓርቲን ከፓርቲዎች የትብብር መድረክ አሰናበቱ።

$
0
0

ነሃሴ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የ33ቱ ፓርቲዎች የትብብር መድረክ -ሰማያዊ ፓርቲን ያሰናበተው፤የፓርቲው ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ሰሞኑን ለ ሰንደቅ ጋዜጣ የሰጡት ቃለምልልስ የሌሎች ፓርቲዎችን ክብር የነፈገ ነው በሚል ነው።

በዚህም መሰረት ፓርቲዎቹ ባደረጉት ስብሰባ ሰማያዊ ፓርቲ ከስብስቡ እንዲወጣ መወሰናቸውን የቪኦኤ ዘገባ ያስረዳል።

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ፀሀፊ አቶ ተስፋዬ ታሪኩ ውሳኔው የተላለፈው ባለፈው እሁድ በተካሄደ አስቸኳይ ስብሰባ እንደሆነ  ገልጸዋል።

አቶ ይልቃል ለሰንደቅ በሰጡት ቃለ ምልልስ በዚህች አገር ከሰማያዊ ፓርቲ ውጪ ሌላ ተቃዋሚ ፓርቲ አለ ብለው እንደማያምኑ መገለፃቸው ይታወሳል።

“ገዥው ፓርቲና ምርጫ ቦርድ የሰጡንን ዕውቅና ሳይቀር አቶ ይልቃል ነስተውናል”ያሉት የመኢአድ ፀሀፊ፤ህዝቡ በፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ እምነት እንዳያድርበት ደባ ስለፈጸሙ፤ ድርጊታቸውን እንዲያርም ጊዜ ቢሰጣቸውም ሊያርሙ ስላለረቻሉ፤ ይባስ ብለውም ያንኑ ሃሳባቸውን ፡”የኛ ፕሬስ”በተሰኘ ጋዜጣ ላይ በማንፀባረቃቸው እና አቋሙ የ እርሳቸው ብቻ ሳይሆን የፓርቲያቸው ጭምር እንደሆነ በመረጋገጡ ከስብስቡ እንዲሰናበቱ ወስነናል ብለዋል።

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ይልቃል በበኩላቸው “የሰጠሁት አስተያየትና ያንፀባረቅኩት ሃሳብ አዲስ አይደለም፤ እውነትም    ነው”ብለዋል።

እስካሁን ሌሎች ፓርቲዎች የከፈሉትን መስዋዕትነት እርሳቸውና ፓርቲያቸው እንደሚያደንቁ ለቪኦኤ የተናገሩት አቶ ይልቃል፤ይሁንና ተቃዋሚዎች በአሁኑ ጊዜ የህዝብን የለውጥ ጥያቄ ለመመለስ በሚያስችል ጥንካሬና አቋም ላይ አለመሆናቸውን ገልጸዋል።

“እኔ ስህተተኛ ብሆን ደስታዬ ነበር”ያሉት አቶ ይልቃል፤”እነዚህ ፓርቲዎች ነን እንደሚሉት ቢሆኑ እኔና ጓደኞቼ ሰማያዊ ፓርቲን አፍርሰን ወደየሌሎች ፓርቲዎች እንገባለን፤ወይም ወደየቤታችን እንሄዳለን”ብለዋል።

“ግን እውነቱ ሌላ ነው። የኢትዮጵያን ችግር መጋፈጥ አለብን ካልን እውነቱን ማድበስበስ የለብንም” በማለት ቀደም ሲል በሰጡት አስተያዬት እንደሚያምኑ በድጋሚ አረጋግጠዋል።


የኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢዎችን ቤት ለማዳረስ ከ20 ዓመታት በላይ እንደሚፈጅ አንድ ሰነድ አመለከተ

$
0
0

ነሃሴ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በከንቲባ ድሪባ ኩማ የሚመራው አዲሱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰሞኑን ይፋ ባደረገው ረቂቅ የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ የኮንዶሚየም ቤት ፈላጊዎችን ለማስተናገድ ከ20 ዓመታት በላይ ጊዜ እንደሚወስድ ጠቆሟል።

አስተዳደሩ ለኮንዶሚየም ቤቶች ብቻ ከ800ሺ በላይ ዜጎችን ቢመዘግብም በቀጣይ አምስት ዓመት ለመስራት ያቀደው 178 ሺ ቤቶችን ብቻ ነው፡፡

አስተዳደሩ ከ2006 እስከ 2010 ዓ.ም ሥራ ላይ አውለዋለሁ ባለው የስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ የቤቶች ልማትን በተመለከተ የያዘው ዕቅድ እጅግ አነስተኛ ሆኖ መገኘት በየደረጃው ያሉ አባላትና ካድሬዎችን ጭምር አስደንግጦአል፡፡

በአሁኑ ወቅት 20 በ80 በሚባለው የኮንዶሚኒየም ቤቶች ባለቤት ለመሆን ከ800ሺ በላይ
ነዋሪዎች ተመዝግበው እየተጠባበቁ ባሉበት ሁኔታ በአምስት ዓመት 178ሺ ቤቶችን ብቻ እገነባለሁ በሚለው ስሌት ሲታሰብ 800ሺ ተመዝጋቢውን ለማዳረስ ከ20 ዓመታት በላይ ጊዜ የሚፈጅ መሆኑ ሕዝቡን በከፍተኛ ደረጃ ተስፋ የሚያስቆርጥ ነው ተብሎ ተሰግቶአል፡፡

የቤቶች ልማት ቢሮው ይህን ዕቅድ የያዘው የአስተዳደሩን አቅምና የእስካሁኑን የግንባታ ልምድ ግምት ውስጥ በማስገባት መሆኑን መረጃው ያመለክታል፡፡ የኩማ አስተዳደር በአምስት ዓመት ቆይታው 36ሺ700 ከባለአደራ አስተዳደር የተረከበውን ቤቶች ጨምሮ በጠቅላላው በሰልጣን ጊዜው መገንባት የቻለው 175ሺ246 ያህል ቤቶችን ብቻ ነው፡፡

ፕሮግራሙ ከተጀመረ ባለፉት ስምንት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ለተጠቃሚዎች የተላለፉ የኮንዶሚኒየም ቤቶች ብዛት 100 ሺ 559 ያህል ነው፡፡ አዲሱ ዕቅድም ሲሰራም ይህን የመገንባት አቅም ታሳቢ አድርጎ መሆኑን ታውቋል፡፡

ይህ ረቂቅ ዕቅድ የአስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማ በተገኙበት ሰሞኑን በየደረጃው ላሉ
የአስተዳደር አካላት ለውይይት በቀረበበት ወቅት ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል፡፡ አንዳንድ ተሰብሳቢዎች በዚሁ መድረክ ላይ ይህን ዕቅድ ሕዝቡ አይቀበለንም፣ ማሳመንም አንችልም በሚል ተሻሽሎ እንዲቀርብ ጠይቀዋል፡፡

በተጨማሪም በአዲሱና አወዛጋቢ በነበረው የሊዝ አዋጅ መሠረት በቀጣይ አምስት ዓመታት በአዲስአበባ ብቻ ካሉ ነባር ባለይዞታዎች ግማሽ ያህሉን ወደሊዝ ሥርዓት ለማስገባት የተያዘው ዕቅድም በተመሳሳይ ሁኔታ በራሱ አመራር አባላት ተቃውሞ ገጥሞታል።

የሊዝ አዋጁ ነባር ይዞታን በተመለከተ ይዞታዎች ሲሸጡ ወደአዲሱ የሊዝ ሥርዓት እየገቡ እንደሚሄዱ ቢደነግግም  አስተዳደሩ በምን መልኩ 50 በመቶ ያህል ነባር ይዞታዎችን ወደሊዝ ሥርዓት
ለማስገባት እንዳቀደ ግልጽ አይደለም ፡፡

የስብሰባው ተካፋዮችም ይህ የሊዝ ጉዳይ አገር አቀፍ ሕግ ሆኖ ሳለ በአዲስአበባ ይጀመር የመባሉ ጉዳይ እና የአፈጻጸሙ ሁኔታ የህዝብን ድጋፍ ያሳጣል በሚል ሳይቀበሉት ቀርተዋል፡፡ ይህ የአምስት ዓመት የስትራቴጂክ ዕቅድ በቀጣይ ህብረተሰቡ ተወያይቶበት ስራ ላይ ይውላል ተብሎአል፡፡

የቁጫ የአገር ሽማግሌዎች በጠቅላይ ሚ/ሩ ጽህፈት ቤት ተገኙ

$
0
0

ነሃሴ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- 60 የሚጠጉ የወረዳዋ ሽማግሌዎች በዛሬው እለት ለ7ኛ ጊዜ በጠ/ሚ ሀይለማርያም ደሳለኝ ጽሀፈት ቤት ቢገኙም ጠ/ሚኒስትሩን ሊያገኙዋቸው እንዳልቻሉና በተወካያቸው በአቶ ወርቁ በኩል መንግስት ጉዳዩን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ያሳውቃል የሚል መልስ እንደተሰጣቸው ለኢሳት ገልጸዋል።

በመንግስት መልስ ደስተኞች ያለሆኑት የአገር ሽማግሌዎች፣ እንደገና ተመልሰው ወደ ክልሉ ዋና ከተማ አዋሳ ማቅናታቸው ታውቋል። ሽማግሌዎቹ ለጠ/ሚንስትር ሀይለማርያም ተወካይ ፣ ወደ ቦታችን ስንመለስ እንደማንታሰር ዋስትና ይሰጠን በማለት ቢጠይቁም፣ ተወካዩ የሚያስሩዋችሁ ከሆነ በቀጥታ ደውሉልኝ ብለው ስልካቸውን እንደሰጡዋቸው ገልጸዋል።

የአገር ሽማግሌዎች ወደ ጠቅላይ ሚኒሰትሩ ጽ/ት ቤት ለመሄድ ያስገደዳቸው በወረዳው የሚታሰረው ሰው ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱና ይህን ተከትሎም ግጭት ሊነሳ ይችላል የሚል ስጋት በመኖሩ አስቀድሞ ለማሳወቅ ነው ብለዋል።

በአካባቢው እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰት ፣ በአገሪቱ መንግስት አለ ወይ የሚያስብል መሆኑን ከሽማግሌዎቹ አንዱ ተናግረዋል።

እስካሁን ድረስ ቁጥሩ በትክክል ባይታወቅም ከ90 እስከ 100 የሚደርሱ ሰዎች መታሰራቸውን ሽምግሌዎቹ ይናገራሉ።

መረጃውን ከቀበሌ ቀበሌ በማመላለስ ግጭት እንዲፈጠር ያደርጋሉ የተባሉ 160 ባጃጅ የሚባሉ ተሽከርካሪዎች አሁንም ፖሊስ ጣቢያ ቆመዋል። ከ30 በላይ ሰራተኞችም ተባረዋል።

የቁጫ ወረዳ ነዋሪዎች በቋንቋችን እንጠቀም፣ ሌሎች መብቶቻችን ይከበሩልን የሚሉ ጥያቄዎችን ማንሳታቸው ይታወቃል።

አምስተኛው ባርነት – ከፋሲል የኔዓለም (ጋዜጠኛ)

$
0
0

ቤቶችበጥንቱ ስርዓት፣ አንድ ሰው ከአራቱ በአንዱ መንገድ ባሪያ ይሆናል። የመጀመሪያው በጦርነት ተሸንፎ ከተማረከ ፣ ሌላው እዳውን መክፈል አልችል ብሎ በእዳ ከተያዘ ፣ ሶስተኛው ከባሪያ ቤተሰብ የተወለደ ከሆነ በውርስ፣ አራተኛው ደግሞ ባሪያ ፈንጋዮች ይዘው ከሸጡት ነው። በዚህ ዘመን የባሪያ ንግድ ቢጠፋም፣ ባርነት ግን አልጠፋም። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እንዲያውም አምስተኛውን የባርነት መንገድ እያየን ነው፤ ይሄ ባርነት በባህሪው እስከዛሬ ከታዩት ሁሉ የተለየና አስገራሚም ነው። እመለስበታለሁ።
ባሪያ ማለት፣ የጌታውን እጅ አይቶ የሚያድር፣ በራሱ ነጻነት የሌለው፣ ሰምቶ የመቀበል እንጅ ሰምቶ የመመለስ መብት የሌለው፣ በግዑዝና በነጻ-ሰው መካከል ያለ ፍጥረት ነው። ባርያ ሰውን ሰው የሚያደርገውን ነጻነት ሙሉ በሙሉ የተገፈፈ በመሆኑ፣ ከሰው ተርታ የሚመደበው ስለሚመገብ፣ ስለሚለብስ፣ መጠለያ ስላለው፣ ቋንቋ ስለሚጠቀም እና አውራጣት ስላለው ብቻ ነው፤ ከዚያ በተረፈ ግን የጭነት እንስሳ ማለት ነው። ባሪያ በእግዚአብሄር አምሳል በመፈጠሩ ክፉና ደጉን የመለየት ስልጣን ቢሰጠውም ፣ ስልጣኑን በጌታው በመነጠቁ ፣ ሁልጊዜ የጌታውን ደግ ነገር ብቻ እያየ እና እያመሰገነ የሚኖር ፍጥረት ነው።

በአሁኑ ጊዜ የሚታየው አምስተኛው የባርነት መንገድ 40 በ60 ከሚባለው የቤት ግንባታ ጋር የተያያዘ ነው፤ በዚህ የባርነት መንገድ ለመጓዝ የወሰነው ደግሞ ዲያስፖራው ( በውጭ የሚኖረው) ኢትዮጵያዊ ነው። መንግስት ለዲያስፖራው 40/በ60ን ሲያዘጋጅ ሁለት አላማዎችን ታሳቢ አድርጎ ነው- ዲያስፖራው ጥሮ ግሮ ያገኘውን ሀብት ሰብስቦ ደቋናውን ለመሙላት እና ዲያስፖራው ስለነጻነቱ እንዳይጠይቅ ወይም መንግስትን እንዳይቃወም አፍ ለማዘጋት።

40 /በ60 የተመዘገበ ዲያስፖራ እናት እና አባቱ፣ እህትና ወንድሙ፣ በአጠቃላይ የአገሩ ሰዎች ቢገደሉ፣ ቢታሰሩ ፣ ቢሰደዱ፣ ቢራቡ ፣ ቢጠሙ፣ ” ለምን?” ብሎ አደባባይ ወጥቶ የመጠየቅ እና የመቃወም ነጻነት አይኖረውም፤ ነጻነቱን በ40/በ60 ተገፎአል። ለሌላው መብት ሊሟገት ቀርቶ፣ በጥፊ ቢመታም እንኳን፣ “ጥፊው እንዴት ይጣፍጣል፣ እባክህ ግራ ጉንጨንም ድገምልኝ” ከማለት ውጭ፣ “ለምን ትመታኛለህ?’ ብሎ የአባትና እናቱን ወኔ ቀስቅሶ ብድሩን የመመለሻ ልብ አይኖረውም። እስክንድር ነጋ፣ አበበ በለው፣ ብርሀኑ ነጋ፣ እና ሌሎችም፣ ከስጋቸው ድሎት ነጻነታቸውን ያስቀደሙ በርካታ ኢትዮጵያውያን፣ ባርነት በቃን በማለታቸው፣ ጥረው ግረው ያፈሩትን ሀብት ተነጥቀዋል።
40/በ60 የተመዘገበ ዲያስፖራ ስለወገኑ ለመጮህ ከእንግዲህ በአውሮፓ እና በአሜሪካ ከተሞች እጅግም አይታይም፣ ለይሉንታ ቢታይ እንኳ ፊቱን በወረቀት ሸፍኖ ከሁዋላ ከመሰለፍ የዘለለ ሚና አይኖረውም። በነጻነት አገር እየኖሩ ገንዘብ ከፍሎ፣ በፍላጎት ባርነትን መምርጥ ማለት ይህ አይደለምን? የሚገዛ የለም እንጅ እነዚህ ሰዎች እኮ መንግስት ቢሸጣቸው እንኳ ምንም የሚናገሩ አይደሉም። ገንዘብ ተከፍሎ ባሪያ አድርጉን ብሎ የሚጠየቅበት አሰራር በታሪክ ታይቶ ይታወቃልን?

በአገር ቤት ያለው ህዝብ ለ 20/በ80 ቢመዘገብ አይገርመኝም፤ በባርነት ውስጥ የሚኖር ህዝብ በመሆኑ፣ አንድ ቀን ራሱን ነጻ እስኪያወጣ፣ ለጊዜው ተመችቶት ይኑር። ባሪያም እኮ ልብሱን ይቀይራል፣ የምኝታውን ሳር ተባይ ሲወርበት በሌላ ሳር ይተካዋል፤ ባበርነት ስር ያለው የአገር ቤት ሰው በነፍሱም በስጋውም ሊበደል አይገባውም፤ ቢያንስ እስከ ጊዜው በስጋው ይደሰት። ዲያስፖራው ግን የኢትዮጵያን ምድር ከለቀቀባት ጊዜ ጀምሮ ከባርነት ነጻ ወጥቷልና በነጻነት መኖር የሚችለበት እድል አለው፤ ለራሱ ብቻ ሳይሆን ለሌላውም ነጻነት ለመታገል ሁኔታው ተመቻችቶለታል፤ ይህን ነጻነቱን ግን እራሱ ገንዘብ ከፍሎ ሊሸጠው ይደራደራል። ፍርፋሪ እየተጣለለት ወደ ቄራ የሚወሰድ እሪያ መጨረሻው ሞት እንደሆነው ሁሉ፣ 40/በ60 የተመዘገበ ዲያስፖራም መጨረሻው ባርነት ነው። አምስተኛው ባርነት!

ኢሕአፓ፣ እኔ እማውቀው፣

$
0
0

tower-in-the-sky-300x399(ባለፈው ሰሞን በሕይወት ተፈራ ተደርሶ ለንባብ ለበቀው፣ Tower In the Sky፣ ስለተባለው መጽሀፍ ውስጥ በተነሱ አንዳንድ ጉዳዮች ላይ የቀረበ አስተያዬት፣)
ከሰላሙ ባላይ፣

ሙሉውን በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

አምስተኛው ባርነት፤ ከፋሲል የኔዓለም (ጋዜጠኛ)

$
0
0

በጥንቱ ስርዓት፣ አንድ ሰው ከአራቱ በአንዱ መንገድ ባሪያ ይሆናል። የመጀመሪያው በጦርነት ተሸንፎ ከተማረከ ፣ ሌላው እዳውን መክፈል አልችል ብሎ በእዳ ከተያዘ ፣ ሶስተኛው ከባሪያ ቤተሰብ የተወለደ ከሆነ በውርስ፣ አራተኛው ደግሞ ባሪያ ፈንጋዮች ይዘው ከሸጡት ነው። በዚህ ዘመን የባሪያ ንግድ ቢጠፋም፣ ባርነት ግን አልጠፋም። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እንዲያውም አምስተኛውን የባርነት መንገድ እያየን ነው፤ ይሄ ባርነት በባህሪው እስከዛሬ ከታዩት ሁሉ የተለየና አስገራሚም ነው። እመለስበታለሁ።

ባሪያ ማለት፣ የጌታውን እጅ አይቶ የሚያድር፣ በራሱ ነጻነት የሌለው፣ ሰምቶ የመቀበል እንጅ ሰምቶ የመመለስ መብት የሌለው፣ በግዑዝና በነጻ-ሰው መካከል ያለ ፍጥረት ነው። ባርያ ሰውን ሰው የሚያደርገውን ነጻነት ሙሉ በሙሉ የተገፈፈ በመሆኑ፣ ከሰው ተርታ የሚመደበው ስለሚመገብ፣ ስለሚለብስ፣ መጠለያ ስላለው፣ ቋንቋ ስለሚጠቀም እና አውራጣት ስላለው ብቻ ነው፤ ከዚያ በተረፈ ግን የጭነት እንስሳ ማለት ነው። ባሪያ በእግዚአብሄር አምሳል በመፈጠሩ ክፉና ደጉን የመለየት ስልጣን ቢሰጠውም ፣ ስልጣኑን በጌታው በመነጠቁ ፣ ሁልጊዜ የጌታውን ደግ ነገር ብቻ እያየ እና እያመሰገነ የሚኖር ፍጥረት ነው።

በአሁኑ ጊዜ የሚታየው አምስተኛው የባርነት መንገድ 40 በ60 ከሚባለው የቤት ግንባታ ጋር የተያያዘ ነው፤ በዚህ የባርነት መንገድ ለመጓዝ የወሰነው ደግሞ ዲያስፖራው ( በውጭ የሚኖረው) ኢትዮጵያዊ ነው። መንግስት ለዲያስፖራው 40/በ60ን ሲያዘጋጅ ሁለት አላማዎችን ታሳቢ አድርጎ ነው- ዲያስፖራው ጥሮ ግሮ ያገኘውን ሀብት ሰብስቦ ደቋናውን ለመሙላት እና ዲያስፖራው ስለነጻነቱ እንዳይጠይቅ ወይም መንግስትን እንዳይቃወም አፍ ለማዘጋት።

40 /በ60 የተመዘገበ ዲያስፖራ እናት እና አባቱ፣ እህትና ወንድሙ፣ በአጠቃላይ የአገሩ ሰዎች ቢገደሉ፣ ቢታሰሩ ፣ ቢሰደዱ፣ ቢራቡ ፣ ቢጠሙ፣ ” ለምን?” ብሎ አደባባይ ወጥቶ የመጠየቅ እና የመቃወም ነጻነት አይኖረውም፤ ነጻነቱን በ40/በ60 ተገፎአል። ለሌላው መብት ሊሟገት ቀርቶ፣ በጥፊ ቢመታም እንኳን፣ “ጥፊው እንዴት ይጣፍጣል፣ እባክህ ግራ ጉንጨንም ድገምልኝ” ከማለት ውጭ፣ “ለምን ትመታኛለህ?’ ብሎ የአባትና እናቱን ወኔ ቀስቅሶ ብድሩን የመመለሻ ልብ አይኖረውም። እስክንድር ነጋ፣ አበበ በለው፣ ብርሀኑ ነጋ፣ እና ሌሎችም፣ ከስጋቸው ድሎት ነጻነታቸውን ያስቀደሙ በርካታ ኢትዮጵያውያን፣ ባርነት በቃን በማለታቸው፣ ጥረው ግረው ያፈሩትን ሀብት ተነጥቀዋል።
40/በ60 የተመዘገበ ዲያስፖራ ስለወገኑ ለመጮህ ከእንግዲህ በአውሮፓ እና በአሜሪካ ከተሞች እጅግም አይታይም፣ ለይሉንታ ቢታይ እንኳ ፊቱን በወረቀት ሸፍኖ ከሁዋላ ከመሰለፍ የዘለለ ሚና አይኖረውም። በነጻነት አገር እየኖሩ ገንዘብ ከፍሎ፣ በፍላጎት ባርነትን መምርጥ ማለት ይህ አይደለምን? የሚገዛ የለም እንጅ እነዚህ ሰዎች እኮ መንግስት ቢሸጣቸው እንኳ ምንም የሚናገሩ አይደሉም። ገንዘብ ተከፍሎ ባሪያ አድርጉን ብሎ የሚጠየቅበት አሰራር በታሪክ ታይቶ ይታወቃልን?

በአገር ቤት ያለው ህዝብ ለ 20/በ80 ቢመዘገብ አይገርመኝም፤ በባርነት ውስጥ የሚኖር ህዝብ በመሆኑ፣ አንድ ቀን ራሱን ነጻ እስኪያወጣ፣ ለጊዜው ተመችቶት ይኑር። ባሪያም እኮ ልብሱን ይቀይራል፣ የምኝታውን ሳር ተባይ ሲወርበት በሌላ ሳር ይተካዋል፤ ባበርነት ስር ያለው የአገር ቤት ሰው በነፍሱም በስጋውም ሊበደል አይገባውም፤ ቢያንስ እስከ ጊዜው በስጋው ይደሰት። ዲያስፖራው ግን የኢትዮጵያን ምድር ከለቀቀባት ጊዜ ጀምሮ ከባርነት ነጻ ወጥቷልና በነጻነት መኖር የሚችለበት እድል አለው፤ ለራሱ ብቻ ሳይሆን ለሌላውም ነጻነት ለመታገል ሁኔታው ተመቻችቶለታል፤ ይህን ነጻነቱን ግን እራሱ ገንዘብ ከፍሎ ሊሸጠው ይደራደራል። ፍርፋሪ እየተጣለለት ወደ ቄራ የሚወሰድ እሪያ መጨረሻው ሞት እንደሆነው ሁሉ፣ 40/በ60 የተመዘገበ ዲያስፖራም መጨረሻው ባርነት ነው። አምስተኛው ባርነት!

Viewing all 13695 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>