Quantcast
Channel: Amharic News & Opinion
Viewing all 13695 articles
Browse latest View live

የድሬዳዋ ቅ/ሚካኤል ካቴድራል ሰ/ጉባኤ: ‹‹የሃይማኖት ጉዳይ በድምፅ ብልጫ አይወሰንም›› ሲል በኑፋቄ ውዝግብ የታሸገው ሰንበት ት/ቤት እንዲከፈትና በኑፋቄ የተጠለፈው አመራር እንዲቀጥል ሀ/ስብከቱ በድምፅ ብልጫ ያስተላለፈውን መመሪያ ተቃወመ

$
0
0
  • አመራሩ በታገደበት ቆይቶ የኑፋቄ ውዝግቡ በገለልተኛ ወገን እንዲጣራ ጠይቋል
  • አመራሩ ኑፋቄው በአግባቡ እንዳይጣራ የተለያዩ ተጽዕኖዎችን ሲፈጥር ቆይቷል
  • ብዙኀኑ የሀ/ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ አባላት በውሳኔው ቃለ ጉባኤ ላይ አልፈረሙም
  • ‹‹ከዚህ በኋላ ለሚፈጠረው ችግር ሓላፊነቱን የሀ/ስብከቱ ጽ/ቤት ይወስዳል፡፡›› /ሰበካ ጉባኤው/

 

በፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ ሕዋስ በመጠለፉና በቃለ ዐዋዲው ድንጋጌ መሠረት ለሰበካ ጉባኤው መመሪያ ባለመገዛቱ የመዘጋት ርምጃ የተወሰደበት የድሬዳዋ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ሰንበት ት/ቤት እንዲከፈትና ነባሩም አመራር እንዲቀጥል የሀ/ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ በድምፅ ብልጫ ወስኖ ያስተላለፈውን መመሪያ የካቴድራሉ ሰበካ ጉባኤ አስተዳደር እንደማይቀበለው አስታወቀ፡፡

‹‹የሃይማኖት ጉዳይ በሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን መሠረት በሊቃውንትና ካህናት ጉባኤ እንጂ በአስተዳደራዊ መንገድና በድምፅ ብልጫ አይወሰንም›› ያሉት የሰበካ ጉባኤው አባላት፣ ውዝግቡ ከሀ/ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ ውጭ በገለልተኛ ጉባኤ እንዲታይ አልያም ሰበካ ጉባኤውንና ማኅበረ ካህናቱን ከታገደው የሰንበት ት/ቤቱ አመራር ጋራ አቀራርቦ በማነጋገር፣ ጥፋተኛውን በመለየትና በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቅ በማድረግ እንዲፈታ አሳስበዋል፡፡

የካቴድራሉ ሰበካ ጉባኤ ለሀ/ስብከቱ ውሳኔ ምላሽ ለመስጠት ነሐሴ ፲፰ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ እንደተገለጸው÷ ከግማሽ በላይ የሀ/ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ አባላት አጣሪም ወሳኝም ኾነው በተሳተፉበትና በፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ ሕዋስ የተጠለፈው የሰንበት ት/ቤቱ ሥራ አመራር ችግር በግልጽ በታወቀበት ኹኔታ በድምፅ ብልጫ የተላለፈው ውሳኔ ፍትሐዊነት ይጎድለዋል፤ የታገደውን አመራር የተሳሳቱ ሐሳቦችም የሚደግፍ ነው፡፡

የሰበካ ጉባኤው የተቃውሞ ውሳኔ እንደሚያብራራው የሰንበት ት/ቤቱ አመራር÷ በኑፋቄ በመጠርጠሩ ከሓላፊነትና አባልነት ታግዶ ማጣራት እየተካሄደበት ለሚገኘው ሊቀ መንበሩ ጥብቅና በመቆም ማጣራቱ በአግባቡ እንዳይከናወንና እንዲድበሰበስ አባላቱን ለዐድማና ዐመፅ በማንቀሳቀስና የዐውደ ምሕረት አገልግሎት እንዲያቆሙ ያለፈቃዳቸው በማስገደድ ጫና ፈጥሯል፤ በቃለ ዐዋዲው ድንጋጌ መሠረት ከሰበካ ጉባኤው የሚሰጠውን መመሪያ ‹‹ሰበካ ጉባኤ አያዘንም›› በሚል አይቀበልም፤ በካቴድራሉ የሚደቡለትን መምህራን ይንቃል፤ ካህናቱን ያቃልላል፤ አባላቱም ከማኅበረ ካህናቱ ጋራ በአባትና ልጅ መንፈስ እንዳይተያዩ እየቀሰቀሰ በካቴድራሉ ከፍተኛ ብጥብጥና ንትርክ እንዲፈጠር አድርጓል፡፡

አመራሩ በዚህ አካሄዱ እንዲቀጥል ከተፈቀደለት የዐመፅና ብጥብጥ ተግባሩን እያሰፋ የሚሄድ በመኾኑ፣ በኑፋቄ በተጠረጠረው የሰንበት ት/ቤቱ ሊቀ መንበር ላይ በጉባኤ ካህናት የሚካሄደው ማጣራት እስከሚጠናቀቅ ድረስ ጽ/ቤቱን የማሸግ፣ አመራሩንም ከሓላፊነት የማገድ ርምጃ መወሰዱ ተገልጧል፡፡ የሀ/ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ በአጣሪ አካሉ አማካይነት ይህን የሰንበት ት/ቤቱን አመራር ችግርና ከመመሪያ ውጭ መኾን አረጋግጦ ሳለ ባለጉዳዮችን አቀራርቦ ለማነጋገር እንኳ ሳይሞክር የታሸገው ሰንበት ት/ቤት እንዲከፈትና የነበረው አመራር እንዲቀጥል መመሪያ መስጠቱ አግባብነት እንደሌለው የካቴድራሉ ሰበካ ጉባኤ በተቃውሞ ውሳኔው ገልጧል፤ ከዚህ በኋላም ለሚፈጠረውም ችግር ሓላፊነቱ የሀ/ስብከቱ እንደሚኾን አሳስቧል፡፡

ሰበካ ጉባኤው በደረሰበት የጋራ አቋምና ስምምነት መሠረት የታገደው የሰንበት ት/ቤቱ አመራር የአስተዳደሩን መመሪያ ካለመቀበል ባሻገር ለካቴድራሉ አገልጋይ ካህናትና መምህራን ያለው አመለካከት ዝቅ ያለና ምንም እንደማያውቁ የሚቆጥር በመኾኑ፣ የሚመደቡለትንም መምህራን በቀናነት ስለማይመለከት እንዲቀጥል ሊፈቀድለት አይገባም፤ ሓላፊነቱን ማስረከብና በአዲስ ሥራ አመራር መተካት ይኖርበታል፡፡ በመኾኑም የሀ/ስብከቱን ውሳኔ ተቀብሎ ለማስፈጸም እንደሚቸገርና ጉዳዩ ከአስተዳደር ጉባኤው አባላት ውጭ በኾነ ገለልተኛ አካል ዳግመኛ እንዲታይ ጠይቋል፡፡

የሀ/ስብከቱ ምንጮች በበኩላቸው፣ በሀ/ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ አማካይነት ለካቴድራሉ ሰበካ ጉባኤ የተላለፈው መመሪያ ሰባት አባላት ያሉት የሀ/ስብከቱ አጣሪ ኮሚቴ ባቀረበው ሪፖርት ላይ የአስተዳደር ጉባኤው አባላት ተወያይተው ውሳኔ ያሳለፉበትን ቃለ ጉባኤ ተመልክተው ሳይፈርሙበት በችኮላ የወጣ ነው፤ በውሳኔያቸውና በተላለፈው መመሪያ መካከል ልዩነት በመኖሩ በድምፅ ብልጫ ተወስኖበታል በሚባለው መመሪያም አይስማሙም፤ ከሀ/ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ ከካህናት አስተዳደር ክፍል፣ ከልማት ክፍል እና የሰንበት ት/ቤቱን አመራር ከጠለፈው የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ ሕዋስ አንዱ ናቸው ተብለው ከሚጠረጠሩት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል ሓላፊው በቀር የሚበዙት ሓላፊዎች በቃለ ጉባኤው ላይ አለመፈረማቸውንም ተናግረዋል፡፡

ሰንበት ት/ቤቱን ለመታሸግ፣ አመራሩን ለመታገድ ያበቃው የኑፋቄ ውዝግብ የተቀሰቀሰው የሰንበት ት/ቤቱ ሊቀ መንበርና በሰበካ ጉባኤው የሰንበት ት/ቤቱ ተወካይ ሐምሌ ፲፪ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም በፌስቡክ ገጹ ላይ ‹‹ያለወላዲተ አምላክ አማላጅነት ዓለም አይድንም የሚለው አባባል    የማይሞች ነው›› ብሎ ማስፈሩን ተከትሎ ነው፡፡ ተቃውሞው በዚያው በፌስቡክ ገጽ ላይ ትችታቸውን በሰነዘሩ የካቴድራሉና ሌሎች አጥቢያዎች ሰንበት ት/ቤት አባላት፣ ሰባክያንና ካህናት ተጀምሮ ሲስፋፋ ሊቀ መንበሩ በሰበካ ጉባኤው ውሳኔ ታግዶ ጽሑፉ የሰፈረበት ኹኔታ እንዲጣራ እየተደረገ ሳለ የሰንበት ት/ቤቱ አመራር አባላት በሙሉ ‹‹የእርሱ አቋም/ሐሳብ ሐሳባችን ነው›› በማለታቸው ለውዝግቡ መጠናከር መንሥኤ ኾኗል፡፡

ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አስተያየት ሰጭዎች እንደሚሉት የውዝግቡ መንሥኤ ወይም አጋጣሚ ይህ ይኹን እንጂ የሰንበት ት/ቤቱ አመራር ከዚህም ሥር በሰደደ የጥርጥር ማዕበል የተመቱ መኾናቸውን ይመሰክራሉ፡፡ ለዚህም የቤተ ክርስቲያናችን ነገረ ማርያም እና የክብረ ቅዱሳን አስተምህሮ ‹‹የዐጤ ዘርዐ ያዕቆብ ሸክም ነው››፤ ‹‹በቀጥታ ኢየሱስን እንጂ የምን ዙርያ ጥምጥም እንሄዳለን››፤ ‹‹ኦርቶዶክስ ባለሥልጣን እንጂ ሊቅ የላትም›› ማለታቸውን በአብነት ይጠቅሳሉ፡፡



የደህንነት ኃይሎች ጋዜጠኞችን ማዋከብና ማስፈራራት አጠናክረው ቀጥለዋል

$
0
0

ከበትረ ያዕቆብ

Fnote23ለረጅም ጊዜ የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ አዘጋጅ ሆኖ ያገለገለዉና የጋዜጣዉ ህትመት ከተቋረጠበት ጊዜ ጀምሮ የኢቦኒ መፅሔት ዋና አዘጋጅ ሆኖ በመስራት ላይ የሚገኘዉ ጋዜጠኛና ብሎገር ብስራት ወልደ ሚካኤል ሰሞኑን በ4 የደህንነት ኃይሎች ታግቶ ዛቻ እና ማስፈራሪያ እንደተፈፀመበት ተናገረ ፡፡ ድርጊቱ የተፈፀመዉ ባሳለፍነዉ ሰኞ (ነሐሴ 20 – 2005ዓ.ም) ከምሽቱ 2፡35 ላይ ከስራ ወደ ቤቱ በጉዞ ላይ እያለ ነበር፡፡ብስራት ወልደ ሚካኤል እንደገለፀዉ ግለሰቦቹ ለ50 ደቂቃ ያህል ያገቱት ሲሆን ፤ ከአሁን በኋላ በየትኛውም ጋዜጣ ፣ መፅሔትም እንዲሆም ብሎግ ላይ ብትፅፍ በህይወትህ ላይ ፈርደህ ነዉ ሲሉ ዝተዉበታል፡፡ በመጨረሻም በጥፊ መተዉታል፡፡ ብስራት እንደገለፀዉ ከሰዎቹ መካከል አንዱ ሽጉጡን እየደጋገመ በማሳየት ሊያስፈራራዉ ሙከራ ያደረገ ሲሆን ፤ ሌላኛዉ ደግሞ እንዳይንቀሳቀስ ሴንጢ በሆዱ ላይ ደግኖበት ነበር፡፡ ጋዜጠኛ ብስራት አያይዞም “አቶ መለስ ዜናዊ አለዉ ከተባለዉ 3 ቢሊዮን ዶላር እና ልጁ ከታማችበት 5 ቢሊዮን ዶላር እንዲሁም የፀረ ሽብርተኝነት ህጉን በሚመለከት የፃፋኳቸዉ ፅሑፎች እንዳናደዷቸውና እንዳበሳጯቸው በንግግራቸው ይጠቃቅሱልኝ ነበር” ሲል ተናግሯል፡፡

“ይህን የጋዜጠኝነት ሙያየ ወድጄና ፈልጌ በመማር የገባሁበት እንጂ ተገድጄና ተመድቤበት የምሰራው አይደለም ፤ ከዚህም ሙያ ልወጣ አልችልም ” የሚል ምላሽ ሰጠኋቸዉ ሲል የተናገረዉ ጋዜጠኛ ብስራት ፤ አያይዞም ፀያፍ ስድብ እንደሰደቡትና ከወላጅ አባቱ ጋር በተያያዘ የተናገሩት አሳዛኝ ነገር እንደነበረ ጠቁሟል፡፡ አያይዞም “ከግለሰቦቹ መካከል አንዱን ልደታ ፍርድ ቤት በተለይም በሽብርተኝነት የተከሰሱትን የእነ አንዱዓለምንና እስክንድርን ጉዳይ ልዘግብ ስሄድ ሁሌም እዚያ የማላጣው ሰዉ ነበር” ብሏል፡፡

“ይህንን ሁሉ ወዲያው ሳሪስ ለሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ሄጄ ያሳወቅሁ ሲሆን ፤ ያኔ ተረኛ መርማሪ ፖሊስ የነበረው ኮንስታብል ጥላሁን ታዴ የተባለ ሰዉ ያንተ ጉዳይ ከበድ ስለሚል የጣቢያው ዋና ኢንስፔክተር አበበ አያሌው ሲመጣ ጠዋት ንገረው አለኝ፡፡ በሰዓቱ የሚተባበረኝ ፖሊስ ቢኖር ግን የገቡበትን አቅጣጫ ስላየሁ አጋቾቹን እናገኛቸው ነበር ፤ ግን በሰዓቱ ለሚቀጥለዉ ቀን ከመቅጠር በቀር የተባበረኝ አልነበረም፡፡” በማለት ጋዜጠኛ ብስራት ተናግሯል፡፡ አያይዞም “በነጋታው ማክሰኞ ጠዋት ነሐሴ 21 ቀን ዋና ኢንስፔክተር አበበን ለማናገር ወደ ጣቢያው ብሄድም አሁን የሉም ፣ ለስብሰባ ወጥተዋል ተብዬ ከሰዓት እንድመለስ ተነገረኝ፡፡ ከሰዓትም ስሄድ ተመሳሳይ መልስ ከተሰጠኝ በኋላ ለረቡዕ ነሐሴ 22 ቀን ጣዋት እንድሄድ ተነገረኝ፡፡” ሲል የገጠመዉን ዉጣ ዉረድ አስረድቷል፡፡

እንደሚታወቀዉ ሰሞኑን እየወጡ ያሉ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት አምባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት በጋዜጠኞች ላይ መጠነ ሰፊ ዛቻና ማስፈራሪያ እየፈፀመ ይገኛል፡፡

የደህንነት ኃይሎች ጋዜጠኞችን ማዋከብና ማስፈራራት አጠናክረው ቀጥለዋል፤ – ከበትረ ያዕቆብ

$
0
0

ለረጅም ጊዜ የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ አዘጋጅ ሆኖ ያገለገለዉና የጋዜጣዉ ህትመት ከተቋረጠበት ጊዜ ጀምሮ የኢቦኒ መፅሔት ዋና አዘጋጅ ሆኖ በመስራት ላይ የሚገኘዉ ጋዜጠኛና ብሎገር ብስራት ወልደ ሚካኤል ሰሞኑን በ4 የደህንነት ኃይሎች ታግቶ ዛቻ እና ማስፈራሪያ እንደተፈፀመበት ተናገረ ፡፡ ድርጊቱ የተፈፀመዉ ባሳለፍነዉ ሰኞ (ነሐሴ 20 – 2005ዓ.ም) ከምሽቱ 2፡35 ላይ ከስራ ወደ ቤቱ በጉዞ ላይ እያለ ነበር፡፡

ብስራት ወልደ ሚካኤል እንደገለፀዉ ግለሰቦቹ ለ50 ደቂቃ ያህል ያገቱት ሲሆን ፤ ከአሁን በኋላ በየትኛውም ጋዜጣ ፣ መፅሔትም እንዲሆም ብሎግ ላይ ብትፅፍ በህይወትህ ላይ ፈርደህ ነዉ ሲሉ ዝተዉበታል፡፡ በመጨረሻም በጥፊ መተዉታል፡፡ ብስራት እንደገለፀዉ ከሰዎቹ መካከል አንዱ ሽጉጡን እየደጋገመ በማሳየት ሊያስፈራራዉ ሙከራ ያደረገ ሲሆን ፤ ሌላኛዉ ደግሞ እንዳይንቀሳቀስ ሴንጢ በሆዱ ላይ ደግኖበት ነበር፡፡ ጋዜጠኛ ብስራት አያይዞም “አቶ መለስ ዜናዊ አለዉ ከተባለዉ 3 ቢሊዮን ዶላር እና ልጁ ከታማችበት 5 ቢሊዮን ዶላር እንዲሁም የፀረ ሽብርተኝነት ህጉን በሚመለከት የፃፋኳቸዉ ፅሑፎች እንዳናደዷቸውና እንዳበሳጯቸው በንግግራቸው ይጠቃቅሱልኝ ነበር” ሲል ተናግሯል፡፡

“ይህን የጋዜጠኝነት ሙያየ ወድጄና ፈልጌ በመማር የገባሁበት እንጂ ተገድጄና ተመድቤበት የምሰራው አይደለም ፤ ከዚህም ሙያ ልወጣ አልችልም ” የሚል ምላሽ ሰጠኋቸዉ ሲል የተናገረዉ ጋዜጠኛ ብስራት ፤ አያይዞም ፀያፍ ስድብ እንደሰደቡትና ከወላጅ አባቱ ጋር በተያያዘ የተናገሩት አሳዛኝ ነገር እንደነበረ ጠቁሟል፡፡ አያይዞም “ከግለሰቦቹ መካከል አንዱን ልደታ ፍርድ ቤት በተለይም በሽብርተኝነት የተከሰሱትን የእነ አንዱዓለምንና እስክንድርን ጉዳይ ልዘግብ ስሄድ ሁሌም እዚያ የማላጣው ሰዉ ነበር” ብሏል፡፡

“ይህንን ሁሉ ወዲያው ሳሪስ ለሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ሄጄ ያሳወቅሁ ሲሆን ፤ ያኔ ተረኛ መርማሪ ፖሊስ የነበረው ኮንስታብል ጥላሁን ታዴ የተባለ ሰዉ ያንተ ጉዳይ ከበድ ስለሚል የጣቢያው ዋና ኢንስፔክተር አበበ አያሌው ሲመጣ ጠዋት ንገረው አለኝ፡፡ በሰዓቱ የሚተባበረኝ ፖሊስ ቢኖር ግን የገቡበትን አቅጣጫ ስላየሁ አጋቾቹን እናገኛቸው ነበር ፤ ግን በሰዓቱ ለሚቀጥለዉ ቀን ከመቅጠር በቀር የተባበረኝ አልነበረም፡፡” በማለት ጋዜጠኛ ብስራት ተናግሯል፡፡ አያይዞም “በነጋታው ማክሰኞ ጠዋት ነሐሴ 21 ቀን ዋና ኢንስፔክተር አበበን ለማናገር ወደ ጣቢያው ብሄድም አሁን የሉም ፣ ለስብሰባ ወጥተዋል ተብዬ ከሰዓት እንድመለስ ተነገረኝ፡፡ ከሰዓትም ስሄድ ተመሳሳይ መልስ ከተሰጠኝ በኋላ ለረቡዕ ነሐሴ 22 ቀን ጣዋት እንድሄድ ተነገረኝ፡፡” ሲል የገጠመዉን ዉጣ ዉረድ አስረድቷል፡፡

እንደሚታወቀዉ ሰሞኑን እየወጡ ያሉ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት አምባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት በጋዜጠኞች ላይ መጠነ ሰፊ ዛቻና ማስፈራሪያ እየፈፀመ ይገኛል፡፡934939_487240494685925_524628143_n

Art: በሕይወትም በሕልፈቱም እያነጋገረ ያለው ደራሲ ስብሐት ገ/እግዚአብሔር

$
0
0

ከብርሃኑ ዓለሙ

በቅርቡ ከ25 በላይ በሆኑ ፀሐፊዎች፣ ገጣሚዎችና ሰዓሊዎች ስለ ስብሐት ያላቸውን የነፍስ ወከፍ ልቡሰ ጥላ አንድ ላይ አጣምረው መንጉለዋል፡፡ መንጎላቸው ዳጎስ ያለና ባለ 278 መጽሐፍ ተገላግሏል፡፡ ስለ ስብሐት ትናንትም፣ ዛሬም፣ ነገም ይፃፋል፡፡ በሁለት ጎራ በጅር በጅር ሆኖ በብዕር መፋለሙ፣ በመድረክ መከራከሩ ይቀጥላል፡፡ ምክንያቱም ስብሐት አወዛጋቢና አከራካሪ ደራሲ ነውና፡፡
ክርክሩ “መልክአ ስብሐት” የሚል ሥያሜ በተሰጠው መድበልም ታይቷል፡፡ “ሰለሜ ሰለሜ” እንደተሰኘው የአገራችን የደቡብ ጭፈራ ተያይዘው መስመር ያበጁ የደራሲው አድናቂዎችና «አምላኪዎች» በአንድ ወገን፣ «ቤተ ክርስቲያን እንደገባች ውሻ» የሚጠየፉት ደግሞ በሌላ ወገን የብዕር ሙግታቸውን አፋፍመዋል፡፡ የንግግር፣ የመፃፍ፣ ሃሳብን በነፃነት ያለምንም ከልካይ መግለፅ ከዚህ እንደ ምሣሌ መውሰድ ይቻላል፡፡
Sebhat-Gebregziabher
ዓለማየሁ ገላጋይ፣ የኢትዮጵያ ዘመናዊ ልቦለድ ከስብሐት ይጀምራል የሚለው ሃሳቡን እጅግ ከሚቃወሙት ኢትዮጵያውያን መካከል አንዱ ነኝ፡፡ በሃሳብ ልዩነት መፍጠር የሥነ ጽሑፍም በሉት የጥበብ አንዱ መገለጫ፣ ከፍ ሲልም ውበት ነው ማለት ይቻላል፡፡ ዓለማየሁ ገላጋይ ሳያውቀኝ ሳላውቀው እንዲሁ በደምሳሳው ብቻ “አምባ ገነን ” ይመስለኝ ነበር፡፡ ልክ እንደ ኤፍ ኤም አዲስ 97.1ዱ የ“ርዕዮት” ፕሮግራም አዘጋጁ ቴዎድሮስ፡፡ ዓለማየሁ በዚህ መድበል ስመለከተው ግን “ተሳስቻለሁ ማለት ነው?” ብዬ ራሴን ጠየቅኩ፡፡ ዝርዝር ባህርዩን ለማወቅ የዓለማየሁ “ማንዋ” መጠየቄ አይቀርም፡፡
አንዳንድ የአገራችን ጋዜጠኞች ይገርሙኛል፡፡ እነሱ ልክ ነው ብለው ያመኑበትን ሃሳብ የሚቃወም ሲያጋጥማቸው ዱላ ከማንሳት አይመለሱም፡፡ ስለ ዴሞክራሲ አስፈላጊነት እያወሩ፣ ነገር ግን ሰው ተቃራኒ ሃሳብ ሰጠ ብለው ይወነጅላሉ፡፡ ዴሞክራሲ መጀመሪያ ነገር ከራስ ይጀምራል፡፡ ከሚስት/ከባል፣ ከልጅ፣ከጎረቤት ወዘተ እኔ የባለቤቴን የመናገር ወይም አስተያየት የመስጠት መብት የምፃረር ከሆነ እንዴት አድርጌ ነው የሌላውን መብት የምጠብቀው? በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙ መፃፍና ብዙ መነጋገር ይቻላል፡፡ አሁን ግን ወደ ጀመርኩት ርዕሰ ጉዳይ መመለስ ግድ ይለኛል፡፡
“ስብሐት ገብረእግዚአብሔርን ከሌላ ማዕዘን” የሚለው የሚካኤል ሽፈራሁ(ው?) መጣጥፍ በጥሩ ሁኔታ ጊዜ ተሰጥቶና ታስቦበት የተሠራ በመሆኑ ሳላደንቅ ባልፍ ኅሊናዬ ይታዘበኛል፡፡ ይሁን እንጂ ሚካኤል ያነሳቸው ነጥቦች ሙሉ በሙሉ ልክ ናቸው ማለቴ አይደለም፡፡ ሚካኤል ያየበት መንገድ የግሉ አተያይ(አንግል) ነውና አስተያየቱን አከብራለሁ፡፡
ብዙዎቹን ፀሃፊዎች በጅምላ መፈረጁ ከባድ ቢሆንም፣ አንዳንዶቹ ግን ሌሎች ያሉትን መነሻ በማድረግ የፃፏቸው፤ ያው የተለመደ የመወዳደስ፣ የመካካብ፣ ወይም በሌላ አገላለጽ የጓደኝነት ስሜት የሚታይባቸው ናቸው፡፡ በርዕስ ከፋፍዬ መተቸትና መተንተን እችላለሁ፡፡ ነገር ግን ይሄ የጋዜጣ ገጽ እንጂ የመጽሔት ያህል እንኳ ነፃነት የሚሰጥ ስላልሆነ በዚያ መሠረት አልሄድኩበትም፡፡
ስብሐት፣ በኢትዮጵያ ረዥምና አጭር ልቦለድ ታሪክ ውስጥ ሁነኛ ሥፍራ የያዘ ትልቅ ደራሲ መሆኑን ማስተባበል አይቻልም፡፡ ስብሐት በቋንቋ ውበቱ፣ በአፃፃፍ ስልቱ፣ በጭብጥ አመራረጡ፣ በገፀ ባህሪያት አሳሳሉ፣ ከመቀመጫዬ ተነስቼ “ዱስቱር” እለዋለሁ፡፡ የስብሐት፦ “አምስት ስድስት ሰባት” አጭር ልቦለድ፣ በኢትዮጵያ አጭር ልቦለድ ታሪክ “ማስተር” ነው ብዬ ባሞካሸው አይበዛበትም፡፡ እነ “እቴ እሜቴ”፣“እኔ ደጀኔ”፣“ሞትና አጋፋሪ እንደሻው”፣”አምስት ስድስት ሰባት” የአጭር ልቦለድ መመዘኛን ከሟሟላታቸው በተጨማሪ ለማስተማሪያ የሚሆኑ ታሪኮች ናቸው፡፡
ስብሐት፣ ከሌሎች ደራስያን የሚለይባቸው ብዙ ባህሪያት አሉት፡፡ አንደኛው፣ ከአብዛኛው ሰው በሃሳብ የማይስማማውን አካፋን አካፋ በማለት ልማዱ የተነሣ ነው፡፡ ስብሐት፣ የመሰለውን እንደመሰለው እንደወረደ ይጽፋል፤እንደወረደ ይናገራል፡፡ በተለይም በወሲብ ዙሪያ ያለው አቋሙ ለብዙዎቹ ኢትዮጵያውያን (በድብቅ ተወልደን በድብቅ እንደግ ለሚሉት) መራራ እውነት ነው፡፡ የወሲብ ርዕስ እንዲህ እንደወረደ መፃፍ “ብልግና ነው” ብለው ፈርጀው ያበቁት፣ ዓይንህን ለአፈር ይሉታል፡፡ ሌሎቹ ደግሞ በሚያጨሰው እፀ ፋሪስ ምክንያት እጅግ ይኮንኑታል፡፡ ደግሞ ሌሎቹ፣ ትውልድን አበላሽቷል (አኮላሽቷል) ብለው ይከሱታል፡፡ “ኲሉ አመክሩ አጽንኡ ወ ዘሰናየ” ተብሎ በተቀኘበት አገር ይህን ያህል ማማረር ግን ተገቢ ነው ወይ? የሚለውን ጥያቄ አንስቼ ባልፍ ደስ ይለኛል፡፡
የስብሐት መንገድ ለየት ያለ ነው፡፡ እኔ ብመኘውም ወይም እሆናለሁ ብዬ ፀጉሬን ባንጨባርር፣ ጺሜን ባጎፍር፣ ለመፈላሰፍ ያዙኝ ልቀቁኝ ብል፣ እንደወረደ እናገራለሁ ብዬ ባቅራራ አይሆንም፡፡ ምክንያቱም ስብሐት የተሠራበት ቀመር የሚያገለግለው፣ ለስብሐት ብቻ ነው፡፡ እኔ ደግሞ ሌላ ቀመር ነኝ፡፡ ብዙዎቹ በእሱ ፍቅር አበድን ብለው፣ የእሱ መንገድ የጥበብም የሕይወትም ነው ብለው ያመኑ፣ ከማመንም በላይ የተጠመቁ አጓጉል ሲወድቁ የምናየው ለዚህ ነው፡፡ የስብሐትን ጎዳና እንከተላለን ብለው ተነስተው ከጎዳናው አፈንግጠው እንደ ገል ተሰባብረው የወደቁ የትየለሌ ናቸው፡፡
ስብሐት፦ በኢትዮጵያ ምድር ሊደገም የማይችል፣ በእኛ እምነት ጥሩም መጥፎም ልማድና አስተሳሰብ የነበረው ደራሲ ነው፡፡ የስብሐት የቋንቋ አጠቃቀም ቀለል ያለ፣ እንደ ውኃ የሚጠጣ የማያነቅፍና ውብ ነው፡፡ ገፀ ባሕሪያቱን ሲያዋቅር ደምና ሕይወት በመስጠት ነው፡፡ የአእምሮው ምጡቅነት ገና፣ ገና አንብበንና ተመራምረን አንጨርሰውም፡፡ በኢትዮጵያ የድርሰት አፃፃፍ ያልተለመደ ጭብጥ፣ “እንዴ እንዲህም አለ እንዴ?” ሊያሰኝ የሚችል፣ ግርምትን የሚፈጥር የጥበብ መንገድ በማሳየት ስብሐት ፋና ወጊ ነው፡፡ ስብሐት ዝና ከአገር አገር የሚንቦገበገው፣ ኖቤል የሚያሸልመው ከዓመታት በኋላ ነው፡፡ ስብሐት የቀደደው የጥበብ መንገድ፣ ድንቅነቱ ፍንትው ብሎ የሚወጣው አዎ ወደፊት ነው፡፡ እነ አጋፋሪ እንደሻው፣ ኮምቡጡር…
ስብሐት መሞቱን የሰማሁ ዕለት አላለቀስኩም፡፡ ነገር ግን ማስቀበር እንዳለብኝ አምኜ ሎሚ ሜዳ ከሚባል ለኑሮዬም ለመቀበርያዬም ከመረጥኩት አካባቢ መጣሁ፡፡ ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን ከሰው በፊት ተገኝቼ፣ ከሰው በፊት ወጣሁ፡፡ “ለምን ወጣህ?” ካላችሁኝ መልስ አለኝ፡፡
በቅድስት ሥላሴ በወቅቱ በአፀደ ነፍስ በነበሩት አባታችን አቡነ ጳውሎስ አጋፋሪነት የተካሄደው የቤተ ክርስቲያንና የቀብር ሥነ ሥርዓት በፍፁም ሊዋጥልኝ አልቻለም፡፡ ምክንያቱም ስርዓቱ ረጅም ነበር።
በጥበብ ሐድራ ከገባ በኋላ ኃይማኖት ለስብሐት ምኑ ነበር? በእርግጥ በልጅነቱ በወላጆቹ ሣቢያ “ሥጋ ወደሙ” ተቀብሎ ይሆናል (ክርስትና መነሳቱን ሰምቻለሁ)፡፡
እኔ የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ አንዳንዴ የማምንበትን ሳይሆን፣ የሚያምኑበትን እከተላለሁ፡፡ የማልፈቅደው እንኳ ቢሆን ከማኅበረሰቡ የኑሮ ማዕቀፍ ላለመውጣት እተጋለሁ፡፡ በዚህም ባሕሪዬ በአደባባይ፣ “እኔ አድር ባይ ነኝ” ብዬ ተናዝዤ ንስሃ ከገባሁ ቆይቻለሁ፡፡ አድር ባይ ፀሐፊ እንደምን የጥበብ ማኅበርተኛ ሊሆን ይችላል? ካላችሁ፣ “የምወዳችሁና የማፈቅራችሁ ጥበበኞች ከልብ ካሰቡበት እምባ አይገድም፡፡ ይቻላል” እላችኋለሁ፡፡ ትንሽ ምሣሌ ልስጣችሁ፡፡ ወሲብን በሚመለከት የዕድሜ እርከን ተጠብቆ በግልጽ መነጋገር ቢቻል ደስ ይለኛል፡፡ በዚህም አቋሜ ከጓደኞቼ ከሠራዊት ፍቅሬ ጋር በገደብ፣ ከመሐልየ መሐልየ ዘ ካዛንቺስ ደራሲ ተድባበ ጥላሁን ግን ያለ ገደብ በነፃነት እናውራ፣ አንዳንዴም እንፈላሰፍ እንደነበር ትዝ ይለኛል፡፡ ተድባበ ነፍሱ ይማር ተአምረኛ ሰው ነበር፡፡ እኔና እርሱ ባለንበት “ታቡ” የሚባል የለም፡፡ ከሌሎች ወግ አጥባቂዎች ጋር ስደባለቅ ግን አመሌን በጉያዬ እይዛለሁ፡፡ እኔ በባህሪዬ በጣም ጥብቅ ዲሲፕሊን አላቸው ከሚባሉት ተርታ እንደምመደብ ይሰማኛል፡፡ “እኔ የማምነው በዚህ መንገድ ነው ብዬ ግን ከጀማው መነጠል አልፈልግም፡፡ አንድ ሰው ባጣሁ ቁጥር፣ አንድ ጣቴ የተቆረጠ ያህል ያመኛል፡፡ ለክርክር ስጋበዝ፣ አቋሜን ስጠየቅ ግን በይፋ ለማስረዳት እሞክራለሁ፡፡ በመሆኑም አድር ባይ ፀሃፊ ተገኘ ብላችሁ አደራችሁን “ጊነስ ቡክ” ላይ እንዳታስመዘግቡ፡፡ በጣም ብዙ ምክንያቶችና እውነቶች ስላሉኝ፣ ከፍርድ በፊት ቃሌን ብትቀበሉኝ ማለፊያ ነው፡፡ የለም እንፈርድብሃለን የምትሉም ከሆነ የጋዜጣ ገጽ ስለማይበቃ የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር መድረኩን ያዘጋጅና ዲሞክራቲክ የሆነ ክርክር አካሂደን ሕዝበ ውሳኔ ይካሄድ፡፡
እኔ አልቃታለሁ እንጂ የስብሐት ገድል፣ የስብሐት ዘመን ተሻጋሪ ምልከታ አያልቅም፡፡ ስብሐት፣ ሞትን ሲሸሽ ኖሮ በሞት የተሸነፈ፣ ነገር ግን ድንቅ ሥራዎቹ ሞትን መቶና ሁለት መቶ ጊዜ ያሸነፈ ጊዜ የማይሽረው ደራሲ ነው፡፡ በእርግጥ በእኛ ዓይን የባህሪ ችግር ነበረበት ማለት እንችላለን፡፡ የማኅበረሰቡ እሴት፣ ወግና ልማድ መጠበቅ አልፈቀደም፡፡ ይሄ ደግሞ እምነቱም ፍላጎቱም አልነበረም፡፡ ስብሐት፣ በኢትዮጵያ ምድር ለጉድ ፈጥሮት ለጉድ አኖሮት ያመለጠን ደራሲ ነው፡፡ ስብሐት የሞተ ዕለት አላለቀስኩም ብያችኋለሁ፡፡ አሁን፣ አሁን ግን በዚች ምድር ቀድሞም፣ አሁንም ወደፊትም ወደር የማላገኝላት እናቴ ብዙነሽ ሐብቴንና ስብሐትን ባስታወስኩ ቁጥር አለቅሳለሁ፡፡ እንባዬ ጉንጬ ላይ ባይወርድም በሆዴ አነባለሁ፡፡ ወንድ ልጅ እፊቱ ላይ እንባ ከማውረድ ይልቅ ሆዱ ውስጥ ያለቅሳል?
በሃሳቡ በጣም የወደድኩት ሚካኤል፣ የስብሐት ነውር ብሎ ከገለፃቸው መካከል ብዙ ወጣቶች እሱን እንከተላለን ብለው ከመስመር መዛነፋቸው አንዱ ነው፡፡ እሱ ራሱም የስብሐት እንደነበር ጠቅሷል፡፡ ነገር ግን ማንነቱን ፈልጎ፣ የራሱን መንገድ አግኝቶ ከጀማው ተገነጠለ፡፡ የራሱን ዕድል በራስ የመወሰን መብት እስከ መገንጠል የተፈቀደ ነውና ይህ አቋሙን ልንኮንነው አይገባም፡፡ ነገርግን አቶ ሚካኤልን የምጠይቀው ስብሐት የሚናገረውን፣ የሚያወራውን፣ ውሎውን… ተመልክቶ ወዶና ፈቅዶ በገዛ ሥልጣኑ እጁን ሰጥቶ ተማርኮ ለደረሰበት ጉዳት ስብሐት ምን ያድርግ? ስብሐት፣ አይደለም ሌላውን የገዛ ራሱንም ጥሏል እያልነው ሌላውን የማዳን ሥራ እንደምን ሊሆንለት ይችላል? ስብሐት የቀይ መስቀል መልዕክተኛ እኮ አይደለም፡፡ ለተጎዱ ወገኖች ድንኳንና ቀለብ አያቀርብም፡፡ ስብሐት፣ ለየት ያለ የጥበብ ሰውና “ሕይወትን ከእነ ብጉንጇ” ማሳየት የሚችል ደራሲ ነው፡፡
እኔ ይህ ጽሑፍ የፃፍኩላችሁ ዳተኛ፣ ከስብሐት ጋር አንድም ቀን ቁጭ ብዬ በግንባር ተነጋግሬ አላውቅም፡፡ በ1986 ዓ.ም የዘንባባ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሳለሁ፣ “ልብ ያለው ልብ ይበል” የሚል ገጽ ላይ ስጽፍ አንድ ስታይል ለማውጣት ሞክሬ ነበር፡፡ “ይድረስ ለሰማይ ቤቱ አጋፋሪ እንደሻው፣ ግልባጭ ለምድሩ ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር -ደራሲ” በሚል ርዕስ ከሰማይ ቤት ወደ ምድር፣ ከምድር ደግሞ ወደ ሰማይ ቤት ጥበባዊ መልዕክት እንዲተላለፍ አደርግ ነበር፡፡ ገጹን የፈጠርኩት ለእርሱ በነበረኝ ፍቅርና ክብር ምክንያት ስለነበር፣ አንብቦት ከሆነ አስተያየት እንዲሰጠኝ ብዬ አንድ ቀን ስልክ ደወልኩለት፡፡ በትህትና ራሴን አስተዋውቄ፣ ርዕሰ ጉዳዩና ስታይሉን እንዴት እንዳገኘው ስጠይቀው ሰደበኝ፡፡ ለስድቡ ምላሽ በስክ ከመስጠት ተቆጥቤ በዚሁ ተለያየን፡፡ በዚህም ቂም ይዤበት በ17 ዓመታት የጋዜጠኝነት ዘመኔ አንድም ቀን ኢንተርቪው አድርጌው ወይም እርሱን የሚመለከት ጽሑፍ ጽፌ አላውቅም፡፡ በዚህ ሙያየዬ እጅግ ብዙ የጥበብ ሰዎችን ኢንተርቪው አድርጌያለሁ፡፡ ሚኒስትሮች፣ የመምሪያ ሥራ አስኪያጆች፣ ዘፋኞች፣ የተለያዩ ባለሙያዎች …፡፡
በወዳጄ ስንዱ አበበ አማካኝነት የስብሐት የታተሙና ያልታተሙ ሥራዎችን ቀደም ብዬ አንብቤ ልዩ ሥፍራና ክብር ሰጥቼዋለሁ፡፡ ታዲያ ስብሐትን ይህን ያህል አውቄው ኢንተርቪው አለማድረጌ ወይም በነበረኝ የመፅሔትና የጋዜጣ ምክትል ዋና አዘጋጅነት ስልጣኔ ኢንተርቪው እንዲደረግ አለማድረጌ ወይም ደግሞ ቀርቤ አለማነጋገሬ ጥፋት ነው ካላችሁም የምትቀጡኝን ቅጣት እስከ “ስቅላትም” ቢሆን፣ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ለመቀበል ዝግጁነቴን ሳረጋግጥላችሁ ከልብ ነው፡፡ ቂመኛ የጥበብ ሰው ግን አለ? ሰላም ሁኑ!

Health: እህቴን ሔፕታይተስ ከውጭ ጉዞዋ ያስቀራት ይሆን?

$
0
0

እህቴን ወደ አሜሪካ ለማምጣት ያልቆፈርኩት ድንጋይ አልነበረም። ሆኖም አልተሳካልኝም። እርሷ በጣም ወደ ውጭ ለመሄድ ከፍተኛ ፍላጎት አላት። ካልሆነ ወደ አረብ ሃገርም ቢሆን ላከኝ በሚል ገንዘብ ልኬላት መሰናዳት ጀመረች። በኋላ ላይ ወደ ውጭ ለመሄድ ባደረኩት የጤና ምርመራ ሔፖታይተስ ‹‹ቢ›› አለብሽ ተባልኩኝ አለችኝ። ወደ አረብ አገር ሄጄ ሰርታ ራሷን ለማሻሻል ባደረረባት ፍላጎት መሰረት በአንድ ኤጀንሲ በኩል እንቅስቃሴ ጀምራለች። ከጉዞዋ በፊት የተለያዩ የላብራቶሪ እና የአካል ምርመራዎች ኤች.አይ.ቪን ጨምሮ አድርጋ ሁሉን ነፃ ስሆን ሔፕታይተስ ‹‹ቢ›› የሚባል ሰምቼ የማላውቀው ችግር በደምሽ ይታያል ተባልኩ አለችኝ። ምን አይነት በሽታ ነው? ምንድነው የእህቴ የወደፊት እጣ ፈንታዋ?
የከበቡሽ ወንድም

የዶ/ር ዓብይ ምላሽ፡- ውድ ጠያቂያችን እህትህ በአጋጣሚ ለሜዲካል ቼክ አፕ ሄዳ የሔፖታይተስ ‹‹ቢ›› (ሔፖታይተስ ‹‹B›› ሰርፌስ አንቲጅን) ከሌሎች ምርመራዎች መካከል ይህ ምርመራ በደምዋ ውስጥ የሔፖታይተስ ቫይረስ እንዳለ ጠቁሟል፡፡ በአጠቃላይ ወደ አምስት የሚደርሱ ሔፖታይተስ ‹‹A›› ሔፖታይተስ ‹‹B›› ሔፖታይተስ ‹‹C›› ሔፖታይተስ ‹‹D›› እና ሔፖታይተስ ‹‹G›› የተባሉ ጉበትን ለጉዳት የሚያጋልጡ የቫይረስ አይነቶች (cirrhosis) እስከ ጉበት ካንሰር በሄፖታይተስ B,C እና D የበሽታ ደረጃዎች ሊከሰቱ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ሁሉ የሔፓታይተስ ቫይረሶች የሚከፋፈሉት በሞለኪዩላቸው እና በአንቲ ጅን ፀባያቸው ነው፡፡
hepitates Bየ እህትህ ችግር የሚያያዘው ከሔፖታይተስ B ጋር ሲሆን ይህ ቫይረስ ከሌሎቹ አራቱ ይለያል፡፡ ይኸውም ሌሎቹ አር ኤን ኤ (RNA) ቫይረሶች ሲሆኑ ሔፖታይተስ ‹‹B›› ዲ.ኤን.ኤ ቫይረስ ነው፡፡ ሔፖታይተስ ‹‹B›› ከነሙሉ አካሉ ‹‹ዳን›› ፓርቲክል ሲባል 42 ናኖ ሜትር ይለካል፡፡ ይህም በኤሌክትሮን ማክሮስኮፕ እንደ ባክቴሪያዎች ለመታየት አያስችለውም፡፡ ቫይረሱም 22 ናኖ ሜትር የሚሆን የውስጥ አካል ሲኖረው ከላይ የሚሸፍነው ከፕሮቲን የተሰራ ሽፋን ወይም የሔፖታይተስ ቫይረስ ሽፋን አንቲጅን አለው፡፡
ይህም ሽፋን በቫይረሱ በተጠቁ የጉበታችን ሴሎች በብዛት ይመረትና በደማችንና በሰውነታችን ፈሳሾች ከቫይረሱ ተለይቶ መጠኑ 22 ናኖ ሜትር በሚሆን ብናኞች (particle) መልክ በብዛት ከቫይረሱ ውጭ ይሰራጫል፡፡ በጠያቂያችን ደም ውስጥ ሔፖታይተስ ‹‹B›› ቫይረስ እንዳለ የታወቀውም በዚህ የቫይረሱ ሽፋን አማካኝነት ነው፡፡
ሔፖታይተስ ‹‹B›› በቀጥታ የሰውነታችን ሴሎችን አያጠቃም፡፡ ነገር ግን በጉበታችን ላይ የሚደርሰው ጉዳት የሚፈጠረው የራሳችን መከላከያ ኃይል ቫይረሱን ለማጥፋት በሚከፍተው ጦርነት ነው፡፡
ሔፖታይተስ ‹‹B›› በመላው ዓለም ሲገኝ እስካሁን ከ2 ቢሊዮን በላይ ሰዎች ውስጥ እንዳለ ይገመታል፡፡ ይኸውም ከዓለማችን ከሶስት ሰዎች መካከል በአንዱ ውስጥ አለ እንደ ማለት ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ ወደ 300 ሚሊዮን የበሽታው ተሸካሚ እንዳሉ ይገመታል፡፡ አሜሪካ እና እንግሊዝ ዝቅተኛ የተሸካሚ ቁትር ሲኖራቸው ማለትም ከአንድ ሺ ሰዎች መካከል አምስቱ የተያዙ ሲሆን በአፍሪካ በመካከለኛውና በሩቅ ምስራቅ ኤሺያ የተሸካሚ ቁጥር 15 በመቶ ይደርሳል፡፡
ይሄ ቫይረስ የሚተላለፈው በደም (ማለትም ለበሽተኛ የተበከለ ደም ሲሰጥ፣ የተበከለ መርፌ በመጠቀም፣ በተበከለ ስለት ንቅሳት ሲደረግ)፣ ከታማሚው ጋር የቅርብ ግንኙነት (ንክኪ)፣ የግብረ ስጋ ግንኙነት (በተለይ የግብረ ሰዶም) ናቸው፡፡ ስለዚህ መተላለፊያው መንገድ ከኤች.አይ.ቪ ጋር ሲመሳሰል የጤና ባለሙያዎች በስራ ጊዜ ከበሽተኛ ፈሳሽ ጋር በሚያደርጉት ግንኙነት በኤች.አይ.ቪ የመያዛቸው ዕድል ወደ 2 በመቶ ሲሆን ሔፖታይተስ ‹‹B›› ግን 35 በመቶ ነው፡፡ በተጨማሪም በወሊድ ጊዜ ከእናት ወደ ልጅ ይተላለፋል፡፡
በአብዛኛው በዚህ ቫይረስ የተለከፈ ሰው በሽታው አይታይበትም፡፡ ቫይረሱ (ሔፖታይተስ ‹‹B›› በደሙ/ዋ ውስጥ መኖሩ የሚታወቀው በአጋጣሚ በሚደረግ የጤና ቼክአፕ ምርመራ ነው፡፡ በጠያቂያችን እህትም የተፈጠረው ይኸው ነው፡፡ ነገር ግን አንዳንዴ ቫይረሱ በርካታ የህመም ስሜት ይፈጥርና ተጠቂው ወደ ሐኪም ዘንድ ይመጣል፡፡ በመጀመሪያም በሽተኛው የህመም ስሜት ይሰማዋል፣ ቋቅ ቋቅ ይለዋል፣ ምግብ ያስጠላዋል፣ ሲጋራ የሚያጤስ ከሆነ ሲጋራ ያስጠላዋል በዚህ ጊዜም አይኑ ላይ ቢጫ የመሆን ምልክት አያሳይም፡፡ ከአንድ ወይም ከሁለት ሳምንት በኋላ አንዳንድ በተለምዶ የወፍ በሽታ የሚባለው ሌላው የህመም ስሜታቸው ጎልቶ ይታያል፡፡
የዓይን ቢጫ መሆኑ እየደመቀ ሄዶ ሽንት ጠቆር ሰገራም ነጣ ይላሉ፡፡ ጉበትና ቆሽት መጠነኛ ማበጥ ያሳያሉ፡፡ አልፎ አልፎ የንፍፊቶች ማበጥ ሊታይ ይችላል፡፡ ከዚህ በኋላ የዓይን ቢጫ መሆን በራሱ ጊዜ እየጠፋ ታማሚው ከሶስት እስከ ስድስት ሳምንታት ይሻላታል ወይም ይሻለዋል፡፡ ከጉበት ውጭ በጣም አልፎ አልፎ፣ መገጣጠሚያ፣ የደም ስሮች፣ የልብ ግድግዳ፣ ኩላሊትንም ሊጎዱ ይችላሉ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ በሽታው ሊያገረሽ ሲችል በዚህን ጊዜ የዓይን ቢጫ መሆኑ በድጋሚ ይከሰታል፡፡ በጣም አልፎ አልፎ በሽታው ጉበትን እጅግ አጥቅቶ አጣዳፊ ደረጃ ደርሶ የጉበት ኮማ የሚባል ፈጥሮ በሽተኛውን ሊገድለው ይችላል፡፡
10 በመቶ የሚሆኑት አክዩት ሔፖታይተስ ‹‹B›› (acute hepatitic B…) በሽታ የያዛቸው ደግሞ በሽታው ወደ ክሮኒክነት (Chronic Hepatitic B infection) ይለወጥባቸዋል፡፡ ከዚህም ውስጥ ከ70-90 በመቶ የሚሆኑት ጤናማ ተሸካሚ ሲሆኑ ጠያቂያችን ከዚህ ግሩፕ እንደምትመደብ እገምታለሁ፡፡ ሌሎቹም ክሮኒክ ከሆነባቸው ከ10-30 በመቶ የሚሆኑት ክሮኒክ ሔፖታይተስ የሚባል ደረጃ ሲደርሱ ከዚያም የጉበት መሸብሸብ (Cirrhosis) ብሎም የጉበት ካንሰር (Hepatocellular carcinoma) ይሆንባቸዋል፡፡ ነገር ግን ጤነኛ ተሸካሚ ይሆናሉ ከተባሉ ስንቱ ወደ ፊት የጉበት ካንሰር ከጊዜ ብዛት እንደሚይዛቸው ገና ግልፅ አይደለም፡፡
ድንገተኛ የሔፖታይተስ ‹‹B›› ኢንፌክሽን (የወፍ በሽታ) የሚታይበት ታማሚ ወደ ሐኪም ዘንድ ሲሄድ የተለያዩ ከጉበት ጋር የተገናኙ የደም ምርመራዎ፣ ሌሎች የአንቲቦዲ ምርመራዎች፣ የሽንት ምርመራ ወዘተ… ይደረግለታል፡፡ ሌሎች ተቀራራቢ ምልክት የሚያሳዩ በሽታዎች መኖር አለመኖራቸው መረጋገጥ አለባቸው፡፡
ወደ ክሮኒክነት ያልተለወጠ አክዩት ሔፖታይተስ ከድጋፍ ሰጪ ህክምና በስተቀር አያስፈልገውም፡፡ ከላይ እንደተጠቀሰው በራሱ ጊዜ እየዳነ ይሄዳል፡፡
ክሮኒክ የሆነ ሔፖታይተስ ‹‹B›› ኢንፌክሽን ያላቸው ታማሚዎች መታከም አለባቸው፡፡ የህክምናውም አላማ ሔፖታይተስ ‹‹ቢ›› እና ‹‹ኢ›› የተባለውን አንቲጂን እና የሔፖታይተስ ‹‹ቢ›› ቫይረስ ዲኤንኤ ከደም ውስጥ ማጥፋት ነው፡፡ ይህም በጉበት ሴሎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ይቀንሰዋል፡፡ ሔፖታይተስ ‹‹ቢ›› ቫይረስ ዲ.ኤን.ኤ ከደም ውስጥ ማጥፋት ነው፡፡ ይህም በጉበት ሴሎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ይቀንሰዋል፡፡ ሔፖታይተስ ‹‹ቢ›› እና ‹‹ኢ›› አንቲጅን ከደም ውስጥ ከጠፋ የበሽታው የመመለስ ዕድል ይቀንሳል፡፡ ታማሚው ከደሙ ሔፖታይተስ ‹‹ቢ›› እና ‹‹ኤስ›› አንቲጅን ቢታከመውም በደም ውስጥ ቆይቶ የበሽታው ተሸካሚ መሆኑ ይቀጥላል፡፡ አብዮተኞቹ ግን በስተመጨረሻም ይሄም አንቲጅን ከደማቸው ይጠቀፋላቸዋል፡፡
አሁን አሁን በየዓመቱ አዳዲስ መድሃኒቶች ይህንን ክሮኒክ ሔፖታይተስ ለማከም ፈቃድ እየተሰጣቸው ሲሆኑ ዋና ዋናዎቹ መድሃኒቶች አልፋ ኢንተርፌሮን (a interferon) እና ፀረ ቫይረስ (anti viruses) ናቸው፡፡
መከላከያው ለበሽታ የማያጋልጡ ሁኔታዎችን ለምሳሌ የተበከሉ (ሊበከሉ የሚችሉ መርፌዎችን) ማስወገድ፣ በርካታ የግብረ ስጋ ጓደኞችን መተው (ልቅ የግብረ ስጋ ግንኙነት ማስወገድ)፣ ለበሽተኛ የሚሰጥ ደም ከቫይረሱ ነፃ መሆኑን ማረጋገጥ፣ የጤና ባለሙያዎች ከበሽተኛ የአካል ፈሳሽ ጋር ያላቸውን ግንኙነት መቀነስ ወይም ጓንት መጠቀም እና ክትባት መውሰድ ናቸው፡፡

Semayawi Party defies protest ban (video)

$
0
0

Semayawi Party defies protest ban (video)

የማለዳ ወግ … ይነጋል ጨለማው … !

$
0
0

የመውጫ ቪዛ_02(2)-1-1-1
ከነብዩ ሲራክ

የጨለመ ቀን ይነጋል ፣ ክፉ ቀን ያልፋል ! የሃገር መሪዎች ለህዝብ ቆመው ትክክለኛ ምርጫ እንኳ አድርገው ስልጣናቸውን ለተተኪው ትውልድ ባያስተላልፉ ሲያረጁና ሲያፈጁ ጥቅማቸውን የሚያስከብርላቸው ተክተውም ቢሆን መሸኘታቸው አይቀሬ ነው! ለህዝብ እና ለሃገር ብሔራዊ ጥቅም ያለተጋ መንግስት በተቀያየረ ቁጥር በዜጎች ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ይህ ነው የማይባል ተጽዕኖን ያሳድራል። ተጽኖ አድራጊነቱ የሚከወነው በዋናነት በመንግስት መሆኑ ባይካድም ለሆዳቸው ያደሩ አጎብጓቢ የአበራካችን ክፋዮች የነዋሪው ውሎ አዳር ላይ የሚያደርሱት ተጽዕኖ እንዲህ በቀላሉ ሊገልጹት የሚችሉት አይደለም! አይቻልምም ! በዘመነ ደርግ ከስርአቱ በላይ አድርባዮች ለስርአቱ ያላቸውን ታማኝነት ለማሳየት ሲሉ ብቻ በገዛ ወገናቸው ላይ ይፈጽሙትን የነበረው ግፍ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው!
ያ ዘመን አከተመ ብለን ትንሽ ሳንተነፍስ ዛሬም በሌላ አደጋ ተዘፍቀናል ። ወደ ትላልቁ ጉዳይ አልገባም ። ዛሬ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ዜጎች በዘመናዊ ባርነት ከህግ ማዕቀፍ ውጭ ስለመሸጣቸው እማኝ በሆንኩበት የአረብ ሃገር ኑሮ የራሳችን ዜጎች መብት ይከብር ብሎ መብታችን ለማስከበር ሃላፊነታቸውን ስላማይዋጡ ሃላፊዎች መናገር ሃጢያት ሆኖ ያስወነጅላል ! ” ህገ መንግስት አልተከበረልንም!” ያሉ ሰላማዊ ዜጎች በተሰጣቸው የህግ ማዕቀፍ መሰረት ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግን ተከልክልው እየተመለከትን ነው ። እኔ እሰከማውቀው እና በአደባባይ ሲነገር እንደሰማሁት አንድ መንግስት በስደት ላይ ያሉ ዜጎቹ ስቃይ ይሰማዋል። ግን ስቃዩን ለማስቆም የሚችሉ ተወካዮችን በአረብ ሃገር ከማሰማራት ጀምሮ በሃገር ቤት የሚሰራውን ለእድሜ ያልደረሱ ታዳጊ እህቶቻችን በደላሎች ወደ አረብ ሃገራት እየተጋዙ የሚፈጸመውን ግፍ ተከታትሎ ማስቆም አልቻለም ። መንግስት ያላቻ ጋብቻ አይፈቀድም እያለ በቤተሰብ አማካኝነት የሚመሰረት ትዳርን ህገ ወጥ ነው ብሎ ማገዱ ባይከፋም ትዳር እንዳትመሰርት በእድሜዋ ምክንያት የተከለከለችው ጉብል ወደ አረብ ሃገር ለስራ ብቁ የሚያደርግ እድሜ ቆልላ እዚህ ሳውዲ አግኝቻት አጫውታኛለች ። ብዙዎች አንድ አይነት ባይሆን በለያዩ መንገዶች በሚከወን ሂደት ይሰደዳሉ ። የድልላ ስራው ከሃገር ቤት እሰክ ውጭ ሃገር በስርአቱ ደጋፊዎች የሚመራ በመሆኑ እንቅስቃሴው በግፍ ሲካሔድ ይህም የስደቱን ኑሯችን እየከፋ ለመሔዱ እማኝ ከሆነን መልካም ነው ።
መንግስት በራሱ ሰአት ከፖለቲካ ፍጆታ ላላለፈው ጥቅም የሚያሳየን የከፋ የስደት ኑሮ ይቀየር ዘንድ የሚሰራው ስራ አያበረታታም። የመንግስት ተወካተዮቻች እንኳንስ ችግር ብሶታችን ሰምተው ሊያሰሙ ፣ እንዳንሰማ እንዳናይ እንዳንሰማ ማግለል ይዘዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከፍተኛ ሃላፊዎች በተደፈጋጋሚ ወደ ሳውዲ ቢመጡም ነዋሪውን አያጋኟቸው ። መረጃ ሰበሰብን ብለው የሚሔዱት ፍትሃዊ የመብት ጥበቃ ከማያደርጉት ሃላፊዎች፣ ከፖለቲካ ካደሬዎችና በልማት ስም ከተደራጁ ማህበራት በመሆኑ ለቀጠለው ችግር መፍትሔ ሊያገኙለት አልቻሉም ! ግፍ ቢበዛም አቤት የሚባልበት ቦታ አጥተናል !የሚነገር የሚጻፈውን አልሰማ ላለ መንግስት ደግሞ የዜጎችን መብት ስል ማስከበር ህገ መንግስቱ የሰጠውን መብት መጠቀምና ጥያቄን ማቅረብ ተገቢ ነው። ተቃውሞን በሰላማዊ ሰልፍ ማቀርብ ደግሞ ብቸኛው ተገቢ መንገድ ነው። ይህንም መብት በመንግስት ስለመራቁና እዚያ ለመድረስ መሔድ ያለብንን ጉዞ አርቆ አጥቦታል! ህዝብ መብቱን ለመጠቀም መንገዱ ከጠበበበት ደግሞ አመጻና የከረረ ተቃውሞን በማምጣት ሃገርን ወደ ሁከት ህዝብን ወዳለመረጋጋት ይገፋልና ተገቢ አይደለም ! በጃንሆይ የሆነው በደርግ ፣ በደርግ የነበረው ተጠናክሮና መንገዱን ቀይሮ በኢህአዴግ መንግስት እየተሰራበት ያለው የመብት ገፈፋ ቆሞ ላስተዋለው ያማል! ሰው በነፃ ሃሳቡ ፣ለሃገሩ ይበጃል ያለውን በግልና በቡድን ህጋዊ በሆነ መንገድ ተደራጅቶ ድምጹን ሰላሰማ ዛሬም ይታሰራል ፣ይደበደባል ፣ ይገደላልም ! ይህ ሁሉ አውጥቸ አወረድኩና ቢከፋኝ በማለዳ ወጋወጌ የዘመን ሂደት ፣ የሰው ለሰው ጉድኝት ትዝብቴን ለማዘከር ” የጨለማው ይገፋል ይነጋል ” ስል ስንኝ ቢጤ ቋጥርኩ …. ይህም ይገኝበታል …
ይነጋል …
“ይሁን ያልፋል ! ” ብለን ዝም ብለን በቻልነው
ያንዱ ቤት ሲፈርስ ባያመው ያ ሌላው
የወገኑ እንግልት ዘልቆ ባይሰማው
ግፍና በደሉ እሱን ሰላልነካው
ነግ በኔን ዘንግቶ አይኑን ቢሸፍነው
ጀሮው እየሰማ “አልሰማሁም “ቢለው
አይን አይቶ እንዳላየ ለእይታ ቢያገለው
የዘመን ክፉ አለው ፣ የዘመን ደግ አለው
እንደከፋ አይቀርም፣ ይነጋል ጨለማው !
ከህሊና ፍርጃ ማያስሸሽ መከራው!
ብርሃን ይመጣል ይነጋል ጨለማው!
(ሙሉውን ግጥም ከዚህ ጋር ተያይዟልና ያንብቡት! )
ቸር ያሰማን !
ነቢዩ ሲራክ

ለሰማያዊ እና አንድነት ፓርቲ ድጋፍ ለማሳየት ነገ በዋሽንግተን ዲሲ ሰላማዊ ሰልፍ ተጠራ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) በአሁኑ ወቅት በሃገር ውስጥ ትግልጉልህ ሚና እየተጫወቱ ላሉት የሰማያዊ ፓርቲ እና የአንድነት ፓርቲን ለመደገፍ እንዲሁም በኢትዮጵያ ውስጥ ካለማቋረጥ እየተፈጸመ ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት ለአለም ሕዝብ እና ለአሜሪካ መንግስት ለማሳወቅ ነገ ማክሰኞ ሴፕቴምበር 3 በዋሽንግተን ዲሲ የሰላማዊ ሰልፍ ተጠራ። የሰላማዊ ሰልፉ ጥሪ ፍላየር ሁሉንም መረጃ ይዟል – ይመልከቱት።
Rally to show solidarity to Semayawi and Andinet party members and protest Human Rights Violations by the regime – Tuesday Sept 3-2013 9AM US Department of StateSemayawi and Andnet solidarity and human rights vioaltions rally (2)


ነሐሴ 25 የሙዚቃ ቃና ፐሮግራም(August 31,2013) –ሴፕቴምበር 02, 2013

$
0
0
የዛሬው የሙዚቃ ቃና ፕሮግራም ሙዚቃ ነክ ዜናዎችን ያስተናግዳል፡፡…

የሶሪያ ጦርነትና የኃያሉ ዓለም ዝግጅት

$
0
0
ፕሬዝዳት ኦባማ የሚተማመኑበትን እቅዳቸዉ ለማስፈፀም-የሚተማመኑበትን ዘመናይ ጦር ከምርጥ መሳሪያዎቹ ጋር አዝምተዋል።የሶሪያ የቅርብ ወዳጆች ሩሲያ፥ ቻይና እና ኢራን የድብደባዉን ዕቅድና ዘመቻ አጥብቀዉ ይቃወማሉ።የሩሲያዉ ፕሬዝዳት ቭላድሚር ፑቲን ከዚሕም አልፈዉ አሜሪካና የተባባሪዎችዋን አቅድ አጣጥለዉ ነቅፈዉታል።…

በአዲስ አበባ የተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ

$
0
0
ከየክልሉ የተውጣጡ የአስተዳደር አባላት እና የሃይማኖት ተጠሪዎች ባለፈው ሳምንት ከማክሰኞ እስከ ኀሙስ በአፍሪቃ ሕብረት አዳራሽ ተገኝተው ሀገር አቀፍ ጉባኤ ማካሄዳቸው ይታወሳል።…

Amharic News 1800 UTC –ሴፕቴምበር 02, 2013

$
0
0
News, Sports, African Topics and Health…

ESAT Radio: Sep 02

$
0
0
  ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

የኢትዮጵያ መንግስትና የሃይማኖት ተቋማት ምክር ቤት የትላንት እሁድ ሰልፍ

$
0
0
የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ምክር ቤት፤ የትላንት እሁድ ሰልፍ  የፖለቲካ ጥቅም ለማግኘት ከአክራሪነት ጋር ተባብረዋል የተባሉ የፖለቲካ ኃይሎች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ፤ ወጣቶችም “ሥልጣን ፈላጊ” ላሏቸው መሣሪያ እንዳይሆኑ ማሳሰቢያ ተሰጠ፡፡ ማሳሰቢያው የተሰማው የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ አዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ላይ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ነው፡፡

የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ምክር ቤት፤ የትላንት እሁድ ሰልፍ –ሴፕቴምበር 02, 2013


ትላንት እሁድ ሳይካሄድ የቀረው የሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍና ጥያቄዎቹ

$
0
0
የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ምክር ቤት፤ የትላንት እሁድ ሰልፍ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ከተመሠረቱት አዲሶቹ የፖለቲካ ድርጅቶች ወገን የሚመደበው የሰማያዊ ፓርቲ አሁንም የተቃውሞ ድምጹን የሚያሰማበት ሰላማዊ ሰልፍ የሚያደርግ መሆኑን ገለጠ። Marthe Van der Wolf ከአዲስ አበባ ለአሜሪካ ድምጽ ባጠናቀረችው ዘገባ እንደጠቆመችው፤ ሰማያዊ ፓርቲ ከመቶ በላይ አባሎቹ ከታሰሩበት በኋላ ለትላንት እሁድ ጠርቶት የነበረውን ሕዝባዊ ትዕይንት መሠረዙን አስታውቋል።

ትላንት እሁድ ሳይካሄድ የቀረው የሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ –ሴፕቴምበር 02, 2013

በሰማያዊ ፓርቲ ላይ የተወሰደውን ህገ-ወጥ ርምጃ አጥብቀን እናወግዛለን!!! ከአንድነት ለዴሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ (አንድት) የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

$
0
0

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ (አንድት) የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም ሰማያዊ ፓርቲ የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ የተወሰደበትን ሕገ-ወጥ ርምጃ አጥብቀን የምንቃወም ሲሆን፤ ይህንን የፈፀሙ አካላትም በአስቸኳይ ለፍርድ እንዲቀርቡ እንጠይቃለን፡፡

እንደሚታወቀው ሰማያዊ ፓርቲ ከአንድ ወር አስቀድሞ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን እንዳሳወቀ የሚታወስ ሲሆን በተመሳሳይ ቀንም የሀይማኖቶች ጉባኤ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱ መገለፁ አደናጋሪ ነበር፡፡ ይህንን የሁለት አካላት የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ በሰከነ መንገድ የአዲስ አበባ መስተዳድር መፍታት ሲገባው ችግሩ እንዲከር አድርጓል፡፡ ይህም የገዥው ፓርቲ የፖለቲካ ምህዳሩን የመዝጋትና የማናለብኝነት አንዱ መገለጫ ነው፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ቅዳሜ ምሽት በሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ላይ የተፈፀመው የሰብዓዊ መብት ጥሰት በሰላማዊ ትግሉ ላይ እየተፈፀመ ያለ ርምጃ ነው፡፡ የፀጥታ ሃይሎች የወሰዱት የማገት፣ የማፈንና የመደብደብ ርምጃ አሳፋሪ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ ፀጥታ አስከብራለሁ የሚለው የፖሊስ አካል መብትን በድብደባ ለማስቆም የሄደበት መንገድም ህገ-ወጥ ነው፡፡ ስለዚህ ፓርቲያችን አንድነት መንግስት እያካሄደ ያለውን የአፈናና የጉልበት ርምጃ አቁሞ አሁንም ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታና ለሰብዓዊ መብት መጠበቅ ቅድሚያ እንዲሰጥ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብም ህገወጥነትን መቃወሙን አጠናክሮ በመቀጠል የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ እየተካሄደ ያለውን ሰላማዊ ትግል እንዲደግፍ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ዘላለማዊ ክብር ለኢትዮጵያ!!!
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ
ነሐሴ 27 ቀን 2005 ዓ.ም

አዲስ አባባ

UDJ

ከአህያ ጋር ብጣሪ በልታ ከፈረስ ጋር ገብስ ትበላለች

$
0
0

"ከአድባይነት እርግማን ይሰውረን!"

ታክሎ ተሾመ

የኃይማኖት መሪው ቡድሐ የሚሰጠን አንድ እንቆቅልሽ የሚከተለውን ይመስላል። አንድ ነጋዴ ሩቅ ሄዶ ሲመለስ፤ ቤቱ በሽፍቶች ተዘርፎና ተቃጥሎ ይደርሳል። ከቤቱ ከተረፈው ረመጥ - መካከል አንድ ተቃጥሎ የከሰለ የሰው ገላ ያያል። "ይሄ ትንሹ ልጄ መሆን አለበት" አለ። በዚህ ምክንያት ምርር ብሎ አለቀሰ። ደረቱን መታ። ፀጉሩንም ነጨ። ገላውን እንደገና የማቃጠል፤ የሐዘን ሥነ-ስርዓት እንዲካሄድም አደረገ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከመንግሥት የቤቶች ግንባታ ጀርባ ያለው ትክክለኛ ዓላማ ሲጋለጥ

$
0
0

ግርማ ሠይፉ ማሩ
ሰሞኑን ከፀረ-አሸባሪነት ሕግ በማስቀጠል የአዲስ አበባን ከተማ ነዋሪን በተለይ ሲያምስ ከርሞ አሁንም በማመስ ላይ ያለው የመኖሪያ ቤት ጉዳይ ነው። በአዲስ አባባ የመኖሪያ ቤት ችግር እንዳለ አሌ የሚባል አይደለም። ይህ ችግር እዚህ እንዲደርስ ደግሞ ዋናው ተዋናይ መንግሥት እንደሆነ መዘንጋት የለበትም። ምክንያቱም ለቤት መስሪያ የሚሆነውን ቦታ በቁጥጥሩ ስር አድርጎ ለዜጎች እንዳይደርስ በማድረጉ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

Viewing all 13695 articles
Browse latest View live