የአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ በታሰሩ ወጣት ፖለቲከኞች ዙሪያ ያቀረበው ዘገባ
የአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ በታሰሩ ወጣት ፖለቲከኞች ዙሪያ ያቀረበው ዘገባ
ኢትዮጵያ – ምእራባውያን – አንዳርጋቸው – የወደፊት እጣ – ለትግል መነሳት – Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
በአሸባሪው መንግስታዊ ዘራፊ እና አፋኝ ቡድን የታፈነው አቶ አንዳርጋቸው ጸጌ ወያኔ ለመፍታትም ሆነ ለመግደል ዝግጁ አይደለም ። ግደሉት አሊያም ስቀሉት ቢባሉ እንኳን በፍጹም አያደርጉትም። ምእራባውያኑ ከአፍ ወሬ ውጪ ምንም የሚተገብሩት ነገር የለም ፡ እስክንድር ነጋ በቂ ምሳሌ ሊሆን ይችላል ከሰብአዊ መብት ድርጅቶች ጀምሮ እስከ አሜሪካው የውጪ ጉዳይ አናት ኬሪ ድረስ ድምጻቸውን ቢያሰሙም ለይስሙላ እና ለብሄራዊ ጥቅማቸው እንዲሁም ነገ ሌላ መንግስት ቢተካ እንዲህ ብለው ነበር እንዲባልላቸው እና እዳ ማውረጃ ንግግራቸው ለትግሉ ምንም የሚያበረክተው አሊያም ለአንዳርጋቸው የሚፈይደው ነገር የለም ።
ለአንዳርጋቸው ይሁን በእስር ለሚማቅቁት ወገኖቻችን የሚፈይደው ዋናውና አንዱ ጉዳይ የኛ ጠንክረን መታገል እና አንድ እርምጃ መጓዝ ሲሆን የዛን ሰአት የኛን መጠናከር እና መታገል የተመለከቱ ም እራባውያን ምን እንርዳችሁ ከምን ደረሳችሁ ምናምን ማለታቸው እና መጠየቃቸው ግድ የሚልበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም ፡፤ አሁን የሚፈለገው የኛ መታገል እና መታገል ብቻ ነው። የነጮቹ የከንፈር ልብላቤ ከብሄራዊ ጥቅም ሚዛን ሂደት ምስረታ ላይ ስለተመረኮዘ ከንግግር ውጪ ምንም አይፈይድም:
ልብ ማድረግ ያለብን ከማ እከላዊ አፍሪካ እስከ አፍጋኒስታ ከሊብያ እስከ ኢራቅ በተለያዩ የአፍሪካ እና የመካከለኛው እንዲሁም የኢስያ ሃገራት ም እራባውያኑ የሚያካሂዱት የፕሮክሲ ጦርነት የተነሳ ሌላ ዙር ቀውስ በምስራቅ አፍሪካ እና ውጥረት እንዲከሰት ስለማይፈልጉ ከወያኔ ጋር እጅና ጓንት ሆነው ለመስራት አለመቦዘናቸው የሚያመለክተው እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሃገራት ላይ በአሁኑ ሰአት ሊፈጠር የሚችለውን አመጽ እና ችግር መቆጣጠር ይዞ የሚመጣውን ውጤት እርግጠኛ ሆነው ለማወቅ አለመቻላቸው ከወያኔ ጋር እንዲተሳሰሩ አድርጓቸዋል።ምንሊክሳልሳዊ
እንዲሁም ደቡብ ሶማሊያ ላይ ነዳጅ መኖሩን ስካን አድርገው ስላረጋገጡ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ25 አመት በኋላ እንግሊዝ ኤምባሲዋን ሞቃዲሾ የከፈተች ሲሆን ይህን ተከትሎ ከ100 በላይ የብሪታንያ ካምፓኒዎች ካልተረጋጋችው ሶማሊያ ፍቃድ እንደተሰጣቸው ለማረጋገጥ ተችሏል። ይህንን ከሶማሊያ ሊያገኙትን ብሄራዊ ጥቅም ሊያስጠብቅ የሚችለው አገር ቢኖር ወታደሮቹን ለሞት እየገበረ የሚተባበራቸው የወያኔው መንግስት ብቻ ስለሆነ ያላቸውን ሃይል ሁሉ በመጠቀም ሕዝብን በዲፕሎማሲያዊ ቋንቋ በመደለል የአምባገነኖች እድሜ እንዲረዝም ሚናቸውን ይጫወታሉ።
እንዲሁም ስለግንቦት ሰባትም ይሁን ታጥቀናል እንዋጋለን ስለሚሉ ድርጅቶች እንቅስቃሴ በቂ መረጃ ስለሌላቸው እንዲሁም እነሱ የማይደግፉት እና የማይቆጣጠሩት አመጽ ላይ ሪስክ/ሃላፊነት ስለማይወስዱ የሚያደርጉል አስታውጾ አነስተኛ ሲሆን እኛ ታግለን አንድደርምጃ ወደፊት እስካልሄድን ድረስ እና ትግላችንን አሳይደን የድጋፍ እና የቁጥጥር ሰንሰሎችን ከም እራባውያን ጋር እስካልፈጠርን ድረስ በመግለጫ እና ድህረገጽ ወሬ ጋጋታ ምንም የምናመጣው ነገር እንዳሌለ ለመናገር እወዳለሁ፡፤ የአንዳርጋቸውን ጉዳይ ግንቦት ሰባት በሎንዶን ፍርድ ቤቶች ቀርቦ የቻለውን ያህል መጋፈጡ የማይቀር ቢሆንም የሚወስደው ጊዜና ጉልበት ቀላል ስለማይሆን እንግሊዛውያኑ ጊዜ ይገዙበታል። ዋናው ቁም ነገሩ ግን ጠንክረን የዲፕሎማሲውን እና የሃገር ቤቱን ትግል ከያዝነው አንድ ነገር መፈንዳቱ አይቀርም ።
ብቸኛው እና ዋናው ጉዳይ ትግሉ/ጦርነቱ በመሃል እና በዳር አገር ከተፋፋመ ፣ ሕወሓት እና አመራሩ አደጋ ውስጥ መግባት ሲጀምሩ የዛን ወቅት ም እራባውያኑ በሌላው አለም እንደለመዱት ይመጡና አንዳርጋቸውን እንደ ጆከር ካርድ ለመጠቅም ይሞክራሉ። በቃ ወያኔ አንዳርጋቸውን እንዲፈታ እና የተኩስ አቁም ተደርጎ ድርድር እንዲጀመር ያደርጋሉ ከዚህ ውጭ ግን የሃይል ሚዛኑ በወያኔ እጅ ባለበት የመንግስትን ወንበር ተቃዋሚዎች ባላዩበት ሁኔታ ምእራባውያኑ የሚያሰሉት ከወያኔ ጋር ያላቸውን ቁርኝት ነው። ይህንን ለመበጠስ ደሞ የግዴታ የተኩስ ትግል መጀመር አለበት ። ወያኔም ቢሆን የትጥቅ ትግሉ በመሃል አገር እና በዳር አገር ሲስፋፋበት ጭንቀት ውስጥ ስለሚገባ ከአጣብቂኙ ለመውጣት ሲል ያለውን አማራጭ ለመጠቀም ይሞክራል። ወያኔ ደጋፊዎቹን እና ካድሬዎቹን ብእጥቅም ስለገዛቸው ጦርነት ከተስፋፋበት ያለውን ሃይል ሁሉ ወደ ዛው ስለሚያጋድለው ለካድሪዎቹ ጥቅሞች ጊዜ ስለማይኖረው አብዮታዊ መበላላት በፓርቲው ውስት ስለሚፈጠር እድሜውን ማቀጨጭ ከዛም መጣል ይቻላል። መታገል ካልቻልን ባሁኑ አካሄዳችን ወያኔን እንድማንጥለው ማወቅ አለብን።
አንዳርጋቸው የት እንዳለ ባልታወቀበት ሁኔታ ቶርቸሩ ባልቆመበት ሁኔታ ላይ 500 ሚሊዮን እነ ብሪታንያ እየሰጡ ባለበት ሁኔታ ወያኔ እና የየመን መንግስት የሚፈልጉትን ነገር እንዲያደርጉ ቀድመው ላይሰንስ አድርገዋቸውል ለማለት መገመት ብቻ ሳይሆን ያስደፍራል።አስር ጊዜ ወያኔዎችን የሚያጥላላ ነገር ከመጻፍ በየመንገዱ ሰልፍ ከመውታት በጋራ ተሰባስበን ሳንናናቅ እና ከኛ በላይ አዋቂ የለም ብለን ሳናስብ አንዱ ለ አንዱ ዝቅ ብሎ የወያኔን ስልጣን አደጋ ውስጥ የሚከት ከባባድ እንቅስቃሴ ማድረግ ከቻልን በትግላችን ስኬት ምእራብያውያኑን ማሳመን እንደምንችል ማወቅ አለብን። ህዝባችንንም ነጻ ማውጣት እንደምንችል መረዳት ግድ ይላል።#ምንሊክሳልሳዊ
መንግስታዊ ወንጀል በነጻነት የሚራመድባት ሃገር ኢትዮጵያ : ከመሃል አዲስ አበባ የተቃዋሚ አመራሮች መያዝ የሚያሳስብ ጉዳይ ነው። – Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
በዚህ ወር ብቻ እጅግ ከባድ የሆኑ ለጆሮ የሚቅፉ እና ለሰው ልጆች የሚያሰቅቁ የሰብአዊ መብት ገፈፋዎች እና የዜጎች ወደ እስር ቤት መወርወር የበለከተበት ከሃገር ቤትም አልፎ እስከ ጎረቤት አገር ድረስ ተዘልቆ በጉቦ የዜጎች የመዘዋወር መብት በስውር እጆች የተደፈሩበት እሱንም ተከትሎ የተቃዋሚ ድርጅቶች አመራሮች ከየመንገዱ እና ከቤታቸው እየተያዙ ወደ እስር የተወረወሩበት ሁኒታ እያየን እየሰማን ነው።
የግንቦት ሰባት አመራር የሆነው አንዳርጋቸው ጽጌን ከመንገድ ያውም ከሰው አገር በጉቦ፡ተልፈው አምጥተወት ለአስራ አምስት ቀን የሚጠጋ በደህንነት ድብቅ የስቃይ ማእበል ሲንጡት ከርመው ጫና ቢበዛባቸው አክመው ባያስተካክሉትም አቅረቡት ። ወገናችን አንዳርጋቸው የተመለከትንበት በድብቅ የተቀረጸው ቪዲዮ ከኦዲዮው ጋር በፍጹም የማይሄድ ከመሆኑም በላይ ልብ ብሎ ለተመለከተው የአንዳርጋቸውን የአፍ እንቅስቃሴ እንዳናየው ከታች በጹሁፍ መልክ በማስቀመጥ የተደጋገመ እና ለማደናበር ሞክረዋል።
እንደ አንዳርጋቸው እምነት እን ዶክተር ብርሃኑ ነጋ እንደነገረን ከሆነ የሁለቱም አባባል አንድ ነገር ላይ ያርፋል ፡ ” አንዳርጋቸውን የያዙት ስራውን ጨርሶ ልተተኪዎች አስረክቦ እረፍት ላይ በሆነ ሰአት ነው፤” የፖለቲካ ቋንቛ ለሚገባው ሰው አንዳርጋቸው የተናገረው ነገር ቢኖር ለሃገሩ ድርሽውን እንደተወጣ እና እረፍት ላይ በሆነበት ወቅት እንደተያዘ ነው።
አንዳርጋቸውን በሚዲያቸው ከማቅረባቸው በፊት የወያኔ የዲሞክራሲ መገለጫ የሆነው የመቀሌውን የአረና አመራር ጨምሮ ዳንኤል ፡ የሺዋስ እና ህብታሙ የተቃዋሚ አመራሮች ተይዘው ቤታቸው እስከመበርበር ደርሶ ወደ ሰቆቃው ማእከል ማእከላዊ ተወርውረዋል። የተቃዋም አመራሮችን ከግንቦት ሰባት እና ከአንዳርጋቸው ጋር አቆራኝቶ ለመወንጀል እየሮጠ ያለው ወያኔ ጉልበቱን እና የሃገር አንጡረ ሃብትን በመጠቀም ታሪክ ይቅር የማይለው ወንጀል በዜጎች ላይ እየፈጸመ ይገኛል፡
በተቃዋሚዎች ዘንድ አንድ እርምጃ የትግል እርከን እንደተጀመረ እየተነገረ ባለበት በዚህ ወቅት በጋራ በመሆን ይህንን የትግል ጥሪ በመተግበር ለሕዝቦች ነጻነት ራሳችንን መስእዋት በማድረግ ብአሸናፊነት ወያኔን ደምሠን በመቃብሩ ላይ የዲሞክራሲን እና የነጻነት ችቦ መለኮስ እንዳለብን ለመናገር እወዳለሁ #ምንሊክሳልሳዊ
አብርሀ ደስታ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ ፍርድ ቤት ቀረበ – ፍኖተ ነጻነት
ካሳለፍነው ማክሰኞ ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በመንግስት ታጣቂዎች በቁጥጥር ስር ውለው በማዕከላዊ በእስር ላይ የሚገኙት ወጣቱ ፖለቲከኛ ሀብታሙ አያሌው የአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ፣ ወጣቱ ፖለቲከኛ ዳንኤል ሺበሺ የአንድነት ፓርቲ ድርጅት ጉዳይ ም/ሀላፊ ወጣቱ መምህርና ፖለቲከኛ አብርሃ ደስታ የአረና ፓርቲ አመራር በትላንትው ዕለት ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ቢጠበቅም ከምሽቱ 12፡16 ላይ የአረና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አብርሃ ደስታ ብቻውን በ3 ፌደራል ፖሊሶች ታጅቦ ፍርድ ቤት ቀርቧል፡፡ ማንም ወደ ፍርድ ቤቱ እንዳይገባ በፀጥታ ሀይሎችና ሲቪል በለበሱ የደህንነት ሀይሎች በመከልከሉ ምክንያት ስለቀረበበት ክስ ለማወቅ ያደረግነው ጥረት ሊሳካልን አልቻለም፡፡ በወጣቱ ፖለቲከኛ አብርሃ ደስታ ፊት ላይ ይታይ የነበረው ጉስቁልና ከፍተኛ የሀይል እርምጃዎች ሳይወሰድበት እንዳልቀረ አመላካች ነበር፡፡ ይህንን ዜና እስካጠናቀርንበት ጊዜ ድረስ የአንድነትና ሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ፍርድ ቤት አልቀረቡም፡፡
ወያኔ አቶ አንዳርጋቸውን እንዴት ማፈን ቻለ? ኪሩቤል በቀለ
ወያኔ አቶ አንዳርጋቸውን እንዴት ማፈን ቻለ? ለዚህ ጥያቄ መልስ መስጠት ለግንቦት 7 ብቻ ሳይሆን ለሁላችንም የሞትና የሽረት ጥያቄ ነው:: በቂ ማስረጃ እስክሚሰበሰብ ድረስ አራት አቅጣቻዎችን መመርመር ያስፈልጋል::
1) ለሻቢያ ሁሉ ነገር ከራስ በላይ ነፋስ ነው:: ራሱ ሻቢያ በተዘዋዋሪ ለወያኔ የአቶ አንዳርጋቸውን የበረራ ሰዓታቸውን አሳልፎ ሊሰጥ ይችላል::ይህ እንግዲህ በኤርትራ ውስጥ የሚገኙ የግንቦት 7 መሪዎች ሁኔታውን በደንብ ሰለሚያውቁ ይህ ግምት ሊሆን ወይም ላይሆን እንደሚችል መጠቆም ይችላሉ:: ለምሳሌ ሻቢያም ሆነ በሻቢያ የሚታዘዘው ደሚት ስለ ግንቦት 7 ደስ ያላላቸው ነገር እንዳለ የታዘቡት ነገር አለ ወይ? ሌላም ሌላም የተፈጠሩ ክስተቶች ካሉ መገምገም ይኖርባቸዋል::
2) በሻቢያ የደህንነት መዋቅር ውስጥ ሰርገው የገቡ የወያኔ ሰላዮች አቶ አንዳርጋቸውን ተከታትለው የበረራ ሰዓቱንና ቦታውን አግኝተው ለወያኔ ልከውት እንድሆነም መጣራት አለበት:: የአቶ አንዳርጋቸውን የበረራ ቀንና ሰዓት የሚያውቁት እነማን ነበሩም ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል:: እንደተባለው አቶ አንዳርጋቸው የበረራውን አቅጣጫ በየመን በክል ለማድረግ መወሰኑን በሰዓቱ እነማን ነው ያወቁት? መቼስ ነው ያወቁት?
3) በግንቦት 7 አመራር ውስጥ ያለ ወይም ለአመራሩ በጣም ቅርበት ያለው ግን አንዳርጋቸውን የሚያገኝ ወይም የአንዳርጋቸው የልብ ወዳጅ የሆነ ግለሰብ የበረራ መረጃውን ለወያኔ በክፍተኛ ገንዘብ አሳልፎ ሰጥቶ እንደሆነ መጣራት አለበት::
4) የመጨረሻው አማራጭ ከግንቦት 7ና ከሻቢያ ቁጥጥር ውጭ በየመንና በወያኔ መካከል ለረጅም ጊዜ የተቀነባበረ ሴራ ሊሆን ይችላል:: የየመን መንግሥትና ወያኔ የሰንኣ አየር መንገድ ሃላፊዎች ውስጥ አንድ ለደህነንት እንዲሰራ የተመደበ ሰው የአንዳርጋቸውን ስም ከተሳፋሪዎች ስም ዝርዝር ውስጥ በየጊዜው እየቃኝ መጨረሻ ላይ አግኝቶ ለየመን ደህነነት ከዛም በኋላ ለወያኔ አሳልፎ አንዳርጋቸው ሊጠለፍ ችሎ ሊሆን ይችላል:: ይህ ሁኔታ ሊሳካ የሚችለው የአንዳርጋቸው ፓስፖርት በእውነተኛ ስሙ የተሰጠው ክሆነ ነው::
ወይም ካልሆነ ከላይ ከተራ ቁጥር አንድ እስክ ሶስት ድረስ እንደተጠቀሰው የአንዳርጋቸውን የፓስፖርት ስም የሚያውቅ የግንቦት 7 አመራር አባል ወይም ለግንቦት 7 በጣም የቀረበ የአንዳርጋቸው የልብ ወዳጅ ወይም ሻቢያ ወይም በሻቢያ ደህነነት ውስጥ ሰርጎ የገባ የወያኔ ሰላይ የአንዳርጋቸውን የበረራ መረጃ ፓስቦርቱ ላይ ካለው ስሙ ጋር ለወያኔ አቀብሎ ከየመን ጋር በመደራደር የተደረገ አፈና ነው::
የአቶ አንዳርጋቸው መታፈን ከአራቱ ምክንያቶች ውጭ ሊሆን አይችልም የሚል ግምት አለ።
Early Edition –ጁላይ 11, 2014
ኢህአዴግ በምርጫ ዋዜማ የጀመረው እስር በአምባገነንነት መስመሩ ለመቀጠል የቆረጠ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው!!! – ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ እና ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
ኢህአዴግ በምርጫ ዋዜማ የጀመረው እስር በአምባገነንነት መስመሩ ለመቀጠል የቆረጠ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው!!!
በፖለቲካ አመለካከታቸው እና እምነታቸው የታሰሩ ዜጎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ በድጋሚ እንጠይቃለን!!
ሕወሓት/ኢህአዴግ ለአለፉት 23 ዓመታት ወደር የሌለው የዴሞክራሲያዊ መብት ገፈፋና የሰብአዊ መብት ረገጣ በዜጎች ላይ ሲፈጽም መቆየቱና አሁንም በዚያው የአፈናና እስር መንገድ መቀጠሉን ዓለም የሚያውቀው እውነታ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በተለይም በሚቀጥለው ዓመት የሚካሔደውን ሀገራቀፍ ምርጫ ተከትሎና ሁለቱ ፓርቲዎች የጀመሩትን የውህድት ጉዞ ለማደናቀፍ ባለመ መልኩ የሰብአዊ መብት ረገጣና ድፍጠጣ እንዲሁም ማሰሩና ማዋከቡ በእጅጉ ተባብሶ ወደ መንግሥታዊ ሕገ ወጥነት ጥቃት ተቀይሯል፡፡ ዜጎች መንግሥት እንዳሰማራቸው በሚጠረጠሩ የደህንነት ኃይሎች ስርዓቱን በሃይል ለማስቀጠል በመቁረጥ ዜጎች ኃላፊነት በጎደለው መልኩ ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ በጅምላ መታሰራቸውን፣ መደብደባቸውንና በስውር እስር ቤቶች ተወርውረው ደብዛቸው እንዲጠፋ መደረጉ ቀጥሏል፡፡ እንደዚህ አይነቱ ሕገ ወጥነት ደግሞ ምርጫ ሲቃረብና የፖለቲካ ፓርቲዎች መሰባሰብ ብሎም መዋሃድ ሲገለፅ ተጠናክሮ የሚቀጥል እንደሆነ ከዚህ በፊት ከነበሩ ተሞክሮዎች ለመረዳት ይቻላል፡፡
ሕወሓት/ኢህአዴግ ለባለፉት 23 ዓመታት ሲያደርገው እንደነበረው ሁሉ ምርጫ ሲደርስ አባሎቻችንን ከመደብደብና ከማሳደድ በተጨማሪም በምርጫው ዋዜማ በተለመደውና አሰልቺ ፍረጃው ተደግፎ አመራሮቻችንን ማሰር ጀምሯል፡፡ እስሩም በፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ላይ ያነጣጠረ ሲሆን ሰሞኑን ብቻ አንድነት የስራ አስፈፃሚ አባልና የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የሆኑትን አቶ ሀብታሙ አያሌውን፤ የምክር ቤት አባልና የድርጅት ጉዳይ ምክትል ሃላፊ አቶ ዳንኤል ሺበሺን፤ የአረና የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የሆነውን አቶ አብርሃ ደስታን እና የሰማያዊ ፓርቲ ም/ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ የሆነውን አቶ የሽዋስ አሰፋን አስሯል፡፡ በተጨማሪም ሰብዓዊ መብታቸውን በመግፈፍ ከ48 ሰዓት በላይ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀርተዋል፡፡ በጠበቃም ሆነ በወዳጅ ዘመዶቻቸው አይጎበኙም፡፡ በአካላቸውም ሆነ በስነ ልቦናቸው የደረሰባቸውን ጉዳት ማረጋገጥ አልተቻለም፡፡ ስለዚህ ሁለቱ ፓርቲዎች እንደዚህ አይነቱን ሃላፊነት የማይሰማውና የጭካኔ ተግባር ማውገዝ ብቻ ሳይሆን እስከመጨረሻው ፍፁም ሠላማዊ በሆነ መንገድ አምርረን የምንታገለው መሆኑን እናረጋግጣለን፡፡
የሰሞኑ እስር እንደተለመደው የተቀነባበረ የስርዓቱ ድራማ ከመሆኑም በተጨማሪ የ2007ን ሀገራቀፍ ምርጫ በተለመደው ማሸማቀቅና ማወናበድ ለመውሰድ የተጀመረ የመጀመሪያ ርምጃ ነው ብለንም እናምናለን፡፡ የተቀነባበረ ድራማም በሚቆጣጠራቸው ስማቸው የህዝብ ተግባራቸው ግን የኢህአዴግ የፓርቲ መገልገያ በሆኑ ሚዲያዎች ማቅረቡን እንደሚቀጥልም እናውቃለን፡፡ ይህ ሁሉ ግፍና ድራማ የሚከናወነው ከአፍ ባለፈ መተግበር ያልቻለውን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለማስመሰያነት ለመጠቀምና የቀጣዩን ዓመት ምርጫ በለመደው ሁኔታ ከቻለ አስሮና አደናግሮ ካልተቻለ ጉልበቱን ተጠቅሞ ለመጠቅለል ነው፡፡
አንድነትና መኢአድ አባላትንና አመራሮቻችንን በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በማሰቃየትና በማሸማቀቅ፣ በመደብደብ የአካል ማጉደል ጉዳት በማድረስ የሚያደርገውን አስነዋሪ ተግባር እያወገዘን በግፍ የተታሰሩት አቶ ሀብታሙ አያሌው፤ አቶ ዳንኤል ሺበሺ፤ አቶ አብርሃ ደስታ እና አቶ የሺዋስ አሰፋ እንዲሁም በስርዓቱ በፖለቲካ አመለካከታቸውና እምነታቸው ብቻ ለእስር የተዳረጉ ፖለቲከኞች፤ ጋዜጠኞችና ብሎገሮች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ እናሳስባለን፡፡
በተጨማሪም በተቃውሞ ጎራ የተሰለፉ ፓርቲዎችም ይህን ህገ ወጥ እስር በማውገዝ እንዲሁም ኢ-ፍትሀዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚደረገውን ሩጫ በመቃወም እጅ ለእጅ ተያይዘን እንድንቆም እየጠየቅን ይህንን ህገ-ወጥነት በህዝባዊና ሠላማዊ ንቅናቄ፣ በነፃና ፍትሓዊ ምርጫ መለወጥ እንዲቻል በጋራ እንድንሰራ ሀገራዊና ወቅታዊ ጥሪ እናቀርባለባለን፡፡ የሲቪክ ተቀቋማት፤ ነፃው ሚዲያና የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ድርጅቶችም በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እየተፈፀመ ያለውን መንግስታዊ ግፍና በደል በዓለማቀፍ ደረጃ በማጋለጥ ግዴታችሁን እንድትወጡ እንጠይቃለን፡፡ ገዢው ፓርቲ የሚከተለው የጉልበት ርምጃ ሀገሪቱን የሚያጠፋና ለትውልድ ጥላቻ የሚያወርስ በመሆኑ ከዚህ ድርጊቱ እንዲቆጠብ እንጠይቃለን፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብም ስለሰብዓዊ መብት መከበርና ዴሞክራሲ መረጋገጥ እየተደረገ ያለውን ትግል በመደገፍ የአምባገነኖችን ውድቀት እንዲያፋጥን ሀገር አቀፍ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
ድል ለሠፊው ህዝብ!!!
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት)
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)
ሐምሌ 3 ቀን 2006 ዓ.ም
አዲስ አበባ
ረመዳንን የሚጾሙ ወጣቶች
የአፍሪቃ መሪዎች የተስማሙበት በወንጀል የማያስጠይቅ መብት
የአፋር ተወላጆች መገናኛ መረብ ማሳሰቢያ
የአሜሪካ ስለላና የጀርመን ርምጃ
የአውሮጳው ሕብረትና ደቡብ ሱዳን
UTC 16:00 የዓለም ዜና 11.07.2014
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና –ጁላይ 11, 2014
በመጭው ምርጫ ከባድ ፈተና ሊገጥመን ስለሚችል ክወዲሁ መዘጋጀት አለብን ሲል ወያኔ አስታወቀ። – Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
” ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ፈታተን መግጠም አለብን። ” የወያኔ ባለስልጣናት
” አላርፍ ካሉ ፍቃዳቸውን ሰበብ ፈጥረን እንነጥቃቸዋለን። ” የምርጫ ቦርድ ሃላፊ
በኢሕአዴግ ባለስልጣናት እና በምርጫ ቦርድ መካከል መጭውን ምርጫ በተመለከተ ሰፋ ያለ ዝግ ስብስባ ተካሂዶ ነበር ሲል ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት አከባቢ የተገኘ መረጃ ጠቁሟል። በአይቶ ጸጋዬ በርሄ የተንታለለ የመሃይማን ቢሮ ውስጥ የምርጫ ቦርድ ታዛዥ ሃላፊዎች እስከምሽት ድረስ ሲያደነቁሩ እና ሲደናቆሩ ያመሹት የወያኔ ባለስልጣናት በመጪው ምርጫ ሕዝቡ ፊቱ እንደሚያዞርባቸው ሳይሸሽጉ ለምርጫ ቦርድ ባለስልጣናት ተናግረዋል።
የወያኔ ባለስልጣናት ወደ ምርጫ ቦርድ አቤቱታ ይዞ የሚመጣ ፓርቲ ካለ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ሪፖርት ለኢሕአዴግ ቢሮ እንዲደረግ እና ፓርቲዎቹ የሚሰጣቸውን መልስ በተለያዩ ዘዴዎች በማዘግየት እንዲሰላቹ እንዲደረግ እንዲሁም እያንዳንዱ የፖለቲካ ፓርቲ እንቅስቃሴ እየገመግገ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ መድረክ እና ኢዴፓ ላይ ነገሮች እንዳይጠብቁ ሆኖም ግን በመድረክ የተሸሸገው ኢፌኮ የኦነግ ተቀጽላ ስለሆነ በኦሮሚያ ክልል ባሉ የምርጫ ቦርድ ቅርንጫፎች በኩል ጥቃት መሰንዘር የሚሉ መመሪያዎች ይገኝባቸዋል።
የምርጫ ቦርድ ሃላፊዎች ሊቀመንብሩን ጨምሮ የተሰታቸውን መመሪያ የዋጡት ሲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎቹ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ በተመለከተ እንደከዚህ ቀደሙ ከኢሕ አዴግ የሚተላለፍላቸውን መመሪያ እንደሚተገብሩ እና ፓርቲዎቹ አላርፍ ብለው ከ እኩይ ተግባር ይማይቆጠቡ እና መንግስትን መዝለፋቸውን የሚቀጥሉ ከሆነ ሰበብ በመፍትር ምርጫ ቦርድ ፈቃዳቸውን እንደሚነጥቃቸው እና ከመንግስት የመጣውን መመሪያ ተግባራዊ እንደሚያደርጉ እንዲሁም ፓርቲዎች የሚያቀርቡትን አቤቱታ ለኢሕ አዴግ ቢሮ ሪፖርት እንደሚይደርጉ ቃል ገብተዋል።
ወያኔ በመጭው ምርጫ ስጋት ስለገባው ጠንካራ ፖለቲክኞችን ከማሰር ጀምሮ እስከ ፓርቲዎች ፈቅድ ደከመንጠቅ እንደሚደርስ ይገመታል ፡ ለዚህም ተጠቂ የሚሆኑ አረና ኦፌኮ ሰማያዊ እና አንድነት ሲሆኑ ከመድረክ በወያኔ ደምወዝ የሚከፈላቸው በየነ ጴጥሮስ እና ቡድናቸው እንዲሁም ኢዴፓ እንደማይነኩ ሲታወቅ ኢሕ አዴግ ለምርጫ ቦርድ ሊቀመንበር ስም ዝርዝራቸውን በምስጢር የሚሰጣቸው ሰዎች ምርጫውን እንዳለፉ እንደሚደረግ ታውቋል። በምርጫ ቦርድ አከባቢ ያለውን ሁኔታ በተመለከት ዝርዝር መረጃዎች ስለሚኖሩ ይከታተሉ።
#ምንሊክሳልሳዊ
አምነስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ የሚፈጸመው እስር እንዳሳሰበው ገለጸ
ሐምሌ ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ ተጠናክሮ የቀጠለው እስር በአገሪቱ ውስጥ ምንም አይነት ተቃውሞ እንዳይኖር ያደረገ ነው ብሎአል።
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ያሉበት ሁኔታ አለመታወቁንና ለከፍተኛ ስቃይ ሊዳረጉ እንደሚችሉ መግለጹንና አለማቀፉ ማህበረሰብ አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ ማሳሰቡን ያስታወሰው አምነስቲ፣ ከዚሁ ጋር በተያያዘ አቶ ደንኤል ሽበሺ፣ አብርሃ ደስታ፣ የሽዋስ አሰፋና ሀብታሙ አያሌው የተባሉ ታዋቂ ፖለቲከኖች መታሰራቸው በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም አይነት ተቃውሞ እንዳይኖር ለማድረግ የታሰበ መሆኑን ገልጿል።
የፖለቲካ ድርጅት መሪዎቹ በማእከላዊ ስቃይ ሊፈጸምባቸው እንደሚችልም አስጠንቅቋል።
ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞአቸውን አሰሙ
ሐምሌ ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በረመዳን ጾም ተጠናክሮ የቀጠለው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ፣ ዛሬም በበኒ መስጂድ እጅግ ከፍተኛ ህዝብ በተገኘበት ተካሂዷል። ኢትዮጵያውያኑ ሙስሊሞች ” የእምነት ነጻነታችን ይከበር፣ ለከፈልነው መስዋትነት ተመጣጣኝ ውጤት እናመጣለን” የሚሉ መፈክሮችን ጽፈው አሳይተዋል።
ከሁለት አመት በላይ የዘለቀው የሙስሊሙ ተቃውሞ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መሪዎቹ እየገለጹ ነው።
የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌና የሌሎችም ፖለቲከኞች መታሰር የፈጠረው ህዝባዊ ቁጣ እንደቀጠለ ነው
ሐምሌ ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የየመን መንግስት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ለመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ህገወጥ በሆነ መልኩ አሳልፈው ከሰጡዋቸው በሁዋላ ኢትዮጵያውያን አሁንም ቁጣቸውን እየገለጹ ሲሆን፣ አንዳንድ ወገኖች ” የአቶ አንዳርጋቸው መታሰር ልብን የሚሰብር ቢሆንም፣ ወሳኙ ነገር ማዘን ሳይሆን ለለውጥ ቆርጦ በመነሳት መታገል ነው” ብለዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የየመን መንግስት የወሰደውን እርምጃ እንዲሁም የኢህአዴግ መንግስት አቶ አንዳርጋቸውን አስሮ ማሰቃየቱን በመቃወም የሚያደርጉትን ተቃውሞ እንደቀጠሉ ነው። በአሁኑ ወቅት የጸጥታ ችግር በሚታይባት እስራኤል የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በቴላቪቭ ባደረጉት ተቃውሞ በአቶ አንዳርጋቸው ላይ የተፈጸመውን ህገወጥ እርምጃ አውግዘዋል። ኢትዮጵያውያኑ እንግሊዝ በአቶ አንዳርጋቸው ጉዳይ ጣልቃ እንድትገባና የሚለቀቅበትን መንገድ እንድትፈልግም ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ መንግስት በሽብርተኝነት ሰበብ ያሰራቸውን በአገር ውስጥ በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉትን ፖለቲከኞች እንዲፈታ አንድነትና መኢአድ በጋራ እንዲሁም ሰማያዊ ፓርቲ ጠይቀዋል።አንድነት እና መኢአድ ” ኢህአዴግ በምርጫ ዋዜማ የጀመረው እስር በአምባገነንነት መስመሩ ለመቀጠል የቆረጠ መሆኑን የሚያረጋገጥ ነው” በሚል ርእስ ባወጣው መግለጫ ፣ ” የሰሞኑ እስር እንደተለመደው የተቀነባበረ የስርዓቱ ድራማ ከመሆኑም በተጨማሪየ2007ንሀገራቀፍምርጫበተለመደውማሸማቀቅናማወናበድለመውሰድየተጀመረየመጀመሪያርምጃነውብለንምእናምናለን” ብሎአል።
ፓርቲዎቹ ” የአንድነትና መኢአድ አባላትንና አመራሮቻችንን በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በማሰቃየትና በማሸማቀቅ በመደብደብ የአካል ማጉደል ጉዳት በማድረስ የሚያደርገውን አስነዋሪ ተግባር አውግዘው፣ በግፍ የተታሰሩት አቶ ሀብታሙ አያሌው ፤ አቶ ዳንኤል ሺበሺ ፤ አቶ አብርሃ ደስታ እና አቶ የሺዋስ አሰፋ እንዲሁም በስርዓቱ በፖለቲካ አመለካከታቸውና እምነታቸው ብቻ ለእስር የተዳረጉ ፖለቲከኞች ፤ ጋዜጠኞችና ብሎገሮች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ ” አሳስበዋል። ፓርቲዎቹ “በተቃውሞጎራየተሰለፉፓርቲዎችይህንህገወጥእስርበማውገዝእንዲሁምኢ-ፍትሀዊምርጫለማካሄድየሚደረገውንሩጫበመቃወምእጅለእጅተያይዘውእንዲቆሙ”ጠይቀው፣ ይህንንህገ-ወጥነት በህዝባዊና ሠላማዊ ንቅናቄ ፣ በነፃና ፍትሓዊ ምርጫ መለወጥ እንዲቻል በጋራ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት በበኩላቸው ገዢው ፓርቲ ስለምርጫ ሳይሆን አገርን ለማጥፋት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የት ነው ያለችው ሲሉ የጠየቁት ኢ/ር ይልቃል፣ ያመጸው ሁሉ ሽብረተኛ ሆኗል፣ በሰላማዊ ትግል የሚታገለውም፣ ጋዜጠኛውም ሽብርተኛ ሆኗል ያሉት ኢ/ር ይልቃል፣ አገሩን ማስተዳደሩ ከአቅማቸው በላይ በመሆኑ፣ የትግሉ እንቅስቃሴ ከፍ ወዳለ ደረጃ መሸጋጋሩን ገልጸዋል።
ትግሉ የጥቂቶች ሳይሆን የሚሊዮኖች ሆኗል። – የሰሜን አሜሪካ የአንድነት ድጋፍ ማህበር
በአገር ዉስጥም ሆነ ከአገር ዉጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ጉጉትና ምኞት ፣ ልጆችዋ ከርሷ የሚሰደዱባት ሳይሆን የተሰደዱት ተመልሰው ለሌሎች መጠጊያ የምትሆን፣ የሕግ የበላይነት የሰፈነባት፣ የሰብአዊ መብቶች የሚከበሩባት፣ ዘር፣ ኃይማኖት፣ ጾታና መደብ ሳይባል ለሁሉም እኩል የሆነች፣ አንዲት ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ማየት ነው። ነገር ግን፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ በአገዛዙ እያየን ያለነው፣ ልብን የሚያደማና የሚያቆስል ነው። በስድሳዎቹ ከነበረው የደርግ ስርዓት በባሰ፣ አገዛዙ ሕዝባችን ላይ የግፍ ቀንበር ጭኖ ፣ የጸረ-ሽብርተኝነት ሕግ በሚል ሰበብ ሰላማዊ ዜጎችን እያሸበረ ነው።
የአንድነት ፓርቲ፣ የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ በሚል መርህ፣ በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች፣ ሕዝቡ ለመብቱና ለነጻነቱ እንዲቆም በመቀስቀስ፣ በዞን እና በወረዳ ደረጃ ድርጅታዊ ሥራ በመስራት፣ በርካታ ሰላማዊ ሰልፎችን እና ሕዝባዊ ስብሰባዎችን እያደረገ እንዳለ ይታወቃል። በቅርቡም ከመኢአድ ጋር የቅድመ ዉህደት ስምምነትን በመፈረም የዴሞክራቲክ ካምፑን በአንድ ላይ ለማሰባሰብ ይቻል ዘንድ፣ ትልቅ ሥራ ተሰርቷል። እነዚህ አገረ ሰፊ እንቅስቃሴዎች፣ አገዛዙን አስደግጠውታል ፣ አሸብረውታልም። ሥር እየሰደደ በመጣዉ ሰላማዊ እንቅስቃሴ፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ድምጹን እያሰማ የመጣዉን የሕዝብ ጥያቄ፣ በአክብሮት ከመመለስ ይልቅ፣ አገዛዙ ከሕዝብ ጋር መላተምን መርጧል። በሕዝብ ዘንድ ከበሬታና ተወዳጅኘት ያላቸውን፣ በሰላማዊነታቸውና በአገር ወዳድነታቸው የሚታወቁትን ወጣት የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችን፣ ወጣት ጋዜጠኞችን እና ብሎገሮች፣ የዲሞክራሲ አክቲቪስቶችን በማሰርና በማስፈራራት ፣ ለነጻነት የሚደረገዉን እንቅስቅሴ ለመግታት ብሎም የሕዝቡን ድምጽ ለማፈን ደፋ ቀና እያለ ነው።
በቅርቡ የአንድነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ፣ የሚሊዮኖች ድምጽ ግብረ ኃይል፣ የመኢአድና አንድነት የውህደት ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሃብታሙ አያሌው፣ የአንድነት የድርጅት ጉዳይ ም/ሰብሳቢ አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ የሰማያዊ ፓርቲ የምክር ቤት ም/ሰብሳቢ አቶ የሺዋስ አሰፋ ፣ የአረና ፓርቲ አመራር አባልና ታዋቂ ብሎገር አቶ አብርሃ ደስታ እና ወገኖችን ህገ ወጥ በሆነ መንገድ አፍኖ እስርቤት ጥሎ ማሰቃየቱን አገዛዙ በሰፊው መያያዙ በጣም አሳዝኖናል። አስቆጥቶናልም። የተቀናጀ ህገወጥ ድርጊቶችን የምንኮንነዉና የምናወግዘው ሲሆን፣ አገዛዙም በሕዝቡ ላይ ጦርነት ማወጁን በገሃድ የሚያመላክት እንደሆነ ለማየት ችለናል።
በአሁኑ ጊዜ የሕዝቡ ስነልቦና ተቀይሯል። ኢትዮጵያዉያን ግፍን ለመሸከም የሚችሉበት ትከሻ የላቸውም። ጥቂት ወጣት የሰላማዊ የፖለቲካ መሪዎችን በማሰር፣ ሕዝቡን አስፈራርቶና መብቱን ረግጦ የመግዛት ዘመን አልፏል። ትግሉ የጥቂቶች ሳይሆን የሚሊዮኖች ሆኗል። በአገር ውስጥና ከአገር ዉጭ ሕዝባዊና ሰላማዊ የእምቢተኝነት ዘመቻው ይጧጧፋል። አገዛዙ በያዘው ብረትና በፈረንጆች ድጋፍ ይመካሉ። እኛ ግን በዉስጣችን ባለው ኢትዮጵያዊ ወኔ፣ በገዛ ክንዳችን እና በፈጣሪ ረድኤት እንመካለን። አገዛዙ ጥላቻን እና ጭካኔን፣ ዘረኝነትን እና መከፋፈልን ይሰብካል። እኛ ግን ፍቅርን እና መቻቻልን፣ አንድነትን እና ኢትዮጵያዊነትን እንሰብካለን።
በርግጥ የታሰሩ ወጣት የፖለቲካ መሪዎች ወደ ወህኒ መዉረድ ሁላችንንም ያሳዘነና ያስቆጣ ቢሆንም ታሳሪዎቹ ግን ፣ እንደ ክብር ነው የሚያዩት። የነርሱን መፈታት እና ለነርሱም አጋርነታችንን ማሳየት ከፈለግን፣ ማድረግ የሚኖርብን ፣ ከዝምታ ወጥተን፣ የፍርሃትን ካባ አዉልቀን፣ ከሚሊዮኖች አንዱ መሆን ነው። ቆመን፣ ተዋርደን፣ ፈርተን እና ተሸማቀን ከመኖር፣ የሕሊና ነጻነት አግኝተን በአካል መታሰር ይሻለናልና።
በአገር ቤት ያሉ የፖለቲካ መሪዎች ያላቸውን ቁርጠኝነት በዚህ አጋጣሚ እያደነቅን፣ ከነርሱ ጋር እጅ ለእጅ በመያያዝ ከመቼዉም ጊዜ በላይ የሰላም ትግሉን እንደምንደግፍ ለማረጋገጥ እንወዳለን። ሕወሃት/ኢሕአዴግ ከሽብር ድርጊቶቹ በአስቸኳይ ተቆጥቦ፣ አራቱ ወጣቶችን ጨምሮ የታሰሩ የሕሊና እስረኞችን በሙሉ በአስቸኳይ እንዲፈታ፣ የሕዝብን ጥያቄ ለራሱ ሲል እንዲያከብር እናስገነዝባለን። አገር በዱላና በጡንቻ አትገነባም። አገር የምትገነባው በፍቅር፣በመቻቻልና በመግባባት ነው። የአገዛዙ መሪዎች ልቦናቸውን ለፍቅር ያስገዙ እንላለን። እምቢ ካሉ፣ ካከረሩ ግን ታሪክ እንደሚያስተምረው አወዳደቃቸው እጅግ ታላቅ እና አስከፊ እንደሚሆን ልናስጠነቅቃቸው እንወዳለን።
ኢትዮጵያዉያን ከተባበርን፣ ሁላችንም የድርሻችንን ለማበርከት ከተነሳን፣ ከሚሊዮኖች አንዱ ከሆንን፣ አገዛዙ ፈለገም አልፈለገም የታሰሩ ወገኖቻችን ይፈታሉ። የተሰደዱ ወደ አገራቸው ይመለሳሉ። የአገራችንን ትንሳኤ እናውጃለን።
የሰላም ትግሉ ተቀናጅቶና ተጠናክሮ ይቀጥላል!!!
‹‹ቀዩ መስመር›› የቱ ጋር ነው?
ጽዮን ግርማ
ኢትዮጵያ በፓርቲ ላይ የተመሰረተ ፖለቲካ ባህል ውስጥ የገባችው የ1960ዎቹን ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ተከትሎ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት የተለያዩ ርዮተ ዓለሞች ተፋጭተው ዴሞክራሲያዊ ሥርዐት ይመሰረትባታል በሚል ተስፋ ቢጣልም የድርጅቶቹ የኋላ ታሪክ እንደሚያስረዳው ለሀገርና ለሕዝብ የሚጠቅም ለውጥ ከማምጣት ይልቅ እርስ በእርስ የመጨራረስ ባህል እንደነበራቸው ነው፡፡ ከበርካታ ንፁሃን ዜጎች ደም መፍሰስና እልቂት በኋላ ህወሓት ኢሕአዴግን መሥርቶ ወደ ሥልጣን ሲመጣም ከሻዕቢያ በስተቀር ሌሎቹ ድርጅቶች እስከ አመራሮቻቸው ደብዛቸው ጠፍቶ ነበር።ኢህአዲግ የሥልጣን ወንበሩን ከጨበጠ በኋላ በሽግግር መንግሥት ምስረታ ፓርቲዎች እንዲሳተፉ ይፋዊ ጥሪ በማስተላለፍ በፓርላማ መቀመጫ እንዲያገኙ በማድረግ ዴሞክራሲያዊ ሥርዐት የተመሰረተ ለማስመሰል ጥረት ቢያደርግም በተለያየ ምክንያት አባሮ መልሶ ለመበታተን ጊዜ አልወሰደበትም ነበር ፡፡