ታጣቂ ቡድኖች በማዕከላይ አፍሪቃ ሬፓብሊክ የደቀኑት ስጋት
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና –ጁላይ 12, 2014
የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ጉዳይ ከሰኔ 16 እስከ ሐምሌ 4 –ጁላይ 12, 2014
የአዲስ አበባ የመሬት ቅርጫ
ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም
ዮሐንስ ታደሰ አካ የሚባል ወጣት ስደተኛ የተስፋው ነጸብራቅ የሚል መጽሐፍ እአአ በ2013 በጀርመን አገር አሳትሞአል፤ ሳይፈራ ሀሳቡን የሚገልጽ በመሆኑ ሳይሆን አይቀርም በታወቀው ሦስተኛ ፖሊስ ጣቢያና በቃሊቲም ታስሮ ነበር፤ እሱ እንደሚለው ‹‹በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት የመሬት አስተዳደር ባለሥልጣን ውስጥ … የመሬት መሀንዲስ›› ተብሎ በ2000 ዓ.ም. ተቀጠረ፤ ከተቀጠረ በኋላ በቦዘኔነት ደመወዝ እየበላ ቆየ፤ ቀይቶ እንደተገነዘበው ‹‹… ለካስ እንኳንስ የእያንዳንዱ ሠራተኛ የሥራ ድርሻ ተለይቶ ሊታወቅ የመሥሪያ ቤቱም ሥራ አይታወቅም፤ መሥሪያ ቤቱም ሥራውን አያውቅም፤ የመሥሪያ ቤቱም ሃላፊዎች መሥሪያ ቤቱን አያውቁትም፤ ጉድ በል አዲስ አበባ! የምናወራው ስለዝነኛው አዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ነው።›› (ገ. 19)
ቆይታ ከአንዳርጋቸው ጽጌ እህት ጋር! “ለአንዳርጋቸው አታልቅሱ!” እስከዳር ጽጌ – ዳዊት ከበደ ወየሳ – አትላንታ
በተቃዋሚ ድርጅቶች ላይ የሚደረገው ማዋከብ ይቁም፣ የፖለቲካ እስረኞች በሙሉ አሁኑኑ ይፈቱ! የ ኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ የትግል ሽንጎ (ሽንጎ- Shengo) ጋዜጣዊ መግለጫ
የአቶ አዳርጋቸዉ መጋዝና እንድምታዉ
130407 ዜና 16:00 UTC
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና –ጁላይ 13, 2014
ጋዜጠኞቹና ብሎገሮቹ በቀጠሮው መሠረት ችሎት ሳይቀርቡ ቀሩ
ጋዜጠኞቹና ብሎገሮቹ በቀጠሮው መሠረት ችሎት ሳይቀርቡ ቀሩ –ጁላይ 13, 2014
አርጀንቲና ወይስ ጀርመን? እስክንድር ጀርመን ይላል –እርስዎስ?
አርጀንቲና ወይስ ጀርመን? –ጁላይ 13, 2014
ከጦማርያኑና ከጋዜጠኞቹ ጠበቃ አቶ አምሐ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ(በቴክኒክ ብልሽት የዘገየ ኢንተርቪው)- በዳዊት ሰለሞን
‹‹ከቅዳሜ አራት ሰዓት ጀምሮ ደምበኞቼ በህገ ወጥ መንገድ መታሰራቸው መታወቅ አለበት ››
‹‹የአካል ነጻነታቸው እንዲከበርም ክስ እንመሰርታለን››
የአራዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለመጨረሻ ጊዜ ከሚል ማስጠንቀቂያ ጋር ለፖሊስ የሰጠው የ28 ቀን ቀጠሮ ቅዳሜ የሚያበቃበት በመሆኑ የዞን ዘጠኞችና የጋዜጠኞቹን ጉዳይ ሲከታተሉ የቆዩ ቤተሰቦች፣ ወዳጆችና ጋዜጠኞች ቀደም ብለው ፍርድ ቤቱ ቅጥር ግቢ ደርሰዋል፡፡ምን ይወሰን ይሆን? በሁሉም ልብ የሚመላለስ ጥያቄም ነበር፡፡ከዘጠኙ ታሳሪዎች መካከል ስምንቱን በፍርድ ቤት ሲወክሉ የቆዩት ጠበቃ አምሀም ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ቀደም ብለው ቅጥር ግቢው ተገኝተዋል፡፡
አራት ሰዓት እንደሚጀመር የተገመተው ችሉቱ እስከ አምስት ከሩብ ድረስ በሌሎች ጉዳዩች ተወጥሮ ቆይቷል፡፡ከማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ነፍጥ ባነገቱ ወታደሮች ታጅበው መምጣት የነበረባቸው ኪቦርድ አንጋቾች እስራት ያልበገረውን ተስፋቸውን እየዘሩ ሊመጡ አልቻሉም፡፡ሁኔታው አግራሞት የፈጠረባቸው የተወሰኑ ጋዜጠኞች ወደ መዝገብ ቤት በማምራት መረጃ ጠየቁ፡፡የተሰማው በግቢው ውስጥ የነበሩትን ጠበቃ አምሀን ጨምሮ ያስገረመ፣ ያሳዘነና ያሳፈረ ነበር፡፡ከጠበቃው ጋር ያደረግኩት አጠር ያለ ቃለ ምልልስ እንደወረደ እነሆ፡፡
ጥያቄ—ወደ ፍርድ ቤቱ ሲመጡ በአእምሮዎ ያመላልሱት የነበረው ነገር ምንድን ነው?
ጠበቃ አምሀ—ምናልባት ምርመራ ባለመጨረሳችን ተጨማሪ ጊዜ ይሰጠን ይላሉ እያልኩ ነበር፡፡ይህንን ጥያቄ ፍርድ ቤቱ በምን አይነት መንገድ እንደሚመልስ ለማወቅም ፈልጌ ነበር፡፡የሆነው ግን በፍጹም ያልጠበቅነው ነገር ነው፡፡ ወደ መዝገብ ቤት ያመሩ ጋዜጠኞች ‹‹የልጆቹ መርማሪ ነኝ ያለ ሰው ምርመራዬን በመጨረሴ ለአቃቤ ህግ አስተላልፊያለሁ›› በማለቱ መዝገቡ እንደተዘጋ እንደተነገራቸው እንደነገሩኝ እውነት መሆኑን አጣርቻለሁ፡፡
ጥያቄ — ሁኔታውን እንደሰሙ ምን አደረጉ?
ጠበቃ አምሀ — እኛ ከቀጠሮው ሰዓት ቀደም ብለን ግቢው ውስጥ ተገኝተን መርማሪው እንዲህ ዓይነት ነገር ሲያቀርብ መስማት ነበረብን፡፡ በፍጹም እንዲህ አይነት መደረግ እንደሌለበት ቅሬታ እንደተሰማንና የተፈጸመው ነገር ህገ ወጥ መሆኑን ለዳኛው ተናግረናል፡፡
ጥያቄ — ህገ ወጥ የሆነው ምንድን ነው?
ጠበቃ አምሀ –ለፖሊስ ልጆቹን ለተጨማሪ 28 ቀናት እንዲያስር ፈቅዶለት የነበረው ፍርድ ቤቱ ነው፡፡እስካሁን ድረስ ደምበኞቼ የታሰሩት በፍርድ ቤት እውቅና ነው፡፡ከዛሬ አራት ሰዓት ጀምሮ ግን ደምበኞቼ የታሰሩት ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ በመሆኑ እስራታቸው ህገ ወጥ ነው፡፡ፖሊስ ልጆቹን ፍርድ ቤት አቅርቦ ምርመራውን መጨረሱን ማስረዳትና ክስ የሚመሰርት ከሆነም ማሳወቅ ይገባው ነበር፡፡የሚመሰርተው ክስ ዋስትና የሚያስከለክልና የማያስከለክል መሆኑን መወሰን የነበረበት ፍርድ ቤቱ ነው፡፡ይህ ሳይደረግ መዝገቡ ተዘግቷል መባሉ ህገ ወጥ ነው፡፡
ጥያቄ — ከአሁን በኋላ ለደምበኞችዎ ሊያደርጉ የሚችሉት ነገር ምንድን ነው?
ጠበቃ አምሀ — ሰኞ ወይም ማክሰኞ የደምበኞቼ የአካል ነጻነት እንዲከበር ክስ እመሰርታለሁ፡፡ሰኞን የምንጠብቀው እንደተናገሩት ክስ የሚመሰርቱ ከሆነና የት እንደሚመሰርቱ ለማጣራት ነው፡፡
ጥያቄ –በ‹‹ሃፒየስ ኮርፐስ›› ደምበኞችዎ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ክስ የምትመሰርቱት በየትኛው ፍርድ ቤት ነው?
ጠበቃ አምሀ –ክሱን የምንመሰርተው በከፍተኛው ፍርድ ቤት ነው፡፡
ጥያቄ –ደምበኞችዎን በማዕከላዊ በወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲጎበኙ ተፈቅዶላቸዋል፡፡ነገር ግን እስካሁን ድረስ አቤል ዋበላን ሰዎች ማግኘት እንዳልቻሉ እየተናገሩ ነው ምክንያቱን ለማጣራት ሙከራ አድርጋችኋል?
ጠበቃ አምሀ — ከዚህ በፊት ልጆቹን በሳምንት አንድ ቀን እንዳናግራቸው ይፈቀድልኝ ነበር፡፡በዚሁ ቀን ስምንቱንም ልጆች የማናገር ዕድል ነበረኝ፡፡ አሁን ግን በአንድ ቀን ማናገር የምትችለው አንዱን ደምበኛህን ብቻ ነው ብለውኛል፡፡እንግዲህ ስምንቱን ደምበኞቼን ለማግኘት አራት ሳምንት ያስፈልገኛል ማለት ነው፡፡ ይህም ፍጹም ህገ ወጥ ድርጊት ነው፡፡ደምበኞቼ ከጠበቃቸው ጋር የመገናኘት ህገ መንግስታዊ መብታቸው ሊከበርላቸው ይገባል፡፡
አቤልን በተመለከተ በተወሰነ ደረጃ ከመርማሪዎቹ ጋር ያልተስማማበት ነገር እንዳለ ሰምቼያለሁ፡፡ ነገር ግን ይህንን ከእርሱ አንደበት ለመስማት እርሱን መጀመሪያ ማግኘት ይኖርብኛል፡፡
ጥያቄ –ደምበኞችዎ በምርመራ ወቅት የማያምኑትን ወይም ያልተሳተፉበትን ጉዳይ እንደተሳተፉበት አድርገው ቃላቸውን በሃይል እንዲሰጡ ስለመደረጋቸው ይነገራል፡፡በሀይል የሰጡት ቃል በፍርድ ቤት የሚኖረው ተቀባይነት ምን ያህል ነው? በተለይ በጸረ ሽብር አዋጁ?
ጠበቃ አምሀ — ለፖሊስ የሚሰጥን ቃል በተመለከተ የወንጀልና የሥነ-ስርዓት ህጉ በዝርዝር ይናገራሉ፡፡ለፖሊስ በሀይል እንደተሰጠ የተነገረበት የተጠርጣሪ ቃል ያን ያህል ዋጋ አይኖረውም፡፡ ሰዎችም በራሳቸው ላይ እንዲመሰክሩ ሊገደዱ አይገባም፡፡
ጥያቄ — ቀሪዎቹ ደምበኞችዎ የፊታችን ሰኞ ከሰዓት በኋላ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ቀጠሮ ተይዞባቸው ነበር፡፡ ከዛሬው በመነሳት ሰኞ የሚቀርቡ ይመስልዎታል?
ጠበቃ አምሀ —- አይመስለኝም፡፡ እኛ ግን ቀጠሯችንን አክብረን በቦታው እንገኛለን፡፡
————– ታላቅ ምስጋና ለጠበቃ አምሀ ————-
ተበላ! ጀርመን በላችው!
ከጦማርያኑና ከጋዜጠኞቹ ጠበቃ አቶ አምሐ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ
(በቴክኒክ ብልሽት የዘገየ ኢንተርቪው)
ከጦማርያኑና ከጋዜጠኞቹ ጠበቃ አቶ አምሐ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ
‹‹ከቅዳሜ አራት ሰዓት ጀምሮ ደምበኞቼ በህገ ወጥ መንገድ መታሰራቸው መታወቅ አለበት ››
‹‹የአካል ነጻነታቸው እንዲከበርም ክስ እንመሰርታለን››
የአራዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለመጨረሻ ጊዜ ከሚል ማስጠንቀቂያ ጋር ለፖሊስ የሰጠው የ28 ቀን ቀጠሮ ቅዳሜ የሚያበቃበት በመሆኑ የዞን ዘጠኞችና የጋዜጠኞቹን ጉዳይ ሲከታተሉ የቆዩ ቤተሰቦች፣ ወዳጆችና ጋዜጠኞች ቀደም ብለው ፍርድ ቤቱ ቅጥር ግቢ ደርሰዋል፡፡ምን ይወሰን ይሆን? በሁሉም ልብ የሚመላለስ ጥያቄም ነበር፡፡ከዘጠኙ ታሳሪዎች መካከል ስምንቱን በፍርድ ቤት ሲወክሉ የቆዩት ጠበቃ አምሀም ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ቀደም ብለው ቅጥር ግቢው ተገኝተዋል፡፡
አራት ሰዓት እንደሚጀመር የተገመተው ችሉቱ እስከ አምስት ከሩብ ድረስ በሌሎች ጉዳዩች ተወጥሮ ቆይቷል፡፡ከማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ነፍጥ ባነገቱ ወታደሮች ታጅበው መምጣት የነበረባቸው ኪቦርድ አንጋቾች እስራት ያልበገረውን ተስፋቸውን እየዘሩ ሊመጡ አልቻሉም፡፡ሁኔታው አግራሞት የፈጠረባቸው የተወሰኑ ጋዜጠኞች ወደ መዝገብ ቤት በማምራት መረጃ ጠየቁ፡፡የተሰማው በግቢው ውስጥ የነበሩትን ጠበቃ አምሀን ጨምሮ ያስገረመ፣ ያሳዘነና ያሳፈረ ነበር፡፡ከጠበቃው ጋር ያደረግኩት አጠር ያለ ቃለ ምልልስ እንደወረደ እነሆ፡፡
ጥያቄ---ወደ ፍርድ ቤቱ ሲመጡ በአእምሮዎ ያመላልሱት የነበረው ነገር ምንድን ነው?
ጠበቃ አምሀ---ምናልባት ምርመራ ባለመጨረሳችን ተጨማሪ ጊዜ ይሰጠን ይላሉ እያልኩ ነበር፡፡ይህንን ጥያቄ ፍርድ ቤቱ በምን አይነት መንገድ እንደሚመልስ ለማወቅም ፈልጌ ነበር፡፡የሆነው ግን በፍጹም ያልጠበቅነው ነገር ነው፡፡ ወደ መዝገብ ቤት ያመሩ ጋዜጠኞች ‹‹የልጆቹ መርማሪ ነኝ ያለ ሰው ምርመራዬን በመጨረሴ ለአቃቤ ህግ አስተላልፊያለሁ›› በማለቱ መዝገቡ እንደተዘጋ እንደተነገራቸው እንደነገሩኝ እውነት መሆኑን አጣርቻለሁ፡፡
ጥያቄ --- ሁኔታውን እንደሰሙ ምን አደረጉ?
ጠበቃ አምሀ -- እኛ ከቀጠሮው ሰዓት ቀደም ብለን ግቢው ውስጥ ተገኝተን መርማሪው እንዲህ ዓይነት ነገር ሲያቀርብ መስማት ነበረብን፡፡ በፍጹም እንዲህ አይነት መደረግ እንደሌለበት ቅሬታ እንደተሰማንና የተፈጸመው ነገር ህገ ወጥ መሆኑን ለዳኛው ተናግረናል፡፡
ጥያቄ -- ህገ ወጥ የሆነው ምንድን ነው?
ጠበቃ አምሀ --ለፖሊስ ልጆቹን ለተጨማሪ 28 ቀናት እንዲያስር ፈቅዶለት የነበረው ፍርድ ቤቱ ነው፡፡እስካሁን ድረስ ደምበኞቼ የታሰሩት በፍርድ ቤት እውቅና ነው፡፡ከዛሬ አራት ሰዓት ጀምሮ ግን ደምበኞቼ የታሰሩት ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ በመሆኑ እስራታቸው ህገ ወጥ ነው፡፡ፖሊስ ልጆቹን ፍርድ ቤት አቅርቦ ምርመራውን መጨረሱን ማስረዳትና ክስ የሚመሰርት ከሆነም ማሳወቅ ይገባው ነበር፡፡የሚመሰርተው ክስ ዋስትና የሚያስከለክልና የማያስከለክል መሆኑን መወሰን የነበረበት ፍርድ ቤቱ ነው፡፡ይህ ሳይደረግ መዝገቡ ተዘግቷል መባሉ ህገ ወጥ ነው፡፡
ጥያቄ -- ከአሁን በኋላ ለደምበኞችዎ ሊያደርጉ የሚችሉት ነገር ምንድን ነው?
ጠበቃ አምሀ -- ሰኞ ወይም ማክሰኞ የደምበኞቼ የአካል ነጻነት እንዲከበር ክስ እመሰርታለሁ፡፡ሰኞን የምንጠብቀው እንደተናገሩት ክስ የሚመሰርቱ ከሆነና የት እንደሚመሰርቱ ለማጣራት ነው፡፡
ጥያቄ --በ‹‹ሃፒየስ ኮርፐስ›› ደምበኞችዎ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ክስ የምትመሰርቱት በየትኛው ፍርድ ቤት ነው?
ጠበቃ አምሀ --ክሱን የምንመሰርተው በከፍተኛው ፍርድ ቤት ነው፡፡
ጥያቄ --ደምበኞችዎን በማዕከላዊ በወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲጎበኙ ተፈቅዶላቸዋል፡፡ነገር ግን እስካሁን ድረስ አቤል ዋበላን ሰዎች ማግኘት እንዳልቻሉ እየተናገሩ ነው ምክንያቱን ለማጣራት ሙከራ አድርጋችኋል?
ጠበቃ አምሀ --- ከዚህ በፊት ልጆቹን በሳምንት አንድ ቀን እንዳናግራቸው ይፈቀድልኝ ነበር፡፡በዚሁ ቀን ስምንቱንም ልጆች የማናገር ዕድል ነበረኝ፡፡ አሁን ግን በአንድ ቀን ማናገር የምትችለው አንዱን ደምበኛህን ብቻ ነው ብለውኛል፡፡እንግዲህ ስምንቱን ደምበኞቼን ለማግኘት አራት ሳምንት ያስፈልገኛል ማለት ነው፡፡ ይህም ፍጹም ህገ ወጥ ድርጊት ነው፡፡ደምበኞቼ ከጠበቃቸው ጋር የመገናኘት ህገ መንግስታዊ መብታቸው ሊከበርላቸው ይገባል፡፡
አቤልን በተመለከተ በተወሰነ ደረጃ ከመርማሪዎቹ ጋር ያልተስማማበት ነገር እንዳለ ሰምቼያለሁ፡፡ ነገር ግን ይህንን ከእርሱ አንደበት ለመስማት እርሱን መጀመሪያ ማግኘት ይኖርብኛል፡፡
ጥያቄ --ደምበኞችዎ በምርመራ ወቅት የማያምኑትን ወይም ያልተሳተፉበትን ጉዳይ እንደተሳተፉበት አድርገው ቃላቸውን በሃይል እንዲሰጡ ስለመደረጋቸው ይነገራል፡፡በሀይል የሰጡት ቃል በፍርድ ቤት የሚኖረው ተቀባይነት ምን ያህል ነው? በተለይ በጸረ ሽብር አዋጁ?
ጠበቃ አምሀ -- ለፖሊስ የሚሰጥን ቃል በተመለከተ የወንጀልና የሥነ-ስርዓት ህጉ በዝርዝር ይናገራሉ፡፡ለፖሊስ በሀይል እንደተሰጠ የተነገረበት የተጠርጣሪ ቃል ያን ያህል ዋጋ አይኖረውም፡፡ ሰዎችም በራሳቸው ላይ እንዲመሰክሩ ሊገደዱ አይገባም፡፡
ጥያቄ -- ቀሪዎቹ ደምበኞችዎ የፊታችን ሰኞ ከሰዓት በኋላ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ቀጠሮ ተይዞባቸው ነበር፡፡ ከዛሬው በመነሳት ሰኞ የሚቀርቡ ይመስልዎታል?
ጠበቃ አምሀ ---- አይመስለኝም፡፡ እኛ ግን ቀጠሯችንን አክብረን በቦታው እንገኛለን፡፡
-------------- ታላቅ ምስጋና ለጠበቃ አምሀ -------------