UTC 16:00 የዓለም ዜና 14.07.2014
ሀምሌ 05,2006 የሙዚቃ ቃና ፐሮግራም( July 12,2014) –ጁላይ 14, 2014
የጀርመን የዓለም ዋንጫ አሸናፊነትና የጀርመናውያን አስተያየት
የእሥራኤልና የሐማስ ፍልሚያ እንዲቆም የተያዘው ዓለም አቀፍ ምክክር
በአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት በወቅታዊ ፖለቲካዊ ሁኔታዎችና በወጣቱ ሚና ላይ ውይይት ተደረገ – ፍኖተ ነጻነት
በአንድነት ፓርቲ የወጣቶች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አዘጋጅነት ትላንት ሀምሌ 6 ቀን 2006 ዓ.ም በፓርቲው ጽ/ቤት “የኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታና የወጣቱ ተሳትፎ” በሚል ርዕስ ውይይት ተደረገ፡፡
በፖለቲከኛና ደራሲ አስራት አብርሃም የውይይት መነሻ ሃሳብ አቅራቢነት በተደረገው ውይይት ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ አበበ አካሉ ወጣቱ ኢህአዴግ እየፈፀመ ባለው እስር ሳይሸበር ትግሉን በቀዳሚነት መምራት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ አክለውም በቅርቡ መንግስት ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ለማዳከም ወጣት ፖለቲከኞች ላይ የወሰደው የእስር እርምጃ የተቃውሞ ትግሉን እንደማያዳክመው ጠቅሰው፣ አንድነት አመራሮቹን አሳስሮ እንደማይቀመጥ ተናግረዋል፡፡
በመቀጠል ፖለቲከኛና ደራሲ አስራት አብርሃም መድረኩን በመረከብ በሁለት ምዕራፎች የተከፈለውን የውይይት መነሻ ሃሳብ አቅርቧል፡፡ በመጀመሪያው ምዕራፍ ስለ ኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ ሰፋ ያለ ዳሰሳ ያቀረበ ሲሆን ኢህአዴግ ለ23 ዓመታት በማሰር ትግልን ለማስቆም የያዘውን ስልት እስርን ባለመፍራት ማስቀረት እንደሚቻል ተንትኗል፡፡ በሁለተኛው ምዕራፍ የወጣቱ ሚና ምን መሆን እንዳለበት በስፋት በመተንተን፣ ወጣቱ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ቀዳሚ ተዋናይ መሆን እንዳለበት ምክረ ሃሳብ አቅርቧል፡፡
የመነሻ ሃሳቡን ተከትሎ ሰፊ ውይይትና አስተያየት በተሳታፊዎች ቀርቧል፤ አቶ አስራት አብርሃምም ለቀረቡለት ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡ ውይይቱን በመዝጊያ ንግግር የደመደመት የአንድነት ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት አባልና የዲሲፕሊን ኮሚቴ ሰብባቢ ሻለቃ አርጋው ካብታሙ በፖለቲካ ውስጥ የወጣቶች ተሳትፎ አስፈላጊ መሆኑን በመጥቀስ ወደትግሉ ጎራ እንዲመጡ ለወጣቶች የትግል ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የጀርመንና የዩናይትድ ስቴትስ ግንኙነት
የማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ኃላፊ ነገ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ታዘዙ – ፍኖተ ነጻነት
የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች የሆኑትን ወጣት ሀብታሙ አያሌውንና አቶ ዳንኤል ሺበሺን ለሰባት ቀናት አስሮ እስከ አሁን ፍርድ ቤት ያላቀረበው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ዘርፍ እና የመአከላዊ ወንጀል ምርመራ ሀላፊ ኮማንደር ተክላይ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ የታዘዘው የታሳሪዎቹ ጠበቆች ባቀረቡት ክስ መሰረት ነው፡፡
ዛሬ ሀምሌ 6 ቀን 2006 ዓ.ም የፌደራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት የአራዳ ምድብ ፍ/ብሔር ችሎት በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት የመአከላዊ ወንጀል ምርመራ ሀላፊ ኮማንደር ተክላይ ታሳሪዎቹን ይዘው በነገው ዕለት ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ተወስኗል፡፡
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና –ጁላይ 14, 2014
የፖለቲካ መሪዎች እሥርና ይዞታ ፓርቲዎቹን እያሳሰበ ነው –ጁላይ 14, 2014
በታሠሩ የፖለቲካ መሪዎች ጉዳይ ኢዴፓ መግለጫ ሰጠ –ጁላይ 14, 2014
ፖሊስ ጋዜጠኞቹና አምደኞቹን በቀጠሯቸው ፍርድ ቤት አላቀረበም –ጁላይ 14, 2014
ፖሊስ ጋዜጠኞቹና አምደኞቹን በቀጠሯቸው ፍርድ ቤት አላቀረበም
በታሠሩ የፖለቲካ መሪዎች ጉዳይ ኢዴፓ መግለጫ ሰጠ
የፖለቲካ መሪዎች እሥርና ይዞታ ፓርቲዎቹን እያሳሰበ ነው
አቶ ሽመልስ ከማል የሚመሩት ፕሬስ ድርጅት ደካማ ነው ተባለ
ሐምሌ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፓርላማ : ባህል ፣ ቱሪዝምና መገናኛ ብዙሃን ቋሚ ኮምቴ ስብሳቢ 73ኛ የምስረታ ዓመቱን በቅርቡ ያከበረውን የኢትዮጽያ ፕሬስ ድርጅት በቁሙ እየሞተ መሆኑን በመጠቆም በራሱ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይትችትአቀረቡ፡፡
የቋሚ ኮምቴው ስብሳቢ ወ/ሮ ፈቲያ ዩሱፍ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ዓርብ እና ቅዳሜ እለት በታተመ ቃለ ምልልሳቸው እንደተናገሩት የአዲስ ዘመን ፣ ኢትዮጵያ ሄራልድ ፣ በሬሳ ፣ ዓልኣለም ጋዜጦች እና የዘመን መጽሄት አሳታሚ የሆነውና በአቶሽመልስከማልየቦርድሰብሳቢነትየሚመራው የኢትዮጽያፕሬስድርጅትተወዳዳሪመሆንእንዳልቻለ፣ የጋዜጦቹህትመትቁጥርምከጊዜወደጊዜእያሽቆለቆለእንደመጣ፣በገበያላይየሚያነበውእንደሌለበመጥቀስበይፋ ድክመቱንተናግረዋል፡፡
ድርጅቱ ችግሩን ለመቅረፍ ወደ ኮርፖሬት አደረጃጀት እንዲገባ በተደጋጋሚ እንደ ተነገረው ነገርግን በማኔጅመንቱ ድክመት እንዳልተሳካ ተናግረዋል፡፡ «አምናሪፎርምውስጥግቡብለናቸውየሆነነገርጀምረውእኛሥራበዝቶብን ወደሌላዘወርስንልይተውታል» በማለት የማኔጅመንቱን እንዝህላልነት አሳይተዋል፡፡
ሠራተኛውገሚሱበሲቪልሰርቪስ፣አንዳንዱበቦርድእንደሚተዳደርናይህልዩነትበኮርፖሬትአደረጃጀት እንዲስተካከልተነግሮአቸውምእንዳላስተካከሉትወ/ሮፈቲያገልጸዋል።
በአማራ ክልል አርሶ አደሮችን ትጥቅ የማስፈታት ሂደቱ ውጤታማ አይደለም ተባለ፡፡
ሐምሌ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአስተዳደር ፀጥታ እና የፖሊስ ኮሚሺን በጋራ የ2006 ዓ.ምየ11 ወራት አፃፀም በገመገሙበት ውይይት የጎጃም ፤የጎንደር ፤የሺዋ እና የኦሮሞ አርሶ አደሮች ዛሬምበድብቅመሳሪያዎችንበነፍስወከፍበየቤቱይዘው እንደሚገኙያወሱሲሆን፣ አርሶ አደሩ የጦር መሳሪያውን እንዲመልስጥረትቢደረግምአልተሳካምብለዋል፡፡
አዲስህግእንዲወጣየጠየቁትየፀጥታሃይሎች በአርሶአደሩበህገወጥእጅየተሰገሰገውከ 4 ሚሊዩንበላይየሚገመትየተለያየየጦርመሳሪያ በአገሪቱ ለሚፈጸም ግድያ ዋና መንስኤ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
በዘመቻየጦርመሳሪያማስፈታትእናየቅጣትወሰንመመሪያእንደሃገርአለመኖርችግር መሆኑንበማንሳትየፊደራል መንግስት የህገወጥመሳሪያቁጥጥርአዋጅእንዲያወጣበሪፖርታቸውጠይቀዋል፡፡
የፌድራልፖሊስ መረጃ እንደሚያመለክተው ከአማራ ክልል በመቀጠል አፋር እና ሶማሌ መሳሪያ ያላ ወረዱ ክልሎች ተብለው ተጠቅሰዋል።
“ግንቦት ሰባትን ለማዳከም የተወሰዱ እርምጃዎች ከፍተኛ ውጤት አስገኝተዋል” ሲል የፀረ ሺብር ግብረሃይል አስታወቀ፡፡
ሐምሌ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቅዳሜ እና እሁድ በጠቅላይ ሚኒስትር አዳራሽ የጸረ ሽብር ግብረሃይሉና የኢህአዴግ ባለስልጣናት በጋራ የመከሩ ሲሆን፣ስኬታማ ስራዎችን ለመስራት 3 ሚልየን 400 ሺ ዶላር ወጭ ማድረጉን ገልጿል፡፡ “ኢሳያስ ቢያስፈልገን እርሱን የመያዝ አቅም ላይነን” በማለትራሱን ያሞካሸውግብረሃይሉ ፣ “ኢህአዴግንግስት ንቧን በመያዙየቀጣዩምርጫድልበርላይይገኛል” ሲልበሪፖርቱ አትቷል።
ከሁሉምክልሎችየደህንነትሃይሎችአመራሮችበተካፈሉበትውይይትበቀጣይከግንቦትሰባትሊፈፀምይችላልየተባሉ ስጋቶችም ተነስተዋል። የመከላከያሃይሉልዩትዕዛዝተሰጥቶትየተዘናጋበትንክልልእንዲሸፍንናከፍተኛጥንቃቄእንዲወስድመመሪያእንዲሰጠው ተወስናል፡፡
“ግንቦትሰባትእስከጎንደርያለምንምእንከንቀድሞመግባትይችላል”የሚለው ሪፖርቱ፤የመከላከያሃይሉእናየደህንነትስራውየላላበመሆኑመጠናከርአለበትብሎአል። ይህንን ተከትሎም በተሰብሳቢዎች መካከል ከፍተኛ ክርክር ተካሂዷል።
አንደኛው ወገን ለህዝቡበተለይለአርሶአደሩመሳሪያእያከፋፈለበቀላሉጎንደርንሊይዝይችላልየሚል ክርክር ያስነሳ ሲሆን፣ ሌለው ወገን ደግሞ ይህን ሃሳብ ቢጋራም፣ ሊሳካ የሚችለው ግን በሻእቢያመታገዝከቻለብቻነው የሚሉሃሳብ አንስቷል። ይህ ይሆናል ብሎ ማሰብህልምነውበማለት የተከራከሩም ነበሩ።
በውይይቱ መጨረሻየመከላከያሃይሉድክመትታምኖበትበአዲስየአጋዚክፍለጦር እየታገዘጥበቃውእንዲጠናከርስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡የደህንነትሃይሉቁጥርይበልጥእንዲጨምርና በቁጥጥሩ የትግራይ ጸረ ሽብር ግብረሃይልከፍተኛ ሚና እንዲጫወት ተወስኗል።
የአቶአንዳርጋቸውጽጌንመያዝተከትሎቀንደኛየተቃዋሚአባላትመያዛቸው፤ህዝቡ ለአቶ አንዳርጋቸው መያዝ ልዩትኩረትእንዳይሰጠው አድርጓል በማለትሪፖርቱ ጠቅሶ፣ ጸረ ሽብር ግብረሃይሉ የወሰደውጥበብ የተሞላበት እርምጃ ነው በማለት እርምጃውን አሞካሽቷል። በሌላ በኩል ግን በአቶ አብርሃደስታ፣ሀብታሙአያሌው፣ዳንኤልሺበሺ እና የሽዋስ አሰፋ ላይ የተወሰደውእርምጃበኢህአዴግላይጥላቻፈጥሮተቃዋሚዎች የበለጠእንዲያንሰራሩያደርጋቸዋል በማለት ሀሳብ የሰነዘሩም ነበሩ።
በቅርቡየፊደራልፖሊስእናየፀረሺበርግብረሃይሉረዘምያለዶክመንታሪሰርቶለእይታእንዲያቀርብየታዘዘሲሆን፣ከሰውየውየተገኘውመረጃአመርቂእናአጋዥአለመሆኑታምኖበትእንደገናምቢሆንየህይዎትታሪኩንእንዲናገርበማድረግ እንዲሰራትእዛዝ ተላልፏል። ዝግጅቱምበኢቲቪአንድእናእሁድበፖሊስፕሮግራምበድጋሚእንዲተላለፍተወሰኗል፡፡
በኖርዌይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌና ሌሎችም የታሰሩት ኢትዮጵያውያን እንዲፈቱ ጠየቁ
ሐምሌ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢትዮጵያውያኑ ዛሬ በኖርዌይ የእንግሊዝ ኢምባሲ ፊት ለፊት ባደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ የአቶ አንዳርጋቸውን ተላልፎ መሰጠት በእጅጉ አውግዘዋል። ከፍተኛ ቁጣ ባስተናገደው ተቃውሞ እንግሊዝ እየወሰደችው ያለው እርምጃ እንዲብራራላቸው ጠይቀዋል።
በኖርዌይ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ፊት ለፊት ባደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ ደግሞ በቅርቡ ከደቡብ ሱዳን ተይዘው ለኢህአዴግ የደህንነት አባላት ተላልፈው የተሰጡትን የአቶ ኦኬሎ አኳይን ጉዳይ በማንሳት ኖርዌይ መልስ እንድትሰጣቸው ጠይቀዋል።
የእንግሊዝ ኢምባሲ ተወካይ ሰልፈኞቹን ወጥተው ያነጋገሩ ሲሆን፣ እንግሊዝ አቶ አንዳርጋቸውን ለመጎብኘት ፈቃድ እንዲሰጣት ጥያቄ ማቅረቡዋንና መልስም እየጠበቀች መሆኗን መናገሩዋን የሰልፉ አስተባባሪ ግብረ ሃይል አባል የሆኑት አቶ ደባሱ መሰለ ገልጸዋል።
ኖርዌይ በበኩሏ የአቶ ኦኬሎን ጉዳይ በቅርብ ተከታትላ አስፈላጊውን መረጃ እንደምትሰጥ መግለጿን አስተባባሪው አቶ ዳንኤል አበበ ተናግረዋል
ይህ በእንዲህ እንዳለ የአቶ አንዳርጋቸውን በግፍ መታሰር አሁንም የህዝቡ የመነጋገሪያ አጀንዳ እንደሆነ ነው። ኢህአዴግን በመረጠው መንገድ እንፋለማለን ያሉ ሰዎች የተለያዩ የተቃዋሚ ድርጅቶችን እየተቀላቀሉ ሲሆን፣ ግንቦት7ትን ለመቀላቀል የሚጠይቁ ኢትዮጵያውያን ቁጥራቸው ከፍተኛ መሆኑን ከድርጅቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የአቶ አንዳርጋቸው መታሰርን ትህዴን፣ አርበኞች ግንባር፣ አርዱፍና በጄ/ል ከማል ገልቹ የሚመራው ኦነግ ማውገዛቸው ይታወቃል። በሰላማዊ ትግል ከሚታገሉ ድርጅቶች መካከል ደግሞ ሰማያዊ ፓርቲ “የአቶአንዳርጋቸውፅጌሰብዓዊአያያዝእንዳሳሰበውና “ህወሓትመራሹየኢህአዴግአገዛዝአያያዛቸውንግልፅእንዲያደርግሰብዓዊክብራቸውምእንዲጠበቅበጥብቅ” ማሳሰቡ ይታወሳል።
በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ፕሪቶሪያ በሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ ፊት ለፊት ማክሰኞቹ የተቃውሞ ሰልፍ የሚያደርጉ ሲሆን በሎስ አንጀለስ የእንግሊዝ ኮንስላ ጽ/ቤት ፊት ለፊትም በተመሳሳይ ቀን ተቃውሞ ይደረጋል።
የጨነገፉ የአፍሪካ መንግስታት የሞራል ዝቅጠት
ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
በልጆች ላይ የሚፈጸም ወንጀል በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸም ወንጀል ነውን ?
የጨነገፉ (ዉድቀት የገጠማቸው) መንግስታትን አስመልክቶ በቅርቡ በወጣ መረጃ መሰረት ከአስሩ የመጀመሪያዎቹ ቁንጮ አገሮች ስድስቱ እና ከ25ቱ የመጀመሪያዎቹ ቁንጮ አገሮች 18ቱ በአፍሪካ የሚገኙ አገሮች ናቸው፡፡ የዚህ ትችት ዓላማ የጨነገፉ የአፍሪካ አገሮችን ሬሳ መደብደብ አይደለም፣ ወይም ደግሞ በብዙ የአፍሪካ አገሮች የአፍሪካን የመንግስት አስተዳደር ውድቀት ትረካ ለማውሳት አይደለም፣ እንደዚሁም ለህዝቦቻቸው መሰረታዊ እና አስፈላጊ የሆኑ አገልግሎቶችን ማቅረብ የማይችሉ፣ የህዝቡን ደህንነት ማስከበር የተሳናቸው፣ እጅግ በጣም እየተስፋፋ የመጣውን ሙስና መቆጣጠር ያልቻሉ፣ መንግስታዊ ወንጀለኝነትን የሚያራምዱ፣ እየተስፋፋ የመጣውን የሰብአዊ መብት ረገጣ ማስቆም የማይችሉ እና ሀብት ባላቸው እና በሌላቸው መካከል ያለውን ልዩነት ለማጥበብ የማይችሉ አቅመቢስ ድሁር የአፍሪካ ሽባ መንግስታት ን ለመንቀፍ አይደለም፡፡ ስለአፍሪካ የጨነገፉ መንግስታት የሞራል ዝቅጠት ባሰብኩ ቁጥር ስሜቴ ይረበሻል፡፡
በመጀመሪያ ደረጃ የጨነገፈ (ዉድቀት የገጠማቸው) የአፍሪካ መንግስት ማለት ምን ማለት ነው? የጨነገፈ መንግስት በገሀዱ ዓለም ያለው መንግስት መጥፎ አምሳያ ነው፡፡ የአፍሪካ የጨነገፉ የአፍሪካ መንግስታትን መንግስታት ማለት ኮካ ኮላ ለሰውነት ጠቃሚ የሆነ መጠጥ ነው አንደማለት ነው (ኮካኮላ የሚባለው መጠጥ በኢትዮጵያ አይጠጣ !)፡፡ ለምዕራባውያን እና ለእነርሱ የብዙሀን የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተቋማት የአፍሪካ የጨነገፈ መንግስት ለልግስና የተቀመጠ ግኡዝ ነገር ነው፣ የጨነገፈ መንግስት የእዳ ክፍያ ስርዓት መሞከሪያ እና የይስሙላ ልማት ባሪያ ነው፡፡ ለምዕራቡ ዓለም አካዳሚ የአፍሪካ የጨነገፈ መንግስት የአፍሪካን ገዳይ መንግስት የሚያጠኑበት እና ስህተት የሰራ መሆኑን የሚያሳውቁበት ዘዴ ነው፡፡ በጎ አመለካከት ላላቸው እና ለትችት አቅራቢዎች የጨነገፈ መንግስት አታላይ እና አስመሳይ የሆነ መንግስት መሳይ ቡድን ነው፡፡ የሞራል ስብዕና የሌላቸው የአፍሪካ የጨነገፉ መንግስታት በሞራል የበከቱ እና ውግዘት የሚገባቸው ደንቆሮዎች ናቸው፡፡ የጨነገፉ መንግስታትን አመልካች መለኪያዎች (በቋፍ ላይ ያሉ በሚል እንደገና የተሰየሙ እና በ2014 በፖለቲካዊ አካሄድ የጨነገፈ ተብለው የተፈረጁ) የሰላም እና የውጭ ፖሊሲ መጽሄት በጋራ በማተም ባወጣው ዘገባ መሰረት የአፍሪክ የጨነገፉ መንግስታት በ12 በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ እና በፖለቲካ አመልካች መስፈርቶች ዝቀተኛ ውጤት አግኝተዋል፡፡
አሁን በህይወት የሌሉት የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ፕሬዚዳንት ሁበርት ምፍሬ እ.ኤ.አ በ1948 ለዴሞክራቲክ ፓርቲ እንዲህ የሚል የተማጽኖ ጥያቄ አቅርበው ነበር፣ “ለሰብአዊ መብቶች መከበር ጥረት አድርጉ“ እናም በመጨረሻ የ1964 የሲቪል መብቶች ደራሲ የሚከተለውን ምልከታ አድርገው ነበር፣ “…የመንግስት የሞራል ጥያቄ ያ መንግስት የህይወት ስንክሳር የተዘባረቀባቸውን ህዝቦች፣ ህጻናት፣ ድንግዝግዝ ባለ ህይወት ውስጥ ላሉ ህዝቦች፣ ለአዛውንቶች፣ በጨለማ ህይወት ውስጥ ላሉ፣ ለታመሙ፣ ለምስኪኖች እና ለአካለ ጎደሎዎች እንዴት በማድረግ ማስተናገድ እንደሚችል የሚመለከትበት ሁኔታ ነው፡፡ “በሞራል ስብዕና የበከቱ የመንግስታት አመላካች መለኪያዎች ብዙዎቹ የአፍሪካ መንግስታት ከመጀመሪያው ረድፍ ላይ ይቀመጣሉ፡፡“ እነዚህ ለመንግስት፣ ገዥ አካል እና ህጋዊ መንግስት የሚደረጉ ደካማ ይቅርታዎች በውድቀት ላይ ያሉትን እንዴት እንደሚያስተናግዱ እና የጧት ህይወታቸው በአሁጉሩ እንዴት እንደሆነ የሚያመላክት አሳፋሪ ድርጊት ነው፡፡
የህጻናት ጠለፋ፣
አሸባሪ ቡድን የናይጀሪያ 300 ልጃገረዶች አፍኖ ከወሰደ ከሶስት ወራት በኋላ ልጆቹ የት እንዳሉ እንኳን ፍንጭ ማግኘት አልቻለም፣ እንዲሁም መንግስት እነዚህን ልጃገረዶች ፈልጎ ለማስፈታት ያደረገው ይህ ነው የሚባል ጥረት የለም፡፡ ሁሉም ንጉሶች እና አጋፋሪዎቻቸው ቢሆኑ ሊፍልጓቸው አልፈለጉም፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ የልጃገረዶቹ መታፈን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሞራል ቁጣ እና ውግዘትን አስከትሏል፡፡ ቀዳሚ ያሜሪካ እመቤት ሚሸሌ ኦባማ በልጃገረዶቹ መጠለፍ የተሰማቸውን ሀዘን እና ቁጣ ገልጸዋል፡፡ እናም በእጃቸው የተጻፈበት ካርድ ከፍ አድርገው በመያዝ “ልጃገረዶቻችንን መልሱ“ ብለዋል፡፡ ይህንን አስቀያሚ ጉዳይ ግለሰብአዊ አድርገውታል፡፡ ሚስስ ኦባማ እንዲህም ብለው ነበር፣ “ባራክ እና እኔ ልጆቻችንን በዚህ አይተናል“፡፡ በጣም አስቀያሚ ነገር ነው፣ የናይጀሪያ ፕሬዚዳንት እና ሚስስ ጉድላክ ጆናታን የዚህ ዓይነት ስሜት አልተሰማቸውም፡፡ ቢያንሰ እንኳ ምንም ያሉት ነገር የለም፡፡ የአፍሪካ ታላቅ እያለ ከሚመጻደቅ አገር በምን ዓይነት መለኪያ ነው 300 ልጃገረዶች ያለምንም ፍንጭ ሳይኖረው በቀላሉ ሊጠፉ የሚችሉት?
የህጻናት ወታደሮች፣
የሞራል ስብዕና መጥፋት እና የአፍሪካን ህጻናት ህልውና እና ደህንነት ለመጠበቅ ቁርጠኝነት ያለው ውሳኔ ያለመወሰን ሁኔታ በህጻናቱ ችግሮች ላይ ዘገባ ያለማቅረብ የአፍሪካ ወንጀለኛ መሪዎች ስህተት ነው፡፡ በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሬፑብሊክ፣ ሩዋንዳ፣ ቡሩንዲ፣ የመካከለኛው አፍሪካ፣ ሶማሊያ፣ ዩጋንዳ፣ ሴራሊዮን፣ ኮትዲቯር፣ ዚምባብዌ፣ ቻድ፣ ሱዳን፣ እና ደቡብ ሱዳን በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩ ህጻናት በየዓመቱ በአማጺያን፣ ሚሊሻ እና የመንግስት ኃይሎች ህጻናቱ ወታደር እንዲሆኑ ያስገድዳሉ፡፡ በገጠር የሚኖሩ የአፍሪካ ህጻናት ከቦታ ቦታ በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ ወይም ደግሞ ወደ ት/ቤት ሲሄዱ እና ሲመለሱ፣ ለዕለት ጉርሳቸው ሲባዝኑ እና ከሚኖሩበት ካምፕ እንኳ ሳይቀር አሁንም ከየቤታቸው የመታፈናቸው ሁኔታ እንደቀጠለ ነው፡፡ በ10 ዓመት እድሜ ህጻናት ወንዶች እንደወጣት የጦር መሳሪያዎችን መፍታት እና በመግጠም ከእራሳቸው የበለጠ የጦር መሳሪያ ይሸከማሉ፡፡ በዚህም መሰረት ህጻናቱ ሁልጊዜ ይደበደባሉ፣ እናም በሰው ልጆች ላይ የጦር ወንጀል ማለትም ግድያ፣ አስገድዶ መድፈር፣ ማሰቃየት፣ አካለጎደሎ ማድረግ፣ እና ሌሎች ለመናገር የሚዘገንኑ ወንጀሎችን እንዲሰሩ ይገደዳሉ፡፡ የተጠለፉ ልጃገረዶች ሁልጊዜ ይደፈራሉ፣ የስሜት ማርኪያና እንዲሆኑም የቤት ውስጥ ስራዎችን እንዲሰሩ ይገደዳሉ፡፡
ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሬፑብሊክ ዉጤቱ ምን ሊሆን እንደሚችል የማይታወቅ ከዓለም ከፍተኛ የሆነ የኅጻናት ወታደር አላት፡፡ በኡጋንዳ የሎርድስ ሬዝንታንሰ እየተባለ የሚጠራው የአማጺያን ኃይል በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ወንወዶች ልጆችን ለውትድርና እና ልጃገረዶችን ደግሞ በአስገድዶ መድፈር የወሲብ ባሪያ አድርጓቸዋል፡፡ በአስቸጋሪነቱ የሚታወቀው የአገሪቱ መሪ የነበረው ጆሴፍ ኮኒ በሰው ልጆች ላይ በፈጸመው የጠለፋ ወንጀል ምክንያት በዓለም ዓቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት አቃቤ ህግ ክስ ተመስርቶበታል፡፡ ሌሎች ጥቂቶች ደግሞ በህጻናቱ ላይ በፈጸሟቸው ወንጀሎች ምክንያት ተጠያቂ ሆነዋል፡፡ በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሬፑበሊክ ጦረኛ ቶማስ ሉባንጋ ዲሎ የተባለው ህጻናትን አስገድዶ ለጦርነት በመመልመል ብቸኛው ተጠርጣሪ እና በዓለም የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ክስ የተመሰረተበት ጦረኛ ነው፡፡
የህጻናት ጉልበት ብዝበዛ፤
ብዙዎቹ የአፍሪካ መንግስታት የህጻናትን ጉልበት ብዝበዛ ለመዋጋት እና ለማቆም ያለመቻል ሌላው የሞራል ስብዕናቸው ውድቀት መገለጫ ነው፡፡ የህጻናት ጉልበት ብዝበዛ “የህጻናትን ደህንነት የሚጎዳ ወይም ደግሞ ከትምህርት ገበታ እንዲታቀቡ የሚያደርግ ሁኔታ ነው፡፡“ በ5 እና በ17 ዓመታት የዕድሜ ክልል መካከል የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የአፍሪካ ህጻናት በአሁኑ ጊዜ ሰብአዊነት በጎደለው መልኩ እና በአገር አቀፍ እና በዓለም አቀፋዊ ደረጃ ህገወጥነትን ባካተተ ሁኔታ በዝባዥ ወይም ደግሞ በአስቸጋሪ የስራ ሁኔታ ተይዘው ይገኛሉ፡፡ በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሬፑብሊክ ዕድሚያቸው ከ15 ዓመታት በታች የሆኑ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ህጻነት ስግብግቦቹን የቻይና ኩባንያዎች ፍላጎት ለማርካት ሲባል በመዳብ፣ ኮባልት፣ እና ሌሎች ውድ ማዕድናት ፍለጋ አስቀያሚ የሆነ የጉልበት ብዝበዛ ይካሄድባቸዋል፡፡ የተባበሩት መንግስታት አገራዊ ዘገባዎች እንደሚያስረዳው ዕድሚያቸው ከ5 እስከ 1 ዓመት የሆናቸው አንድ ሶስተኛ የሚሆኑት ሁሉም የኬንያ ህጻናት በህጻናት የጉልበት ብዝበዛ ተግባራት ላይ ተይዘው ይገኛሉ፡፡ በናይጀሪያ ከ14 ዓመት ዕድሜ በታች የሆኑ ወደ 20 ሚሊዮን የሚገመቱ ህጻናት በጣም አስቸጋሪ በሆነ እና ለረዥም ሰዓት በሚጠይቅ ስራ ላይ ተጠምደው ይገኛሉ፡፡ እ.ኤ.አ እነደ አሜሪካ የስራ መምሪያ የስራ ጥናት እንዳቀረበው፣
በኢትዮያ ያሉ ህጻናት በግብርናው እና በሌሎች የቤት ውስጥ ስራ በጣም አስቀያሚ በሆነ የጉልበት ብዝበዛ ይፈጸምባቸዋል፡፡ የመረጃ ውሱንነት የገደበ ቢሆንም በጣም አስቀያሚ የሆነ የጉልበት ብዝበዛ በአፕል፣ በቡና፣ በሽንኩርት፣ በሙዝ፣ በአበባዎች እና በስኳር አገዳ ምርቶች በጣም አስከፊ የሆነ የጉልበት ብዝበዛ አለ፡፡ በግብርና ላይ የሚሰሩ አደገኛ የሆኑ መሳሪያዎችን ይጠቀማሉ፣ ከባድ ሸክም ይሸከማሉ፣ እንዲሁም ጎጂ የሆኑ ጸረ ተባዮችን ይጠቀማሉ፡፡ እንስሶችን የሚጠብቁ ህጻናት በርካታ ጉዳቶች ማለትም የመነከስ፣ በኃይል የመገፍተር፣ ወይም የመወጋት አደጋ ይደርስባቸዋል፡፡ ህጻናት በተለይም በቤት ውስጥ የሚሰሩ ልጃገረዶች ለአስገድዶ መደፈር ወይም ደግሞ ለሌላ የጥቃት ሰለባ ይሆናሉ፡፡ በኢትዮጵያ የህጻናት ማደጎን በመተግበር ህጻናቱ በልዩ ልዩ የአዕምሮ በሽታ እንዲሰቃዩ ያደርጋል፡፡ የማገዶ እንጨት የሚሰበስቡ እና ውኃ የሚያመላልሱ ከባድ ሽክም ተሸክመው ብዙ ርቀቶችን እንዲጓዙ ይገደዳሉ፡፡
የማይታዩ ህጻናት፤
በኤች አይቪ ኤይድስ ወላጅ የለሽ የሆኑ፣ የኃይል ጥቃት የሚፈጸምባቸው፣ የሚፈናቀሉ እና በጦርነት ጉዳት የሚደርስባቸው በሚሊዮን የሚቆጠሩ የአፍሪካ የማይታዩ ህጻናት አሉ፡፡ በጨነገፉ የአፍሪካ አገሮች መሪዎች የተረሱ ናቸው፡፡ እነዚህ ህጻናት በውስጥ የተፈናቀሉ ወይም ደግሞ በተፋፈገ ሁኔታ በጥገኝነት የሚኖሩ፣ ንጽህናው ባልተጠበቀ እና በሽታን ባዘለ መልኩ ህይወትን በመግፋት ላይ ይገኛሉ፡፡ በወሮበላ ወንጀለኞች በመጠለያ ካምፖች እና በሌሎች ምክንያቶች ብዙውን ጊዜ ሰለባ ላይ እንዲወድቁ ይሆናል፡፡ በተለይ በመጠለያ ካምፖች ያሉ ህጻናት ለጾታ እና ለሌሎች መሰል ጥቃቶች የተጋለጡ ናቸው፡፡ አብዛኞቹ የተፈናቀሉ እና በመጠለያ ካምፖች ውስጥ ያሉ ህጻናት በስነ ልቦና ችግር ማለትም የአዕምሮ ጭንቀት፣ ድብርት፣ ከማህበራዊ ግንኙነት መገለል፣ እና አጠቃላይ የአዕምሮ መታወክ ችግር ሊገጥማቸው ይችላል፡፡
የህጻናት ምግብ እጥረት፣
የሰብ ሰሀራ አፍሪካ አገሮች ከዓለም ከፍተኛ የሆነ የምግብ እጥረት የሚታይባቸው ናቸው፡፡ አስከፊ የምግብ እጥረት አንዳንድ ጊዜም “ድብቅ ረሀብ“ እየተባለ የሚጠራው ህጻናቱ የሚወስዷቸው ንጥረ ነገሮች (ስብ፣ ፕሮቲን፣ ቫይታሚኖች እና ማዕድኖች፣ ወዘተ) የህጻናቱ ሰውነት ከሚፈልገው በታች የሚቀርቡ ናቸው፡፡ በአስከፊ የምግብ እጥረት የተጎዱ ህጻናት በአዕምሮም ሆነ በአካል የኮሰሱ እና በቀላሉ በበሽታ የሚጎዱ ልጆች ናቸው፡፡
በኢትዮጵያ ህጻነት በተመጣጠነ ምግብ እጦት የተጎዱ ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ በ2013 በአፍሪካ ህብረት እና በኔፓድ ዕቅድ እና አስተባባሪ ኤጀንሲ፣ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን እና በተባበሩት መንግስታት የምግብ ፕሮግራም በጋራ በተደረገ ጥናት “በኢትዮጵያ ከአምስት ህጻናት ሁለቱ በእድገት መቀጨጭ የሚጠቁ ናቸው“፡፡ ይህም ሊከሰት የሚችለው ህጻናቱ ወሳኝ የሆኑ ንጥረ ነገሮችን በማህጸን ላይ እያሉ ወይም ደግሞ በመጀመሪያዎቹ 5 ዓመታት ጊዜ ውስጥ ሳያገኙ ሲቀሩ ነው፡፡ 81 በመቶ የሚሆኑት የህጻናት የምግብ እጥረት እና ከዚህ ጋር ተያይዘው የሚከሰቱ በሽታዎች ህክምና አይደረግላቸውም፣ በኢትዮጵያ 28 በመቶ የህጻናት ሞት በምግብ እጥረት የሚመጣ ነው፣ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 16 በመቶ ደጋሚዎች ከእድገት መቀጨጭ ጋር የተያያዙ ናቸው፡፡ ከምግብ እጥረት ጋር በተያያዘ መልኩ በሚከሰተው የህጻናት ሞት ምክንያት የስራ ኃይሉን በ8 በመቶ ቀንሶታል፡፡ በኢትዮጵያ 67 በመቶ የሚሆነው ጎልማሳው ትውልድ በህጻንነት ጊዜው በእድገት መቀጨጭ የተጎዳ ነው፡፡ በህጻናት ያልተመጣጠነ ምግብ እጥረት ምክንያት በየዓመቱ 55.5 ቢሊዮን ብር ማለትም 16.5% የሚሆነውን የአገሪቱን ጠቅላላ ሀብት የሚሸፍን ገንዘብ ይባክናል፡፡ የእድገት መቀጨጭን ማስወገድ የእድገት እና ትራንስፎርሜሽን አስፈላጊው ደረጃ ነው፡፡”
በዚህ ጥናት መቅድም ላይ አምሃ ከበደ “የኢትዮጵያ የጤና እና ስነምግብ ምርምር“ ከቢሮክራሲያዊ አካሄድ በወጣ መልኩ የሚከተለውን ጠቁመዋል፣ “የኢትዮጵያ መንግስት የእድገት እና ትራንስፎርሜሽን እቅዱን በሚተገብርበት ጊዜ የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን የማስወገድን ጠቃሚነት ማጉላት አለብን“፡፡
የስብዕና ድህነትን ወይም የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት እና ተራንስፎርሜሽን እቅድ መጋረጃን መቅደድ፣
የአፍሪካ መሪዎች፣ የእነርሱ ከፍተኛ ተከፋዮች እና ከመጠን በላይ የድህነት ወትዋቾች እና አዕምሮ የሌላቸው የብዙህን መገናኛ አስመሳይ ጋዜጠኞች አፍሪካ በመነሳት ላይ እንደሆነች እና አስገራሚ በሆነ መልኩ ተሀድሶ እና ልማትን እያካሄደች እንደሆነች እንድናምን ጥረት ያደርጋሉ፡፡ አፍሪካ የኢኮኖሚ እድገት አስመዝግባለች፣ ተሀድሶ እና ተራንስፎርሜሽን እያካሄደች ነው የሚለው የማስመሰያ ንግግር እና ስለአፍሪካ መተረት የውሸት ተረት ነው፡፡ አፍሪካ በአምራች ኢንዱስትሪዎቿ፣ ዓለም አቀፍ ንግድ እና ቱሪዝም አማካይነት በብዙ ቢሊዮን የሚቆጠር የውጭ ምንዛሬ ታገኛለች፡፡ አፍሪካ ለኢንቨስትመንት ዋና ቦታ ናት ብለው ያምናሉ፡፡ ጠቅላላ የሀገር ሀብት መጣኔ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ነው ይላሉ፣ የነፍስወከፍ ገቢ በእጥፍ እና ሶስት ጊዜ እጥፍ እያደገ ነው፣ ድህነት እየከሰመ ነው እናም የአፍሪካ መካከለኛ ገቢ ያለው የህብረተሰብ ክፍል እያደገ ነው ይላሉ፡፡ አፍሪካ በአሁኑ ጊዜ ከመቸውም ጊዜ በላይ ብዙ ሚሊየነሮች እና ቢሊየነሮች አሏት፡፡ አፍሪካውያን/ት በተንቀሳቃሽ ስልክ እና በሌሎች የመገናኛ ቴክኖሎጂዎች የተገናኘች ናት፡፡ ብልህ ያልሆኑ የአፍሪካ የጨነገፉ መንግስታት መሪዎች አፍሪካ በአንድ ተኩል አስርት ዓመታት ጊዜ ውስጥ የመካከለኛ ጊቢ ያላቸውን የዓለም አገሮች ትቀላቀላለች የሚል ተስፋ አላቸው፡፡
ሆኖም ግን በድህነት ወትዋቾች እና በዓለም አቀፍ የጨነገፉ መንግስታት መሪዎች መገናኛ ብዙሀን ማስመሰያ ጀርባ አንድ መሰረታዊ የሆነ ስህተት አለ፡፡ የእነርሱ ተረት ተራኪዎች ሁልጊዜ ስር የሰደደውን ሙስና ትኩረት ባለመስጠት ያናንቃሉ፣ ትልቁን የተቆለለ እዳ እና የጨነገፉ የአፍሪካ መንግስታት ለምዕራቡ ዓለም የእርዳታ እና ብድር ተቋማት ያጎበድዳሉ፡፡ ትንሽ አበጥ ላለችዋ ነገር ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ኃይል ጊዚያዊ ችግር እንደሆነች አድርገው የማስመሰል ስራ ይሰራሉ፡፡ የግብርና ምርቶችን፣ ጥሬ እቃዎችን፣ ብረት እና ማዕድናትን ወደ ውጭ በመላክ አፍሪካ ከድህነት ትወጣለች በማለት የአፍሪካ ህዝቦችን ይዋሻሉ፡፡
ስለሆነም በእንቁዎቹ በአፍሪካ ወጣቶች መሰረት ያልተገነባውን የእድገት እና የትራንስፎርሜሽን እቅድ ማን ጉዳይ ሊለው ይችላል? አፍሪካ ልጆቿ በአስከፊ ሁኔታ በምግብ እጦት እየተሰቃዩ፣ ደካማ የትምህርት አቅርቦት እየተተገበረ፣ ዝቅተኛው የደህንነት ሁኔታ ባልተሟላበት ሁኔታ፣ በስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ዜጎች ተረስተው በሚቀሩበት ሁኔታ እና ለሁሉም ዓይነት ኃይል እና የመብት ረገጣ በተጋለጠበት ሁኔታ ማንም በእውነተኝነት አፍሪካ አድጋለች ብሎ መከራከር ይቻለዋልን! እንደዴትስ ነው አፍሪካን ከድህነት አራንቋ መንጥቆ በማውጣት ወደ ብልጽግና ተራራ ለማውጣት የሚቻለው? በእርግጠኝነት የወደቁት እና የስብእና ዝቅጠት ያለባቸው የወደቀችዋ የአፍሪካ መንግስታት መሪዎች አያደርጉትም!
በወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ከፍተኛ የሆነ መዋለ ንዋይ ካልተመደበ አፍሪካ ልታድግ አትችልም፣ ይልቁንም ትወድቃለች፣ ወድቃለችም፡፡ የአፍሪካውያንን/ትን ፍላጎት በመገደብ ተሀድሶ ማምጣት ከቶውንም አይቻልም፡፡ ከልጆች ጠንካራ ትከሻ እና ክንፍ በስተቀር አፍሪካ ከድህነት አራንቋ ልትወጣ አትችልም፣ አፍሪካ በድህነት ወጥመድ ውስጥ ተተብትባ ትቀጥላለች፣ እናም በእዳ ማጥ፣ በገንዘብ ክፍተት፣ በርሀብ፣ በእጥረት፣ በሙስና፣ በኋቀርነት እና በልመና ተቀይዳ ትቀራለች፡፡
ሆኖም ግን ወደፊት ስናይ ለአፍሪካ ወጣቶችዋ ወሳኝ ናቸው ነው፡፡ በሞይ ኢብራሂም ፋውንዴሽን እንደተጠቃለለው በሚቀጥሉት ሶስት ተከታታይ ትውልዶች 41 በመቶ የሚሆነው የአፍሪካ ህዝብ ወጣት ይሆናል፡፡ አፍሪካ በወጣት ኃይል እድገት ብቸኛዋ አህጉር ትሆናለች፡፡ ምዕራብ አውሮፓ በህዝብ ብዛት እየቀነሰ ይሄዳል፣ ላቲን አሜሪካ እና ኤሽያ የተመጣጠነ የህዝብ እድገትን ይይዛሉ፡፡ ያ ዘገባ አፍሪካ እ.ኤ.አ በ2040 የአፍሪካ ሰራተኛ ህዝብ ቁጥር ከቻይና ወይም ህንድ የሚበልጥ ይሆናል፡፡ እ.ኤ.አ በ2050 የአፍሪካ ሰራተኛ ህዝብ ቁጥር ቢያንስ ከአውሮፓ 3 ጊዜ እጥፍ በመብለጥ የዓለምን ህዝብ ሶስት አራተኛ የሚይዝ ይሆናል፡፡ ቁጥር ብቻውን ምንም ማለት አይደለም፣ ነገር ግን የአፍሪካ ወጣቶች በዓለም ገበያ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ግዛት፣ መንግስታት እና ገዥዎች ካላመቻቹላቸው ማሰብ ብቻውን የሚፈይደው ነገር አይኖርም፡፡
የአፍሪካ ወጣቶች በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ ካልሆኑ በስተቀር ቀጥር ብቻውን የሚፈይደው ነገር ለመኖሩ ምን ማረጋገጫ አለ? “ለወደፊቱ ውድ የሆነውን የወጣት ህብታችንን እንዴት ነው ልንፈጥረው የምንችለው?” በማለት የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን ዘገባ ጥያቄ ያቀርባል፡፡ እኔ በበኩሌም ስብዕናቸው ለዘቀጠው የአፍሪካ መሪዎች ተመሳሳይ ጥያቄ አቀርባለሁ፡፡
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
ሀምሌ 5 ቀን 2006 ዓ.ም
ፍርድ ቤቱ በእነ ሐብታሙ ጉዳይ ጠንከር ያለ ትዕዛዝ አስተላለፈ – ከዳዊት ሰለሞን
የዛሬ ሳምንት ማክሰኞ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ የተደረጉት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ህገ መንግስቱና የጸረ ሸብር አዋጁ በሚያዙት መሰረት እጃቸው ከተያዘበት አንስቶ በ48 ሰዓት ውስጥ ፍርድ ቤት መቅረብ እንደሚገባቸውና በቤተሰቦቻችውና በጠበቃቸው መጉብኘት መብታቸው መሆኑን ከግምት በማስገባት ጠበቆቻቸው ያልተሟሉላቸው መብቶች በፍርድ ቤት ጣልቃ ገብነት ይከበሩ ዘንድ በዛሬው ዕለት ክስ መስርተው የማዕከላዊ አመራሮች ለቀረበባቸው ክስ በአካል በመገኘት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
ሃላፊዎቹ ለፍርድ ቤቱ በሰጡት ምላሽ ሰዎቹን ፍርድ ቤት በ2/11/2006 ዓ.ም ማቅረባቸውን ጠቅሰዋል፡፡የታሳሪዎቹ ጠበቆች የሆኑት ጠበቃ ተማም አባቡልጉና አቶ ገበየሁ ደምበኞቻቸውን ማግኘት አለመቻላቸውን ፍርድ ቤት ሲቀርቡም እንዲያውቁ አለመደረጋቸውን አስረድተዋል፡፡ጠበቆቹ ደምበኞቻቸውን ማየት እንዲፈቀድላቸውና በቤተሰቦቻቸውም እንዲጎበኙ እንዲደረግ ትዕዛዝ እንዲሰጥ አቤት ብለዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ ግራ ቀኙን ካደመጠ በኋላ ታሳሪዎቹ በቤተሰቦቻቸው እንዲጎበኙ እንዲደረግና ከጠበቆቻቸው እንዲመካከሩ ይደረግ ሲል ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ፍርድ ቤቱ ከዚሀ በተጨማሪም በማዕከላዊ እንደሚገኙ የተነገረላቸውን ታሳሪዎች የፊታችን አረብ 4፡00 እንዲቀርቡ ሲል አዟል፡፡የማዕከላዊ ኃላፊም በፍር ቤቱ የተሰጠውን ትዕዛዝ መፈጸሙን እንደሚከታተሉ ተናግረዋል፡፡