Quantcast
Channel: Amharic News & Opinion
Viewing all 13695 articles
Browse latest View live

ዶ/ር ሽፈራው ተ/ማርያም በስደተኛው ሲኖዶስና በማህበረ ቅዱሳን ያሉ ምእመናንን የግንቦት 7 ከበሮ መቺ አሏቸው

$
0
0

የፌደራል ጉዳዮች ሚ/ር ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም ከሰሞኑ መንግስት በአዲስ አበባ በጠራው ጽንፈኝነትን እና አክራሪነትን የሚኮንን ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር በስደተኛው ሲኖዶስና በማህበረ ቅዱሳን ውስጥ መሽገዋል ያሏቸውን ምእመናን የግንቦት 7 ከበሮ መቺ ሲሉ መናገራቸውን ሐራ ተዋሕዶ ዘገበ። ከዚህ ቀደም በሕይወት የሌሎት ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ ማህበረ ቅዱሳንን አክራሪ ሲሉ በፓርላማ መናገራቸውን ያስታወሱ ምእመናን የሚ/ሩ ንግግር እንዳስቆጣቸው ለመረዳት ተችሏል። የሐራ ተዋሕዶ ዘገባ እንደወረደ ይኸው፦

‹‹በስደተኛው ሲኖዶስ የተሸፈኑና በማኅበረ ቅዱሳን የመሸጉ የትምክህት ኀይሎች የግንቦት ሰባትን ከበሮ ሲመቱ ከርመዋል››

የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ባዘጋጁትና ከነሐሴ ፳፩ – ፳፫ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም በተካሄደው ‹‹አገር አቀፍ የሰላም እሴት ማጎልበቻ ጉባኤ›› ውይይት ከተካሄደባቸው ጽሑፎች መካከል የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሽፈራው ተክለ ማርያም ‹‹የአክራሪነት/ጽንፈኝነት ዝንባሌዎችና መፍትሔዎቻቸው›› በሚል ርእስ ያቀረቡት ጽሑፍ ይገኝበታል፡፡

dr shiferaw tekelamariam

በሰባት ንኡሳን አርእስት ተከፋፍሎ በስፋት የቀረበው ጽሑፋቸው÷ አክራሪነትና ጽንፈኝነት ከሕገ መንግሥት አንጻር እንዴት እንደሚታይ፣ በአገራችን ይታያሉ ያሏቸውን የአክራሪነትና ጽንፈኝነት ዝንባሌዎች፣ አክራሪነትን/ጽንፈኝነትን የማስፋፊያ ስልቶችን፣ የአክራሪ/ጽንፈኛ ኃይሎች መነሻና መድረሻ ምስጢር፣ ሃይማኖትን ሽፋን ስላደረጉ የአክራሪነት አደጋዎች እና አክራሪነትን/ጽንፈኝነትን በአስተማማኝ ደረጃ ለማሸነፍ መሠራት ይገባቸዋል ያሏቸው ስድስት የመፍትሔ ሐሳቦች የተካተቱበት ነው፡፡

በሚኒስትሩ ጽሑፍ አክራሪነት/ጽንፈኝነት የሚለው ቃል የተበየነው በሦስት መንገዶች ነው፡፡ ይኸውም አክራሪነት/ጽንፈኝነት÷ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ ፳፯ ንኡስ አንቀጽ ፫ ዜጎች የፈለጉትን እምነት የመከተል መብት እንዳላቸው የተደነገገውን በመተላለፍ የሃይማኖትና እምነት ነጻነትን በተግባር ለመናድ መንቀሳቀስ ነው፡፡ የሕገ መንግሥቱ አንቀጽ ፳፭ ስለ እኩልነት መብት በሚደነግጋቸው ንኡሳን አንቀጾች በሃይማኖቶች መካከል የማበላለጥ ጉዳይ እንደማይኖር የተቀመጠውን ድንጋጌ በመጣስ የሃይማኖት እኩልነትን በተግባር ለመናድ መንቀሳቀስ ነው፤ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ ፲፩ ስለ መንግሥትና ሃይማኖት መለያየት በግልጽ የተቀመጠውን ድንጋጌ በመፃረር መንግሥታዊ ሃይማኖት ወይም ሃይማኖታዊ መንግሥት ለመመሥረት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ነው፡፡

አክራሪው/ጽንፈኛው ኃይል ደረጃው ይለያይ እንጂ በሁሉም ሃይማኖቶች ሽፋን እንደሚንቀሳቀስ የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ዓለም አቀፋዊና ከባቢያዊ ገጽታም ያለውና የሚመጋገብ እንደኾነ ያስረዳሉ፡፡ ስለዚህ እኔን የሚመለከተኝ አይደለም የሚል ሃይማኖትና አገር ይኖራል ተብሎ እንደማይታሰብ፣ እንደየአገሩ የሕዝቦች በሰላም አብሮ የመኖር ታሪክ፣ ከድህነትና ኋላቀርነት ተጋላጭነት የመላቀቅ፣ የሕገ መንግሥታዊ ሥርዐት የብዝሃነት አያያዝ ጥበቃ ዋስትና ሊለያይ እንደሚችል ይናገራሉ፡፡

በአገራችን በሁሉም ሃይማኖቶች (በኦርቶዶክስ ሃይማኖት ሽፋን፣ በእስልምና ሃይማኖት ሽፋንና በፕሮቴስታንት ሃይማኖት ሽፋን) የአክራሪነትና ጽንፈኝነት አስተሳሰብና ተግባር አራማጆች ከሃይማኖቱ መሪዎች ያልተላኩና መነሻቸውም መድረሻቸውም ሃይማኖታዊ ሳይኾን ፖሊቲካዊ መኾኑን ይጠቁማሉ፡፡

ከዚህ በታች ሚኒስትሩ ‹‹በኦርቶዶክስ ሃይማኖት ሽፋን›› ይታያል ለሚሉት ‹‹የአክራሪነት እና ጽንፈኝነት አስተሳሰብና ተግባር›› በማብራሪያነት የሰጡት ገለጻ ለሐራውያን ቀጥተኛ መረጃና ማገናዘቢያ ይኾን ዘንድ በጽሑፋቸው በሰፈረበት ይዘቱ ቀርቧል፡፡

* * *

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በንጉሡ ዘመን የመንግሥት ሃይማኖት እንደኾነች በ1948 ዓ.ም. ሕገ መንግሥት የተደነገገና እስከ ንጉሡ ሥርዐት መውደቅ ድረስ የቀጠለ እንደኾነ ይታወቃል፡፡ በዚያን ዘመን ንጉሡና የገዥ መደቡ አካላት ለሥልጣን ማራዘሚያ፣ የጥቅም ማካበቻና የሌሎች እምነት ተከታዮችን በማሸማቀቅ አንድ አገርና አንድ ሃይማኖት ፍልስፍና ለማራመድ ተጠቅመዋል፡፡

በሌላ በኩል ግን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንግሥት ሃይማኖት ገጽታ የተላበሰች ብትኾንም የውስጥ ነጻነት አልነበራትም፡፡ የጳጳሳትና የዲያቆናት ሹመት ሳይቀር በመንግሥት የሚወሰንና የሚጸድቅ ስለነበር መንፈሳዊም ይኹን አስተዳደራዊ ነጻነት ያልነበራት ነበረች፡፡ በሌላ በኩል የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይ ከገዥዎች አስተሳሰብ በተለየ ኹኔታ ከሌሎች ሃይማኖት ተከታዮች ጋራ አብሮ በሰላም በመኖር የሺሕ ዓመታት ታሪክ የነበረው እንደኾነ ደጋግመን አውስተናል፡፡

ይህ እንደተጠበቀ ኾኖ በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት የተረጋገጠው የሃይማኖት/እምነት ነጻነት፣ የሃይማኖቶች እኩልነት እና መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው የሚለው መርሕ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ክብርና ሞገስ፣ ታሪክና ጥቅም የነፈገ አድርገው የሚያስተጋቡ ግለሰቦችና ቡድኖች አሉ፡፡ እነዚህ ግለሰቦችና ቡድኖች የሃይማኖት/እምነት ነጻነትን፣ የሃይማኖት እኩልነትን፣ መንግሥታዊ ሃይማኖትም ይኹን ሃይማኖታዊ መንግሥት እንደማይኖር የተቀመጡ ድንጋጌዎችን ይጥሳሉ፡፡

ከሃይማኖት/እምነት ነጻነት አኳያ ሲታይ የሌላውን እምነት ትክክል ነው ብሎ ለመውሰድ ማንም እንደማይገደድ ቢታወቅም የሌላውን ሃይማኖት የተለያዩ ስያሜዎችን እየሰጡ የማብጠልጠልና የማሳነስ አመለካከትና ተግባራዊ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ግለሰቦችና ቡድኖች ይታያሉ፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ከሌሎች ሃይማኖት ጋራ እኩል ተደርጎ ሊወሰድ አይገባም፤ ይኽም ክብሯንና ታሪኳን የሚጎዳ ነው በሚል ይንቀሳቀሳሉ፡፡ እንደማሳያም የአማኝ ቁጥራችን ብዙ ነው፤ ታሪካችን ረዥም ነው በሚል ለመከራከር ይሞክራሉ፡፡

ሃይማኖቶች እኩል ናቸው በሚል የተቀመጠው ድንጋጌ የአማኝ ቁጥርንና የሃይማኖቶችን ታሪክ የሚደፈጥጥ ሳይኾን የአገራችን ሕዝቦች እንደ ዜጋ በነጻ ፍላጎታቸውና ምርጫቸው የያዙት አመለካከት – ሃይማኖትና እምነት ከሌላኛው እንደማይበልጥና እንደማያንስ ብሎም ሁሉም ዜጎች የዴሞክራሲያዊ መብት ተጠቃሚ መኾናቸውን ለማረጋገጥ ነው፡፡ ይህን ሕገ መንግሥታዊ መርሕ ዐውቀው በመጣስ በዙሪያው የትምክህት ኀይሎች የሚሰበሰቡበት ገጽታም የሚታይበት ኹኔታ አለ፡፡

በኦርቶዶክስ ሃይማኖት ሽፋን ከሚካሄዱት ቅስቀሳዎች ‹‹የበላይነትን አጥተናል፤ ይህንኑ መመለስ ይገባናል›› የሚል ሕገ መንግሥታችን የሻረውን አስተሳሰብ የሚደግፍ ነው፡፡ በዚህ ረገድ ‹‹ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ነች››፤ ‹‹አንድ አገር አንድ ሃይማኖት›› ወዘተ. . . ጉዳዮችን በማቅረብ በአንድ በኩል የአገራችንን የሃይማኖት ብዝሃነት የሚፃረር በሌላ በኩል ደግሞ አገራችን የሃይማኖቶች ብዝሃነት ነባራዊ መገለጫዋ መኾኗን የሚቃወም አካሄድ ነው፡፡

በሃይማኖት ሽፋን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት መንግሥታዊ ሃይማኖት መኾን ይገባዋል በሚል አቋራጭ የፖሊቲካ መሣርያ ለማድረግም የሚንቀሳቀሱ አካላት ይታያሉ፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖትን ሽፋን ያደረገ የአክራሪነትና ጽንፈኝነት እንቅስቃሴ በዋናነት የሚታየው በተለያዩ የማኅበራት አደረጃጀት ውስጥ ራሳቸውን ደብቀው በሚሠሩ ግለሰቦችና ቡድኖች ነው፡፡ በእነዚህ ማኅበራት ውስጥ የመሸጉ አክራሪ ግለሰቦችና ቡድኖች በሚያሰራጭዋቸው የተለያዩ የኅትመት፣ የኤሌክትሮኒክስና የድረ ገጽ ውጤቶች በተከታታይ ሃይማኖትን ከሃይማኖት፣ ሕዝብን ከሕዝብ፣ ሕዝብንና መንግሥትን የሚያጋጩ ዘገባዎችን በማስተጋባት የኢፌዴሪ መንግሥት የኦርቶዶክስ ክርስትናን ያሳነሰና ተገቢውን ክብርና ጥቅም የነፈጋት አድርገው ለምእመናን ያቀርባሉ፡፡

መንግሥት የሚያካሂዳቸው የልማት ሥራዎች መንግሥት የሚያሳያቸውን የገለልተኝነት ሚና. . .ወዘተ መንግሥት በሃይማኖታችን ጣልቃ ገብቷል በሚል ገሃድ ፍላጎትና ድብቅ አሠራር ካላቸው የውጭ ቡድኖች ጋራ በማበር ሰላምን አደጋ ውስጥ የማስገባትና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱን በሃይማኖት ሽፋን ለመናድ ይንቀሳቀሳሉ፡፡ በቅርቡ በነበረው የፓትርያርክ ምርጫና በዋልድባ ገዳም ዙሪያ የተፈጠረው ዝንባሌ የነዚህ ፍላጎቶች ጉልሕ ማሳያ ነው፡፡

* * *

የአክራሪው/ጽንፈኛው ኃይል የማስፋፋት ስልቶች

የሃይማኖት ተቋማቱን የአመራር ዕርከኖች መቆጣጠር
አክራሪነትና ጽንፈኝነትን ለማስፋፋት ከሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች አንዱ በሃይማኖት ተቋማትም ይኹን በመንግሥት መዋቅር ሰርጎ በመግባትና ደጋፊ በመምሰል በድብቅ መሠረቱንና መረቡን ማስፋፋት ነው፡፡ ይህን መሠረት የማስፋፋትና መረብ የመዘርጋት ተግባር ውጤታማ በኾነና በአጭር ጊዜ ማከናወን የሚቻለው የመንግሥትንም ይኹን የሃይማኖቶች አደረጃጀቶችን በበቂ ደረጃ መቆጣጠር ከተቻለ ነው፡፡

በእስልምናም ይኹን በክርስትና ሃይማኖቶች ሽፋን የሚካሄደው የአክራሪነት/ጽንፈኝነት እንቅስቃሴ በዋናነት እያነጣጠረ የሚገኘው የተቋማቱን የበላይ አመራር ዕርከኖች መቆጣጠር ነው፡፡ ለዚህ ጥሩ ማሳያ የሚኾነው በቅርቡ በተካሄደው የእስልምና ምክር ቤቶች ምርጫ ወቅት ለአክራሪው ኀይል ለራሱ በሚበጅ መንገድ ካልኾነ ምርጫው ትክክለኛ አይደለም በሚል የዑላማ ምክር ቤት ፋትዋ ጭምር በመቃወም ያደረገው ሙከራ ነው፡፡

ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራዊ ኾኖ ከ8 ሚልዮን በላይ ሕዝበ ሙስሊም ወጥቶ የፈለገውን አመራር ከመረጠ በኋላ እስከ ፍርድ ቤት የሚሄድ ክሥ የመመሥረት፣ ሕዝበ ሙስሊሙ በራሱ ነጻ ፍላጎት መርጦ ያቋቋመውን መሪ ተቋም ማብጠልጠል የሚታይ የዘወትር ክሥተት አድርገዋል፡፡ አክራሪው ኀይል ‹‹የራሴ ብቻ ካልኾነ›› የሚለውን አመለካከት በግልጽ ያመላከተ ሂደት ነበር ለማለት ይቻላል፡፡ ከምርጫ ሂደቱም በኋላ ከቀበሌ ጀምሮ የተመረጡ አመራሮችን በየዕርከኑ የራሱ ለማድረግ የሌት ተቀን ሥራውን በተለያዩ መደለያዎችና ማስፈራሪያዎች እየሠራ መኾኑ በግልጽ የሚታወቅ ነው፡፡

በኦርቶዶክስ ሃይማኖት የ፮ኛው ፓትርያርክ ምርጫ ሲካሄድም በተመሳሳይ እንቅስቃሴዎች ከአገር ውስጥና ከአገር ውጭ ተስተውለው እንደነበር ይታወቃል፡፡ የሚሾመው ፓትርያርክ ጉዳይ የራሱ የአማኙ መኾኑ እየታወቀና ራሱ ሲኖዶሱ አስመራጭ አካል ሠይሞ ከየሀገረ ስብከቱ በውክልና ከ800 በላይ መራጮች እንዲሳተፉ አድርጎ ያካሄደውን ሂደት በማብጠልጠል ‹‹መንግሥት ጣልቃ ገብቷል›› ስለዚህም የፍላጎታችንን መሾም አልቻልንም በሚል ለማስተጋባት ተሞክሯል፡፡

አክራሪው/ጽንፈኛው ኃይል የሃይማኖት ተቋማቱን የአመራር ዕርከኖች መቆጣጠር የሚፈልግበት ምክንያት ሕዝባችንን በተደራጀ መንገድ በበቂ ለማደናገርና ከዚያም ከሕገ መንግሥታዊ ሥርዐታችንና ከሕገ መንግሥት ጋራ ፊት ለፊት ለማፋጠጥ ነው፡፡ ‹‹በሃይማኖትኽ መንግሥት ጣልቃ ገብቷል›› የሚለውን መፈክራቸውን የሁሉም ሕዝብ መፈክር በማድረግ በሕገ መንግሥታችንና በዴሞክራዊ ሥርዐታችን ላይ በተሳሳተ መንገድ ሕዝብን ለማዝመት ነው፡፡ ተቋማዊ ቁመናና ትስስር ተጠቅመው ገንዘቡንም ሕዝቡንም ለአክራሪነት ግባቸው ለማሰለፍ ስለሚመቻቸው ነው፡፡ የሃይማኖቱ ተቆርቋሪ መስለው አክራሪነቱን ለማስፋፋት ምርጥ ዕድል ስለሚኾን ነው፡፡

በተቃራኒው ግን ሕዝበ ሙስሊሙም ይኹን ሕዝበ ክርስቲያኑ ለአፍራሽ ፍላጎት ተገዥ እንዳልኾነ፣ ለሰላምና ልማት የቆመ ሕዝብ መኾኑን ደጋግሞ በተግባር አሳይቷቸዋል፡፡ በእነርሱ እኩይ ዓላማና ፍላጎት እንደማይገዛ፣ ሕገ መንግሥታችንና ዴሞክራሲያዊ ሥርዐትን በኃይል ለመናድ ከሚንቀሳቀሰው ኃይል ጋራ እንደማይተባበር ፊት ለፊት በሰፋፊ ሰላማዊ ሰልፎች ጭምር ነግሯቸዋል፡፡

ስለዚህ አክራሪው ኃይል ቢቻል እነዚህን የአመራር ዕርከኖች ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር ካልተቻለም ደረጃ በደረጃ እየሰረገና አቋሞቻቸውን እየሸረሸረ የራሱ ተቋም ለማድረግ ሰፊ ርብርብ ያደርጋል፡፡ ንጹሓን አማኞች ሁሌም ቢኾን ይህን አደጋ በንቃት በመጠበቅ ከመንግሥት ጋራ ተባብሮ መሥራት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ጉዳዩ ፀረ ሕገ መንግሥት አቋም እንደመኾኑ የሁሉም የሰላምና ልማት ኃይሎች ርብርብ የሚፈልግ ነው፡


ESAT Radio Sep 07

$
0
0
ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

ስለእግራቸው ውጤት (የስንኝ ቋጠሮ ለብሔራዊ ቡድናችን ተጫዋቾች) – ከፋሲል ተካልኝ አደሬ

$
0
0

waliyaa2
ያልከውን አላልኩም..ሰማህ ወይ ወዳጄ?
እንዴት እበላለሁ?..እጄን በገዛ እጄ::

ክብሬን አላቀልም..እንደምን አድርጌ?
እንደሌለ አውቃለሁ..
የቁሳቁስ እንጂ..የጀግና አሮጌ::

መቼም..መቼም..መቼም አልዘነጋ
የናቤን..የማሞን..ክብርና ዋጋ::
እንዳልከው በእግራቸው..በዓለም የነገሱ
ሁሌም የሚኖሩ..በታሪክ ሲወሱ
ሕያው ጀግኖቻችን..መቼም አይረሱ!!!

ሰማህ ወይ ወዳጄ?
ፈለግ ተከትለው..ዛሬ በእግር ኩዋሱ
በፈጸሙት ገድል..ቢንቆለዻዸሱ
በእግራቸው በሠሩት..
ባስመዘገቡት ድል..አገር ስላኮሩ
በክብር ቢነሱ..በክብር ቢጠሩ
ፈጽሞ አልገባኝም..ምንድ ነው ነውሩ?!?

ሰማህ ወይ ወዳጄ?
ስቼ ያሳሳትኩት..
…አልታይህ አለኝ
ስለእግራቸው ውጤት..
እንኩዋንም ደስ አለህ!..
…እንኩዋንም ደስ አለኝ!
* * *

___ ፋሲል ተካልኝ አደሬ ___ —

የአዳማ ሰልፍ ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ተጠናቅቋል!!! ኢቴቪ በአዳማ የሁከት ድራማ በመስራት ለመቅረጽ ያደረገችው ሙከራ ከሸፈ ብራቮ አዳማዊያን! ጉዞ ወደ አዲስ አበባ!

$
0
0

የአዳማ ሰልፍ ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ተጠናቅቋል!!! ኢቴቪ በአዳማ የሁከት ድራማ በመስራት ለመቅረጽ ያደረገችው ሙከራ ከሸፈ ብራቮ አዳማዊያን! ጉዞ ወደ አዲስ አበባ! በጎንደር፣ ደሴ ፣ባህር ዳር፣ጂንካ፣ ወላይታ፣ባሌ ሮቢ፣ ፍቼ፣ አርባ ምንጭ ዛሬ አዳማ ቆይታ በማድረግ የሚልዮኖችን ድምጽ ያሰማው የአንድነት ለዴሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ ህዝባዊ ንቅናቄ ለመስከረም 5/2006 የመስቀል አደባባይ ሰለማዊ ሰልፍ ጓዙን ጠቅልሎ ሸገር ገብቷል፡፡

በዛሬው ዕለት በአዳማ ከተማ በአንድነት የተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ የተጠናቀቀ መሆኑ ታውቋል። የአንድነት ሰላማዊ ሰልፍ የማይቀር መሆኑን የተገነዘቡት የክልል መስተዳድሮች ሰልፉ የሚጀመርበትን አካባቢ በፌደራል አድማ በታኝና በፖሊሶች እንዲከበብ አድርገዋል፡፡ አስገራሚው ነገር ግን ወደ ሰልፉ መጀመሪያ ቦታ እየተመመ የሚገኘው ህዝብ በዙሪያው እየተከናወነ ለሚገኘው ነገር ቁብ ሳይሰጥ የተዘጋጁ መፈክሮችን እይሰማ መንገዱን ቀጥሏል፡፡ የፖሊሶችና የአድማ በታኞቹ ከበባ የህዝቡን ስነ ልቦና በፍርሃት ለመሙላት እንደሆነ የተረዱ የአንድነት አመራሮች በቁርጠኝነት ያለ ምንም ስጋት ህዝቡ እንዲቀላቀላቸው በማበረታት ሕዝቡም የፍርሀትን ጠርሙስ ሰበሮ ሰልፉን በቆራጥነት ተቀላቅሏል። ሆኖም በአዳማ በተደረገው ሰልፍ ላይ ሰላማዊ ሰልፈኞቹ እንቅስቃሴ እንደጀመሩ ፖሊስ ከፊት በማስቆም ‹‹እኔ የደረሰኝ በዋናው መንገድ እንደማትጠቀሙ ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ መንገድ ማለፍ አትችሉም›› ይላል፡፡ በዚህ ና በዚያ መንገድ በማለት በዚህ ሰዓት መከልከል እንደማይችሉ በመጥቀስ ሰልፈኞቹ በመንገዱ ተቃውሟቸውን በማሰማት ቀጥለዋል፡፡

ሌላው አስገራሚ ትዕይንት በአዳማ አንድነት ፓርቲ የጠራውን ሰልፍ ተገን አድርጎ የኦሮሚያ ቴሌቭዥን በአዳማ ሊሰራው የነበረው ድራማ ከወያኔው ኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ጎን ለጎን የተደናቀፈበት መሆኑ ታውቋል:: በዚሁ ሰልፍ ላይ የአንድነት የምዕራብ ቀጠና ሃላፊ አቶ አስናቀ ሸንገማ በኦሮምኛ ቋንቋና ፣የአንድነት የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ አቶ ስዮም መንገሻ ንግግራቸውን ያሰሙ ሲሆን በመጨረሻም ዶክተር ሃይሉ አርአያ ንግግር አድርገዋል፡፡

በአዳማ በteደረገው ሰልፍ ከተደመጡ መፈክሮች መካከል ፤

ውሸት ሰልችቶናል!
የኢቴቪ የሃሰት ዶክመንተሪ ፊልም ከአሸባሪነት አይለይም!
ድህነት በፕሮፓጋንዳ ብዛት አይጠፋም!
ሰብዓዊ ልማት ለሁሉም!
ስራ ማግኘት የዜግነት መብት ነው!
አምባገነኖች ባሉበት የአንዷለም ቤት እስር ቤት ነው!
ርዕዮት አለሙ ጋዜጠኛ እንጂ አሸባሪ አይደለችም!
አንዷለም አራጌ፤ እስክንድር ነጋ፤ ናትናኤል መኮንን፤ ውብሸት ታዬ፤ ርዕዮት አለሙና ሌሎችም በአስቸኳይ ይፈቱ!!!!BToiHt6CYAEyOQo1069404_10151870041599743_631710615_n

አንድነት በአዳማ የጠራው ሰልፍ በሰላም ተጠናቀቀ

$
0
0

udJ Adma

UDJ Dr hailu Areaya(ዘ-ሐበሻ) የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት በሚል በጎንደር፣ ደሴ፣ ባህር ዳር፣ ጂንካ፣ ወላይታ ፣ባሌ ሮቢ፣ ፍቼና አርባ ምንጭ ተካሂዶ የነበረው የአንድነት ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬ ደግሞ በአዳማ ከተማ ተደርጎ በሰላም መጠናቀቁን የፍኖተ ነፃነት ጋዜጠኛ ዳዊት ሰለሞን ከስፍራው ዘገበ። እንደ ጋዜጠኛው ዘገባ በዛሬው የአዳማ ሰላማዊ ሰልፍ መንግስት ፌደራል ፖሊሶችን በማሰማራት፣ የሰልፉን መንገድ በማስቀየርና በኢቲቪ በኩል ድራማ ለማሠራት ቢሞርክም እንዳልተሳካለትና ከምንም በላይ ሰልፉ በሰላም ተጠናቆ ሕዝቡ ድምጹን ከፍ አድርጎ ያሰማበት ነው።
በአዳማ ከተማ በተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ የአንድነት የምዕራብ ቀጠና ሃላፊ አቶ አስናቀ ሸንገማ በኦሮምኛ ቋንቋ፣ የአንድነት የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ አቶ ስዮም መንገሻ እንዲሁም ዶክተር ሃይሉ አርአያ ንግግር ማድረጋቸውን የገለጸው ጋዜጠኛው ስልፈኛው በመፍክሩ መንግስትን የተለያዩ ጥያቄዎችን ጠየቋል፡
ከነዚህም መካከል፦
- ውሸት ሰልችቶናል
- የኢቴቪ የሃሰት ዶክመንተሪ ፊልም ከአሸባሪነት አይለይም
- ድህነት በፕሮፓጋንዳ ብዛት አይጠፋም
- ሰብዓዊ ልማት ለሁሉም
- ስራ ማግኘት የዜግነት መብት ነው
- አምባገነኖች ባሉበት የአንዷለም ቤት እስር ቤት ነው
- ርዕዮት አለሙ ጋዜጠኛ እንጂ አሸባሪ አይደለችም
- ድሌ ዛሬ ነው! ድሌ ዛሬ ነው ድሌ ድሌ ድሌ
የሚሉ መፍክሮችን እነዚሁ ከፍርሃት የተላቀቁ ኢትዮጵያውያን አሰምተዋል።

አንድነትየሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት በሚል ላለፉት 3 ወራት በመላው ኢትዮጵያ በመዘዋወር ሕዝቡን በሰላማዊ ሰልፍ በማደራጀትና ፊርማ በማሰባሰብ ሲያደርገው የቆየውን ሰላማዊ ትግል በመቀጠል የፊታችን እሁድ ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር በመሆን በመስቀል አደባባይ ት ዕይንተ ሕዝብ መጥራቱን ዘ-ሐበሻ ከቀናት በፊት መዘገቧ ይታወሳል።

ESAT Radio Sep 08

ESAT 3rd year Anniversary in Munich Germany

Amharic News 1800 UTC –ሴፕቴምበር 08, 2013

$
0
0
News, Radio Magazine or Mestawot…

የሸህ ኑሩ ልጅ ለምን ታሰረ ? BBN

ኑሮ በካንጋሮ ምድር (ክፍል ፫)

$
0
0
እዚያው ፉትስክሬይ ቁጭ ብለን ወግ በመሰለቅ ላይ ነን፡፡ ባለፈው ወዳጄ ስለ ‹‹ኢምፖርት›› አንሥቶ ነበር ያቆመው፡፡ እስኪ ይቀጥል፡፡
‹‹ምንድን ነው ኢምፖርት የሚያደርጉት ኢትዮጵያ ሄደው››
‹‹ሚስት ነዋ››
‹‹እንዴት ነው ደግሞ ሚስት ኢምፖርት ማድረግ ማለት››
‹‹እዚህ ሀገር ያለ ሐበሻ በሦስት መንገድ ነው ሚስት የሚያገኘው››
‹‹በምን በምን››
‹‹በኢምፖርት፣ በኤክስፖርትና በባላንስ››
‹‹ይሄ ትርጓሜ ያስፈልገዋል››
‹‹ኦኬ፤ ኢምፖርት የሚባለው ሀገር ቤት ትሄድና ሚስት ወይም ባል ይዘህ ስትመጣ ነው፡፡ ኤክስፖርት የሚባለው ደግሞ የውጭ ሀገር ሰው በተለይም የዚህን ሀገር ሰዎች ስታገባ ነው፡፤ ባላንስ ሠራህ የሚባለው ደግሞ ሁለት አበሾች እዚሁ ተገናኝተው ሲጋቡ ነው፡፡››
‹‹ታድያ የትኛው ነው የሚሻለው››


‹‹ሁሉም የራሱ ጣጣ አለው፡፡ ኢምፖርት ስታደርግ ከታደልክ ትዳር የጠማትን ወይም የጠማውን ታገኘዋለህ ወይም ታገኛታለህ፡፡ ካልታደልክ ደግሞ እዚህ ከመጣች በኋላ አቢዩዝ አደረገኝ ብላ ልትፈነግልህ ትችላለች፡፡ ወንዱም ትቷት ሊሄድ ይችላል፡፡ ወይም ይፋታሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ እዚህ ኢምፖርት ተደርገው ከመጡ በኋላ ስቃያቸውን ያዩም አሉ፡፡ ውጭ እንሄዳለን፣ ባል እናገኛለን፣ አለፈልን ብለው ሳያመዛዝኑ ውጭ ሀገር ስለተባለ ብቻ ይመጡና አበሳቸውን ያያሉ፡፡ በተለይ ስደት ላይ ብዙ ዘመን ኖረው፣ እድሜያቸውን ጨርሰው፣ ራሳቸውን መልጠው፣ ሁለት ጠጉር አውጥተው ከሀገር ቤት ዘልላ ያልጨረሰች ሚስት የሚያመጡ ፌንት ይገጫሉ፡፡››
እንዴት ነው የሚገጩት››
‹‹አየህ አንተ ሃያ ዓመቷን ሱዳንና ኬንያ ከጫርካት በኋላ አባባ የምትልህን ቆንጆ ልጅ ስታመጣ፤ እርሷ እያማረባት ሲሄድ አንተ ግን እድሜ ሲያናጭርብህ ቅናቱን አትችለውም፡፡ የነገር አባቷ እንጂ ባሏ ስለማትመስል ሥጋት እየገባህ ይሄዳል፡፡  ያም ያም አንተን ረስቶ የሚስትህን ቁንጅና ሲያወራ እርሷ ተጨዋች አንተ ተመልካች የሆንክ ይመስልሃል፡፡ ያን ጊዜ አበሻነትህ ይነሣብሃል፡፡ አውስትራልያ መሆንክን ትጠላውና መንዝና ሞላሌ፣ ወልቃይት ጠገዴ፣ ሽሬ እንዳ ሥላሴ መሆን ያምርሃል፡፡ መሳደብ፣ መጨቃጨቅ፣ ሲብስም መማታት፣ ሲያልፍም አካል መጉዳት፣ በመጨረሻም ሕይወት እስከ ማጥፋት ትሄዳለህ፡፡
እዚህ ሜልበርንኮ አንዱ እልኩና ቅናቱ አልወጣለት ሲል ከሕንድ ቤት ቀይ ቃርያ ገዝቶ ሚስቱን በበርበሬ አጥኗታል፡፡ ስንቱ ሚስቱን ገድሏል፤ ስንቶቹስ ተደብድበውና ተፈንክተው በሐኪም ጥረት ከሞት ተርፈዋል፡፡ ኢምፖርት ዕዳው ብዙ ነው፡፡
የዚህን ሀገር ሰዎች አግብተው የሚኖሩ ብዙ አበሾች አሉ፡፡ በተለይ ሴቶቹ በዚህ ጎበዞች ናቸው፡፡ እነርሱ ጋር እስካሁን የሰማሁት የከፋ ችግር የለም፡፡ ባይሆን ወንዶቹ ፈተና ይገጥማቸዋል፡፡ ፈረንጅ ወዳጄ ፍቅራዊ (ሮማንቲክ) ነገር ይወዳል፡፡ እኛ ደግሞ ሃኒ፣ ስዊት፣ ዳርሊንግ የሚል ነገር አልለመድነው፡፡ እኔ ሐኒ የማውቀው ከሦስተኛ ክፍል ጀምሮ ማር በእንግሊዝኛ ሐኒ መሆኑን ነው፡፡ ስዊት - ጣፋጭ ነው፤ በቃ፡፡ ዳርሊንግ እዚህ ነው የሰማሁት፡፡ እኛ ደግሞ ቆፍጠን ያልን ነን፡፡ ‹ሌቱን ለአራዊት ቀኑን ለሠራዊት› ነው ወዳጄ፡፡ የኛ አኗኗር ለእነርሱ መሥሪያ ቤት ይሆንባቸዋል፡፡ እንኳን እነርሱ እዚህ ሀገር ቆየት ያሉት ሴቶች እንኳን ‹‹የኛ ወንዶች አባወራነት እንጂ ፍቅረኛነት አይችሉም›› ይሉናል፡፡
ከቻልክ እዚህ ሀገር ባላንስ መሥራት ነው፡፡ ተዋውቀህ፣ ሀገሩንም ዐውቀህ መጋባት፡፡ ችግሩ እዚህ እንደ አሜሪካ ዲቪ የለ፣ እንደ አውሮፓ በመርከብ የሚገባ የለ፣ ከየት ታመጣለህ፡፡ ወይ እዚያው ስደት ላይ ተጋብተህ ካልመጣህ በቀር፡፡ ››
‹‹ይህን ችግርኮ ተባብራችሁ መፍታት ትችሉ ነበር››
‹‹አንዳንዱን አበሻ ተባበር ከምትለው ተሰባበር ብትለው ይሻለዋል፡፡ ሁሉም በየጎጡና በየሠፈሩ ነው፡፡ አብዛኞቹ ቤተ ክርስቲያኖች እንኳን ዘርን መሠረት ያደረጉ ናቸው፡፡ የአማራውን፣ የትግሬውን፣ የኦሮሞውን ቤተ ክርስቲያን ትለየዋለህ፡፡ ትግሬውም አንድ መሆን እያቃተው አድዋ፣ ሽሬ ሲል ታገኘዋለህ፡፡ አማራውም ወልቃይት፣ ጎንደር እየተባባለ ለብቻው ቸርች ይከፍትልሃል፡፡ ኮሙኒቲውም ለየብቻ ነው፡፡ እዚህ ሀገር የኦሮሞ፣ የሶማሌ፣ የሐረሪ፣ የትግራይ ኮሙኒቲዎች አሉ፡፡ አንደኛው ከአንደኛው ጋር የሚጠራጠሩ፣ የማይተባበሩ፡፡ ከትብብር ርቀው ንጽሕ ጠብቀው የሚኖሩ፡፡ በፍቅር የተጎዱ፣ ከኅብረት የጸዱ፡፡ አንዳንዶቹ ኢትዮጵያውያን ነን ይላሉ፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ‹‹ምሥራቅ አፍሪካ›› የሚባል ሀገር ፈጥረውልሃል፡፡ …››
‹‹ኧረ እንዲያውም አዳሙ ተፈራ በጻፈው ‹‹ገመናችን በሰው ሀገር› የሚለው መጽሐፍ ላይ ሜልበርን የሚገኘው የኦሮሞ ኮሙኒቲ በ2010 እኤአ 25ኛ ዓመቱን ሲያከብር የጻፈውን አይቼ ገርሞኝ ነበር፡፡
‹‹The Oromo are indigenous African people from the north eastern of Africa.›› ይላል፡፤ ኢትዮጵያ ላለማለት አዲስ ሀገር ፈጥረዋል፡፡ ››
‹‹እይውልህ እንደዚያ ነው እንግዲህ፡፡ የሚገርምህኮ እዚህ ያለ ሰው መገንጠልን የሚጠላ ተገንጣይ መሆኑ ነው››
‹‹በዚህ ብቻ አይበቃም ትርጓሜ ያሻዋል - ብሏል ኪነ ጥበብ›› አልኩት፡፡
‹‹በውጭ ያለ ዳያስጶራ ስለ ኤርትራ መገንጠል ሁል ጊዜ እየተንገበገበ ያወራል፡፡ እርሱ ግን ራሱ በፈቃዱ ያለ ሪፈረንደም ተገነጣጥሏል፡፡ በምትቃወመው ነገር ውስጥ ራስህን እንደማግኘት ያለ አስነዋሪ አካሄድ የለም፡፡ በየስብሰባው ‹ዐንቀጽ 39› የምትባል ነገር ትነሣለች፡፡ ‹‹የብሔረሰቦች መብት እስከ መገንጠል›› የምትባለው፡፤ ይህች ዐንቀጽ እስካሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ተግባራዊ አልተደረገችም፡፡ እዚህ ግን ተግባራዊ ተደርጋለች፡፡ የተገበሯት ደግሞ የሚቃወሟት ሰዎች ናቸው፡፡ ለዚህ ነው ‹‹መገንጠልን የማይደግፍ ተገንጣይ›› ያልኩህ፡፡ አሁን ዘመን መለወጫ እየመጣ አይደለ? ሦስት ቦታ ነው ፕሮግራም የተዘጋጀው፡፡ ከዚያ መርጠህ እንደየብሔረሰብህ መሄድ ነው፡፡ ወዳጄ እዚህ ሀገር ጩኒ ይምጣብኝ››
‹‹ማነው ጩኒ ደግሞ››
‹‹ጩኒ ሰው አይደለም፤ ሕዝብ ነው››
‹‹ጩኒ የሚባል ሕዝብ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ መስማቴ ነው፡፡››
‹‹ጩኒ ማለት ቻይና ነው፡፡ እዚህ ሀገር ጩኒ ነው የምንላቸው፡፡ ጩኒ እርስ በርስ በመደጋገፍ ማንም አይችላቸውም፡፡ ብድር ይሰጡሃል፤ መረጃ ይሰጡሃል፡፡ ያቋቁሙሃል፡፡ ከዚያ ምርጥ ኢንቨስተር ትሆናለህ፡፡ ያለበለዚያ ደግሞ ወጥሬ እሠራለሁ ካልክ በቀላሉ የምትከራየው ቤት ይሰጡሃል፡፡ እንዲት ክፍል ተከራይተህ ኑሮ ሳይከብድህ ወጥረህ ትሠራና በዓመትህ ቀና ትላለህ፡፡ ወዳጄ ጩኒ አንገቱን ደፍቶ እየሠራ ልጁን ምርጥ ትምህርት ቤት ነው የሚልከው፡፡ ኮሙኒቲያቸው ልጆቹን በሚገባ ነው የሚረዳቸው፡፡ ስለዚህ ልጆቹ ውጤታማ ናቸው፡፡ እኛጋኮ ወላጆችና ልጆች አልጣጣም ብለዋል፡፡ ልጆቹን የቤት ሥራ ማን ያሳያቸው፡፡ ማን በትምህርት ያግዛቸው፡፡
አገርሽ ምንኛ መንደርሽ ምንኛ
አላውቅበት አልኩኝ ያንችን አማርኛ
ሲባል አልሰማህም፡፡ በምን ቋንቋ በምን ዕውቀት ከልጆቻችን ጋር እንግባባ፡፡ ልጆቻችን አያውቁም ብለው ንቀውናል፡፡ በዚህ የተነሣ ከትምህርት የሚያቋርጡት ብዙ ናቸው፡፡››
‹‹ቆይ ግን እዚህ መጥተው የተሳካላቸው የሉም››
‹‹ለዓይነት ያህልማ አሉ፡፡ መቼም ለስማችን መጠሪያ ቁና ሰፍተናል፡፡ ለአካባቢ ምርጫ እስከመወዳደር የደረሱ አሉ፡፡ ያው ከሆቴልና እንጀራ ቤት ባናልፍም ቢዝነስ ያላቸውም አሉ፡፡ በተማሩት ሞያ የሚሠሩም በመጠኑ አሉ፡፡ እኔ የሚገርመኝ ግን በኢሕአፓ፣ በኢሕአዴግ፣ በግንቦት ሰባት፣ በኢዲዩ፣ በቅንጅት ውስጥ ለመግባት እንጂ በምንኖርበት ሀገር በሚገኙ ፓርቲዎች ውስጥ ገብቶ፣ አባል ሆኖ፣ ተወዳድሮ ፓርላማ ለመግባት፣ የአካባቢ ተመራጭ ለመሆን የሚተጋ አበሻ ብዙ አናይም፡፡ አሜሪካ እንኳን ሚሊዮን የሚሞላ ኢትዮጵያዊ ተከማችቶ እስካሁን አንድ የአካባቢ ተወካይ እንኳን አለማግኘታቸው ይገርመኛል፡፡ እኛ በሀገራችን አምባሻ ነው የምንራኮተው፡፡ ለምሳሌ እዚህ አውስትራልያዊ ዜግነት ካለህ መምረጥ ግዴታህ ነው፡፡ እንደ አሜሪካ አይደለም፡፡ የመምረጥ ግዴታ አለብህ፡፡ ያለበለዚያ ቅጣት አለው፡፡ የፓርቲዎቹ አባል ስትሆንና ሳትሆን ዕድልህ ይለያያል፡፡ if you are not a member, you are a number ይሉሃል፡፡ ችግሩ ግን እዚህ ሀገር ተመልካች እንጂ ተጨዋች የለም፡››
‹‹ማለት››
‹‹ኳሱ ጉዳያችን ነው፡፡ ሜዳው አውስትራልያ ይባላል፡፡ ሕጉ የሀገሪቱ ሕግ ነው፡፡ ዳኛው ሲስተሙ ነው፡፡ ዋንጫው ውጤትህ ነው፡፡ እዚህ በሚገባ ተጫውተህ የስኬትን ዋንጫ መሳም ትችላለህ፡፡ ምን ያደርጋል ታድያ፡፡ በዙሪያህ ቆሞ ለምን ይህ አይሆንም? ለምን ይሄ አይደረግም? እገሌ ለምን እንዲህ ያደርጋል? እንዲህ በመሆኑ አኩርፌ ቀርቻለሁ፣ የሚል የዳር ተመልካች እንጂ ሜዳው ውስጥ ገብቶ ለመጫወት የሚፈልግ የለም፡፡ እዚህ ያለውን ሰው ‹‹ሰይጣን›› ከምትለው ‹ኮሙኒቲ› ብትለው ደንግጦ ያማትብብሃል፡፡ ተበላ፣ ተጠጣ፣ ተጣሉ፣ ተከፋፈሉ ብቻ ነው የምትሰማው፡፡ አንድ ወዳጄ ምን ይላል መሰለህ
የትልቅ ሰው ልጅ ቀረ በከንቱ
ሀገር ሳይገዛ ሳይባል አንቱ - እንዲህ ነው እንግዲህ፡፡
ካሮላይን ስፕሪንግስ፣ አውስትራልያ

የመከላከያ ሠራዊቱ-ድምበር አስከባሪ ወይስ አሳሪና አስተዳዳሪ ?

$
0
0

  ( እምብኝ በል-ጎፍንን )         

ethiopian-troopsየደርግ ወታደራዊ መንግሥት የፖለቲካ ሥልጣኑን በለስ ቀንቶት  ሥልጣን ለመያዝ  ለበቃው ህወሃት ከለቀቀ በኋላ ህወሃት ትኩረት ሰጥቶ ያጠናክር የነበረው የካድሬውንና የመከላከያ ሠራዊቱን መዋቅር ነበር። በመከላከያ ሠራዊቱ ሥር  የአጋዚ ሠራዊት (የፌደራል ፖሊስ እያሉ የሚጠሩት) ቅጥረኛ የከተማ  ነዋርዎች ነብሰ ገዳይ ቤት ለቤት እያውደለደለ ንብረት በመዝረፍ የተሰማራ በቤተ-መንግስት በጅት ይተዳደር የነበረውን የደርግ ልዩ ጥበቃ ኃይልን ቦታ የተካውና በህወሃት የሚመራው፤ የፖሊስ ኃይል ፤ የደህንነትና ፈጥኖ ደራሽ ኃይል እንዳሉበት ግምት ውስጥ አስገብተን ማለት ነው። በመሆኑም እነዚህ መዋቅሮች እስከ ዛሬ ድረስ የሥርዓቱን እድሜ በማራዘም ረገድ የተጫወቱት ጨዋታ ቀላል አይደለም ወይም የህወሃት የጀርባ አጥንት ናቸው ቢባል ነገሩን ክብደት ሊሰጠው እንደሚችል በመግለጽ ለዛሬ ያለኝን ትኩረት በዚህ ላይ ላድርግና በመጠኑም ቢሆን  በዚህ ተቋም ላይ ያለኝን ሃሳብ ማካፈሉ ጉዳዩን በቅርበት ለሚከታትሉ ምንጭ ወይም የመነሻ ሀሳብ የሚሆን መስሎ ስለታየኝ ከዚህ የሚከተለውን የግል  አስተያየቴን ለአንባቢዎቼ አቀርባለሁ።

በሽግግሩ ወቅት የመከላከያ ሚንስትር የነበረው ስየ አብርሃ ሲሆን ከፀደቀ 18 ዓምታትን ያስቆጠረውና በሥራ ላይ ሳይውል የቀረው በህወሃት ተረግጦ የሚገኘው ሕገ-መንግስት ከመታውጁ በፊት ስየ አብርሃ -የቀጣይቷ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራስያዊት ሪፐብሊክ ሠራዊትን በሚመለከት፦ እንዲህ ብሎ ነበር ፦የመከላከያ ሠራዊቱ ከዋና መንገድ 20 ኪ/ሜትር  ከዋና ከተማ 40 ኪ/ሜትር ርቆ እንዲሰፈር እንደሚደረግ ፤ የሠራዊቱ ብሔራዊ አስተዋጾም እንደየ መጣበት ብሔር ወይም ብሔረሰብ ሕዝብ ብዛት እየታየ እንደሚመደብና ወታደራዊ ብቃቱም ፕሮፌሽናል ስታንዳርድ  (ዓለም አቀፋዊ ደረጃውን የጠበቀ) ወይም እንዲኖረው ተደርጎ እንደሚሰለጥን መሪ አቅጣጭ ተቀምጦለት ነበር። ይሁን እንጅ ስየ አብርሃ ይሁን ሌላው በመከላከያ ሠራዊቱ ውስጥ በከፍተኛ አመራር ደረጃ ላይ የነበረው አካል ይሁን አሁን ያለውም ቢሆን ይህን መርሕ እንዲተገበር ሲያደርጉት አልታዩም። በርግጥ ስየ አብርሃ በመከላከያ ሚንስትርነቱ ብዙ አልቆየበትም። ቢቆይም እዚህ ግባ የሚባል  መሠረታዊ ለውጥ ያመጣል ብየ አልጠብቅበትም ነበር። ምክንያቱም እሱም ቢሆን በህወሃት ውስጥ ለረጅም ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ በአመራር ላይ የቆየና ወደኋላ አካባቢ በጥቅምና በሥልጣን ክፍፍል ተገቢውን ድርሻ ባለማግኘታቸው በህወሃት ውስጥ ክፍፍል ሲፈጠር በሟቹ መለስ ዜናዊና በአዲሱ ለገሰ ውሳኔ ተገፍተው ከጎድና ከወጡት አንዱ ቢሆንም አሁን ህወሃት የሚያራምደውን የአንድ ጎሣ (የትግሬ) የበላይነትን ዓላማ ወደ ፊት ይገፉ ከነበሩት ጽንፈኞች ስፊ ድርሻ የነበረው በመሆኑ ለተወሰኑ ወራቶች የህወሃት ተቃዋሚ መስሎ ብቅ ቢልና ኢትዮጵያዊነቱን ለማስመስከር ቢሞክርም  እምነት እንዳንጥልበት የሚያደርጉ ብዙ ሊገልፃቸው የሚገቡ ነገሮችን አፍኖ መያዙና ለግል ሕይወቱ ቅድሚያ መስጠቱ ከትግሉ ጎራ መራቁን አመልካች ነው። ይህን ስል ግን የስየን ጠንካራ ጎኖቹን ማለትም ራሳቸውን ደብቀው (አድፍጠው) ዝም ካሉት አረጋሽ ፤ተወልደና ዓለምሰገድ እንዲሁም አብረው ብዙ ሳይራመዱ ተመልሰው የሥልጣን ጥማታቸውን ለማስታገስ ከወሰኑት ሐሰን ሽፋና አባይ ፀሀየን ከመሰሉት በእጅጉ የተሻለ መሆኑን ፤ ለሥርዓቱ አለመገዛትና ድርጅቱን ጥሎ በመውጣት ህውሃትን በውጭ ሆኖ መመልክቱ ብዙ አስተማሪ ነገር እንዳገኘበት፤ እንድሁም ይመራውና ይታገልለት የነበረው ድርጅት ቅጥረኛና ፀረ-ኢትዮጵያ ድርጅት መሆኑን፤ ከሱ በፊት የተገደሉ የታሰሩ ፤ የተባርሩ ነባር ታጋዮችን እጣም በሱ ላይ በመድረሱ አዛኝ ልቦና ሊያድርበት ይችልላ የሚለውን በታሳቢነት በማሳደር አሁንም ስየ ከሕዝብ ጎን በመሆን ትግሉን ቢቀጥል የተሻለ እንደሚሆን እግረ መንገዴን መጠቆም እወዳለሁ ምክንያቱም ኢትዮጵያ አሁን ከደረሰችበት አደገኛ ሁኔታ እንድትደርስ ካደረጉት አንዱ ስለሆነ  ከደሙ ንጹሕ ለመሆን የኢትዮጵያን ሕዝብ የሚክስ ተግባር መፈጸም ይጠበቅበታልና ህወሃትን  አለበት።

የመከላከያ ሠራዊቱ ከላይ በተቀመጠለት መርህ መስረት ስፍሮ የሀገር ሉዓላዊነትን ማስከበር ሲግባው  የሚፈጽመው ተግባር ግን በግልባጩ በየመሸታ ቤቱና ስራ አጥተው ሰውታቸውን ሸጠው በሚያድሩ ምስኪን እህቶቻችን መኖሪያ መንደር ለመንደር ትጥቁን ተጀብሎ መዋያና ማደሪያ ማድረጉን ፤ በገጠርና በየከተማው በአስዳደር ሥራ ጣልቃ ሲገባ ፤ መሬት ሲመራና ሲያካፍል ፤ በየተሰማራበት አካባቢ ሴቶችን አስገድዶ ሲደፍር ፤ በኃይል አስገድዶ የጠለፋ ተግባር ሲፈጽምና አለቆቹ  እንደ አንድ የገቢ ምንጭ ቆጥረውት ሩዋንዳ ፤ ሱዳንና ሶማሌ ድረስ እየሰደዱ ከዩኤን ወፍራም ደመወዝ በዶላር እንዲከፈለው በማስደረግ ለአለቆቹ የሀብት ምንጭ ከመሆንና መጠቀሚያ ከመሆኑ ባሻገር በሕዝቡ ዘንድ የሚያስመሰግን ተግባር ሳይሆን የሚፈጽመው አሳፋሪና የጠመንጃውን አፈሙዝ በሕዝብ ላይ በማዞር በአደባባይ ንጹሃን ዜጎችን ከመግደል ከመደብደብና ከማፈን ውጭ ኢትዮጵያዊ የአገር መከላከያ ሠራዊት መሆኑን የሚያስመሰክር ተግባር አልፈጸመም ። እዚህ ላይ እንደሰለጠነው አገር ሰራዊት የተፈጥሮ አደጋ ሲደርስ ሄዶ አላገዘም ፤አቅም ለተሳናቸው ድጋፍ አላደረገም በማለት መክሰሴ አይደለም የጠመንጃውን አፈሙዝ በምን ሂሳብ ነው ወደ ሕዝብ እንዲያነጣጥርና አልሞ እንዲተኩስ የሚደረገውና ሕዝብ የሚጨርሰነው ነው? ?

የመከላከያ ሠራዊቱ ውስጡ በሰፊ ቅራኔ ውስጥ የተሞላ ቢሆንም ከአማራው ብሔር የመጣው የመከላከያ ሠራዊት አማራውን ሲያጠቃና ሲጨፈጨፍ ተባባሪ ሆኖ ከማገልገልና ነገሩን ከማባባስ አልፎ የአማራውን ብሔር ሕዝብ እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ መብት ተነካ ብሎ የአማራውን ሕዝብ ጥቃት ሲመክት አልታየም። ከኦሮሞው ብሔር የመጣው የኦሮም ተወላጅ የሆነው የመከላከያ ሠራዊት አባልም ኦሮሞው ሲንገላታ ከመተባበር የዘለለ ተግባር ሲፈጽም አልታየም። በርራ ላይም  በየግዳጁ ሲግባ በፊቱና በኋላው የሁለት ወገን እሣት የህወሃት አለቆቹና ሥርዓቱን ለመጣል በመታል ላይ ያሉት የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ጥይት እንደሚገድለው ይታወቃል።ይህ ሁሉ እየሆነ ግን የሥርዓቱን እድሜ ለማራዘምና በአለቆቹ ዘንድ ምስጉን ለመባልና በበጎ እንዲታይ ምዝብሩን ሕዝብ በማንገላታት በመግደል  ስቃዩን በማባባስ ለሰሞንም ቢሆን የህወሃት ታማኝ መስሎ እያደረ ይገኛል። የደርግ የጦር ሠራዊት በጅምላ ጨፍጫፊነት የሚታወቅ ቢሆንም የሥርዓቱ  ከአናቱ  ወይም ከላይ የተበላሸ መሆን እንጅ በጦር ሠራዊቱ ውስጥ አንድ የሚያደርግ ባህሪ ኢትዮጵያዊነትን ስንቅ የሰነቀ ነበር።  ያም ሆኖ ይህ ዛሬ የሚታየው የአገር ሉዓላዊነት መደፈር አስከፊ ጥቃትና ገጽታ በኢትዮጵያችን እንዳይመጣ ግን ሕይወቱን አሳልፎ የሰጠ፤ ደሙን ያፈሰሰ፤ አጥንቱን የከሰከሰ ነበር። ይሁን እንጅ የደርግ ሥርዓት ሲናድ በሠራዊቱ ላይ የደረሰበትን የሞራል ፤ የአካል ፤ የህይወት ዋስትና ማጣትና የጎዳና ተዳዳሪ እንዲሆን መዳረጉ በዜግነቱ ሊከበር አለመቻሉ መቼም ቢሆን የማይረሳ የህወሃት በቀልተኛነት ታሪክ በታሪክ ማህደር ተዘግቦ የሚጠብቅ ይሆናል። የአሁኖቹ ሰሞነኞችና አዲስ ናፋቂዎችም ነገ መሀሉ ዳር -ዳሩ መሀል የሚሆንበት ሁኔታ ሲፈጠር በማን ላይ ሊያሳብቡ ማንን ምክንያት ሊያደርጉ እንደሚችሉ እግዚአብሔር ብቻ የሚያውቀው ጉዳይ ይሆናል። እንደኔ የግል አስተያየት ግን ህወሃትን መከታ በማድረግ በማንኛውም አይነት መዋቅር የተፈጸመች እያንዳንዷ ግፍ ጊዜዋን ጠብቃ  ብህዝብ ፊት ለፍርድ እንደምትቀርብ ትንበያ  ወይም ጥንቆላ ሳይሆን በግልጽ እንደሚሆን በድፍረት መናገር ከእውነቱ መራቅ አይደለም።

  በሽግግሩ ወቅት በተቋቋመው ሕገ-ምንግሥት አንቀጽ 87 ላይ የመከላከያ መርሆዎች ይልና፦ከዚህ የሚቀጥለውን ደንብ ያትታል።ደንቡ ግልጽነት የጎደለውና አሻሚ ትርጓሜ እንዲሰጥ የተደረገ ውይም የያዘ ሲሆን ሆነ ተብሎ ለማጭበርበር የተዘጋጀ መሆኑን ያመለክታል። ራሱን እንደመንግሥት አደርጎ የሚቆጥረውና በማርክስዊ ሌኒናዊ ሊግ ትግራይ የሚመራው የታጠቀው የደደቢት ፖለቲካዊ ኃይል በክህደት ተወልዶ በክህደት ያደገና የፀረ-ሕዝብ ተቋም ቢሆንም በየጊዜው የሚቀያየረውን የማጭበርበሪያ ስልት ደግሞ ለይቶ ማወቅ የግድ ይሆናል ብየ አስባለሁ።

1/ የሀገሪቱ የመከላከያ ሠራዊት የብሔር ብሔረሰቦችን ፤የሕዝቦችን ሚዛናዊ አስተዋፅኦ ያካተተ ይሆናል።

 እንደሚታወቀው በደርግ መውድቂያ አካባቢ ህወሃት አገር ለማጥፋት ብዙ ቁጥር ያለው ሠራዊት አስታጥቆ ነበር ። ወደ መሀል አገር ሲገባም በአምሳሉ የፈጠራቸውን ጨምሮ ይህ ኃይል የማይናቅ ቁጥር ነበረው። ከተራ ውንብድና ወደ ሕጋዊ ውንብድና ሲሸጋገርና አገር መግዛት በእጅ የተያዘና የሚቻል መሆኑ ሲረጋገጥ በቅጥፈት ያደገው ህወሃት ያሰለፈውን ኃይል የሥርዓቱ አገልገጋይና ታማኝ በማድረግ ማስቀጠል ስለነበረበት የሚጠቀምበት መንገድ መፈለግ የግድ በመሆኑ የተወሰነውን የህወሃት ኃይል የአካባቢውን ህዝብ በማስለቀቅ ዳንሻ በተባለ ቦታ ውስጥ በአንድ ማዕከል የመተዳደሪያ በጀት ስጥቶ ሲደራጅ የቀረውን ለማሸጋሸግ ደግሞ ድርጅቱ መላ መምታት ነበረበት። ይኸውም በሕጉ መሠረት የሰፈረው የሠራዊት ምደባ ሕግ እንደ ብሔሩ ወይም ብሔርሰቡ ብዛት ሚዛናዊ መሆን አለበት ስለሚል ይህን ሕግ ለመከላከል አብዝኛው የህወሃት ሠራዊት በአማራው ክፍለ ሀገራት ብዙ ጊዜ ስለቆየ አማርኛ መናገር የሚችለውን በቀጥታ የአማራ ብሔር ተወላጅ እንደሆነ አድርጎ መመደብ ነበረበት ተመደበ  ኦሮምኛ ተናጋሪ ህዝብ ባለበት ተወልደው ያደጉ ትግሬዎችም የኦሮሞውን ሠራዊት ኮታ እንዲቀላቀሉ ተደረገ ( አባዱላ ፤ዘገየ የማነብርሃን…ወዘተ የመሳስሉ)  እዚህ ላይ ለኢህአፓና ለደርግ አንምበረከክም ያሉትና ለህውሃት የተንበረከኩት ኢህዴኖች በዚህ የተግባር አፈፃፀም ወቅት ብአዴኖች የሆኑት በድጋሚ ለህውሃት ተንበረከኩ። ለህወሃት መረጃ በማቀበል፤ መንገድ በመምራት፤ በስለላና በአጠቃላይ የህወሃትን ዓላማ ስኬታማ ለማድረግ ታጥቀው ያገለገሉ ባለሟል የሆኑት እስላሙን ከእስላሙ፤ ክርስቲያኑን ከክርስቲያኑ ፤ደገኛውን ከቆለኛው፤ ሽናሻውን ከአገው ጋር፤የደቡቡን ከሰሜኑ፤ የምሥራቁን ከምዕራቡ ጋር በማጋጨት አገር ያጠፉት (አዲሱ ገለሰ ፤ ታምራት ላይኔ ፤ ተፈራ ዋልዋ ፤ ብረከት ስምኦን ፤ታደሰ ካሳ ፤ህላዊ ዮሴፍ) በዚህ መጥፎ ምግባራቸውና በአማራው ሕዝብ ላይ በፈፀሙት ሁሉም አይነት ግፍ  ሰፊው የአማራ ሕዝብ ለሁሉም ጊዜ አለውና አንድ ቀን ይፋረዳቸዋል።እዚህ ላይ ልብ ብላችሁ እንድታነቡልኝ የምጠይቀው ቢኖር ህወሃት ሕዝብና አገርን መግደል ዓላማው አድርጎ የተነሳ ሲሆን ዓላማውን ለማሳካት ለ40 ዓመታት ያህል ሥራውን እየሰራ ይገኛል ተግብሩ ወይም ዓላማው ጥፋት ነው ነገር ግን ለዓላማው አሁንም ወደፊት የሥርዓቱ እድሜ እንዲረዝም ለማድረግ ተስፋ ባለ መቁረጥ እየታገለን ይገኛል። እኛም የሕዝብና የአገር ጠላት መሆኑን ተገንዝበን በቻልነው መንገድ ሁሉ ድንጋያችን እየወረወርንበት እንገኛለን ነገር ግን ትግሉ አንድ የዘነጋው መሠረታዊ ጉዳይ አለ ይኸውም ቀደምት የኢህዴን አመራር የነበሩና ዛሬም ህወሃት በተለያዩ ከፍተኛ የኃላፊነት ደረጃ ላይ አስቀምጧቸው የሚገኙትን በዋናነት ከፍ ሲል ስማቸውን የዘረዘርኩት አደገኛ የኢትዮጵያ ጠላቶች መሆናቸውን ቅድሚያ ሰጥቶ አለመንቀሳቀሱና አሁንም ትኩረት እንዲደረግበት ለምሳሰብ ነው። ዛሬ በተለያዩ መዋቅሮች ቁልፉን ቦታ ይዞ የአማራውን ክልል በቅኝ -ገዥነት እየገዛ የሚገኘው ኃይል ምንጭ በእነዚህ በተጠቀሱ ግለሰቦችና በዙሪያቸው በተሰማሩ አሾክሿኪዎች አማክኝነት ነው። ህግ መጣስ የተጀመረው በዚህ ጊዜ ባይሆንም ኢህዴን ያሰለፈው ምስኪኑ የአማራ ብሔር ሠራዊት ግን በብር ከ3ሽህ በታች ድጎማ እየተሰጠው ወደ የመጣህበት ከብትና  ፍየል ጥበቃህ ተመለስ እየተባለ መሳለቂያ ሆኖ እንዲሄድ ተገዶ ከሠራዊቱ አባልነቱ ተወገደ። የቀረውም በህወሃት ካድሬና የሠራዊት አለቆች በየጊዜው እየተገመገመ እንዲባረር ሲደርግ ድምጣቸውን አጥፍተው ሰጥ ለጥ ብለው የተግዙት የሠራዊት አባላትም ህወሃትን የሚያስጭንቅ ውጫዊ ሁኔታ በተፈጠረ ቁጥር ወደ እሥር መወርወር ፤በድብቅ በመግድል፤ ጤና በሚነሳ መድኃኒት ተወግተው እንዲሞቱ ማድረግ የድርጅቱ መደበኛ ባህሪ እየሆነ መጣ። 1/ለምሳሌ ኮሎኔል ታደለ ገብረሥላሤ ሩውንዳ አዝማች ሆኖ ሄዶ የነበረ ህወሃትን ከደደቢት እስከ ደቡብ፤ ምእራብና ምሥራቅ ግንባር ከፋች በመሆን የሚታወቅ እንደነበር የማይካድ ነው። 2/ኮሎኔል ናቃቸው ጫቅሉ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርንት በመጨረሻ የወጣው ዝነኛ ተዋጊና አዋጊ ታመው በህክምና ላይ በነበሩበት ወቅት ህወሃት ሆነ ብሎ በመርዝ ተወግተው እንዲሞቱ ያደረጋቸው ሰለባዎች ናቸው። ይህ አድሎ እስከመቼ ይቀጥላል በሚል በመከላከያ ሠራዊቱ ውስጥ ተነስቶ የነበረው የመከለከያ ሠራዊቱ ጥያቄና አመጽ በተለይም በአማራው የመከላከያ ሠራዊት አባላት እድገቱን ጨምሮ ክልሉ በልማት ወደ ኋላ መቅረቱና በብአዴን አመራር ቦታ የተቀመጡት አማራ ያልሆኑና ለአማራው ብሔር ሕዝብ የማይጠቅሙ ጠላቶች ናቸው በማለት 1/በረከት ስምኦንና 2/ተፈራ ዋልዋን  እንዲሁም ሌሎችንም ምሳሌ አድርጎ የተነሳው እንቅስቃሴ እየተገመገመ እያለ ድንገት የኢትዮ-ኤርትራው ጦርነት ተጭሮ ሠራዊቱን ለመምታት ምቹ ሁኔታ ተፈጠረ እነሆ  ከዚያ በኋላ ገዥው ኃይል አመጹን አዳፍኖ ሠራዊቱን የሥርዓቱ አሽከር በማድረግ ሕዝብ እንዲጨርስ አሰማርቶት ይገኛል ። አሁን ይህችን መጣጥፌ እያዘጋጀሁ እያለሁ በፖሊስ ስም የሚሸቅጠው የአጋዚ ሠራዊት በመባል የሚታወቀው የሠራዊት ኃይል በሰላማዊ ፓርቲ አመራር ኃይልና አባላት ላይ ያደረሰውን ጥቃት እየተመለከትኩ በድርጊቱ እጅግ አዝኘ እስከ መቼ? በሚል ጥያቔ ስሜት ውስጥ ገብቼ ነው።

2/ የመከላከያ ሚንስትር  ሆኖ የሚሾመው ከስቪል ይሆናል።

የሕግ ባለ ሙያ ባልሆንም እስከ አሁን በመከላከያ ሚንስትር ሚንስትር ሆነው የነበሩትን ወስደን ስንመለከት በትግል ላይ የነበሩ ለፓርቲያቸው የሚያደሉ ሠራዊትን በበላይነት ሲመሩና ሲያዋጉ  ሲያዋጉ የነበሩ ሲሆን ምንጫቸውም ያው ከህወሃት እንደሆነ ይታወቃል። ከአገር አጥፊው መለስ ሞት በኋላ የመጣው ካቢኔም ለማጭበርበሪያ ይሆን ዘንድ አንዳንድ የሹመት መስጠትና የመለዋወጥ ሁኔታዎችን ያደረገ ቢሆንም ከኋላ ያሉት አስተኳሾችን እነማን እንደሆኑ ስለምናውቃቸው የተጃጃሉት እራሳቸው እንጅ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዳልሆነ ሊገነዘቡ ይገባል። ነገር ግን ቀልዱን አበዙት። እነሳሞራም ራሳቸውን አንቱ ያሉ በፀረ_ህዝብነት ታሪካቸው የታወቁ ስለሆነ ማንም የሚያዛቸው እንዳልሆኑ መግደል የሚፈልጉትን ከመግደል እንደማይታቀቡ ግልጽ  ሆኖ እያለና ነፍጥ አምላኪ ኃይልን በጎ ነገር ሊያመጣ ይችላል ብሎ ማሰብ አይቻልም። ማንም ይሾም ማንም ይህ ሥርዓት ፀረ-ሕዝብ ፤ ፀረ- ኢትዮጵያ እስከሆነ ድረስ መውወድ ብቻ ነው ያለበት።

3/ የመከላከያ ሠራዊት የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ከመጠበቅ በተጨማሪ በዚህ ሕገ-መንግሥት መሰረት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚሰጡትን ተግባሮች ያከናውናል።

ይላል። ይህን ነጥብ በሁለት ከፍለን ብንመለከተው መሰሪነቱን ለመረዳት ይቀላል፦

ሀ/ የመከላከያ ሠራዊት የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ይጠብቃል፦ አዎ!! የአንድ አገር የመከልከያ ኃይል(ሠራዊት) ተቀዳሚ ተግባሩ የአገርን ዳር ድንበር (ሉዓላዊነት) ከማንኛውም ጥቃት መጠበቅ ማስከበር ነው። በዚህ ዙሪያ ይህ የህወሃት የመከላከያ ኃይል በአገር ሉዓላዊነት ጉዳይ የተፈተነበት ወቅት ነበረ ወይ ? ካልነበረ በምን መለኪያ ሊታመን ይችላል ? ለዚህ የሚያበቃ መንፈሳዊና ብሔራዊ ሞራል አለው ወይ? በከፍተኛ ደረጃ አመራር ላይ ያሉት ከዚህ ጨዋታ ውጭ ከሆኑ እታች ያለው ኃይል አገራዊና ሕዝባዊ ፍቅር አለው ብሎ ለመናገር ዋስትና የሚሆኑት ከየት ሊገኙ ይችላሉ ? ትንሽ በኢትዮ-ኤርትራው ጦርንት ዙሪያ ልቆይና የመጨራሻ መደምደሚያየን አስቀምጣለሁ።

በ1958 የተቋመው ኤ.ኤል.ኤፍ ( የኤርትራ ነፃ አውጭ ግንባር) ቀደም ሲል ከዘውዳዊው ሥርዓት ጋር በኋላ ከወታደራዊ መንግሥት ጋር ውጊያዎችን ያካሂድ እንደነበር ይታወቃል ። ወደኋላ አካባቢ ግራ ዘመም የሚመስል ነገር ግን ያልነበረ ኢ.ኤል.ኤፍን ከሁለት እንዲከፈል አደረግ። አዲስ በተቋቋመው ኤ.ሕ.ኤል.ኤፍ (የኤርትራ ሕዝብ ነፃ አውጭ ግንባር **ሻቢያ**) እና በኤ.ኤል.ኤፍ መካከል ቅራኔዎች እያደጉ በመሄዳቸው አንዱ ሌላውን መብላት ጀመረ። በመሆኑም ሻቢያ ጉልበት እያገኘ ጀብሃ እየተዳከም መጣ ። ሻቢያ ጀብሃን ብቻ ሳይሆን ሌሎችንም ትጥቅ የያዙ በኤርትራ ውስጥ ይንቀሳቀሱ የነበሩትን የማዳከም አቅም አገኘ። በ1967 ዓ/ም የተቋቋመው ተጋድሎ ሀርነት ትግራይ በኋላ ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ በኤርትራ ከተከሰተው ሁናቴ ጋር የሚያገናኘው ብዙ መሠረታዊ ምክንያት ሊኖር እንደሚችል ነገር ግን ይህን ጉዳይ ቀንጭቦ ማለፍ ስለማይገባ ራሱን አስችሎ ማቅረቡን በማመን ወደ ተነሳሁበት ነጥብ ልመለስና ጀብሃም ሆነ ሻቢያ ህወሃትን በቀጥታም ይሁን በተዛዋሪ የማደራጀትና የማስታጠቁን ጉዳይ በበላይነት ይዘውት እንደነበር ይታወቃል። ደርግ በሚያደርጋቸው ዘመቻዎችም በጋራ ማለትም ሻቢያና ህወሃት በከፍትኛ ደረጃ ይተባበሩ ነበር። ይህ ግን ቀጠለ ወይስ አልቀጠለም ? ወደሚለው ስንገባ ሻቢያ የአዛዥነቱን ህወሃት የታዛዥነቱን ጉዳይ በአግባቡ ሊያደርጉ ባለመቻላቸው በመሃከላቸው የነበረው ጥብቅ ግንኙነት በህወሃት አልታዘዝም ባይነት ምክንያት ሊቀጥል አልቻለም። ለይቶላቸው የከፋ ግጭት ባይፈጥሩም ደርግ እስኪወድቅ ድረስ ይረዳዱ ነበር።ይህ በዚህ እንዳለ ግን ሻቢያ ህወሃትን ማጥመዱ አልቀረም ህወሃትም ሻቢያን የማደናቀፍ ተግብሮችን ማራመድ ጀመረ። ለምሳሌ ዴሞክራሲያዊ ምንቅስቃስ ህዝብ ኤርትራ የሚባለው ድርጅት ፀረ-ሻቢያ ሆኖ እንዲቆም የማደራጀቱን ሥራ ይመራው የነበረው ህወሃት ነበር።ሻቢያ ይህን ተግባር ቢያውቅም የተነሳበትን የመገንጠል ዓላማ ላለማደናቀፍ ህወሃትን ይጠቀምበት እንደነበርና ወደፊት ግን ወጥመድ ውስጥ ለማስገባት አለመቦዘኑን የሚያመላክቱ አንዳንድ ጉዳዮች ነበሩ። ከላይ እንደገለጽኩት ይህን ጉዳይ ባጭሩ ማሳየት ስለማይቻል ገረፍ ገረፍ አድርጌው ልለፍና ደርግ ከወደቀ በኋላ በአዲሲቷ አፍሪቃዊት አገር ኤርትራና ኢትዮጵያ ምን አይነት አንድነትና ልዩነት ነበር የሚለውን በመነካካት በጉዳዩ ሰፊ እውቀት ያላቸውን አባንኘ በሰፊው እንዲያብራሩት በመተው በበኩሌ የማውቀውን እንዲህ ለመግለጽ እሞክራልሁ።

  ወዶም ይሁን ተገዶ ኤርትራን በአማራ ገዥ መደብ በቅኝ አገዛዝ የነበረች አገር ናት በማለት አስቀድሞ እውቅና የሰጠው ህወሃት እንደሆነ ይታወቃል። ሻቢያ አስመራን ህወሃት አዲስ አበባን ከተቆጣጠሩ በኋላ ከበሮ መደለቁ ብቻ ሳይሆን ሁለቱ አገሮች በመሠረታዊ ጉዳዮች በጥቅም የሚያስተሳስራቸው ውሎችን መፈራረማቸው ይታወቃል። ከብዙ በጥቂቱ ማንኛውም ኤርትራዊ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ፓስፖርት ወይም የመታወቂያ ደብተር እንደማያስፈልገው፤ኢትዮጵያ የጦር ካሳ ለኤርትራ መክፈል እንዳለባት፤ በኢትዮጵያ የሚኖሩ ኤርትራዊ ጡረተኞች የጡረታ ደመወዛቸው በኢትዮጵያ እንደሚከፈል፤የአስብ ወደብ ኢንሹራንስ በኢትዮጵያ እንደሚሸፍንና የመንገድ ሥራ ጥገናው በኢትዮጵያ ወጭ እንደሚከናወን፤ኤርትራዊያን ማንኛውንም ምርት ከኢትዮጵያ ሲገዙ ታክስ እንደማይከፍሉ …ወዘተ ተብለው 25 ወሎችን ዛሬ የመናፍቃን መሪ ነኝ በሚለውና የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ሲኖዶስ ከሁለት የከፈለው ታምራት ላይኔ በኩል ተፈራርመዋል።

ያ ሁሉ እከከኝ ልከክህ ከንቱ ውዳሴው ሳይውል ሳያድር ወደ ግጭት አመራ አንዴ አንዱ ሲገፋ ሌላ ጊዜ ደግሞ ተገፍቶ የነበረው ሲገፋ መቆየቱ ይታወቃል። ሸራሮ የነበረው የህወሃት ጦር ሻቢያ በኢትዮጵያ ድንበር ምሽግ እየሰራና እየተጠጋ መሆኑን ተመልክቶ የሻቢያን ምሽግ ሰብሮ በመግባት የሻቢያን ጦር በማባረር ባረንቱ ድረስ መሸኜቱንና በዚህ ጉዳይ የሠራዊቱ አመራሮች ማን አዟችሁ ነው ተብለው አዲስ አበባ ተጠርተው መገምገማቸውን አንድ የሠራዊቱ አመራር የነበረ አጭውቶኝ ነበር። ተገምጋሚዎቹ ከአዲስ አበባ ሳይለቁ የሻቢያ ጦር ተደራጅቶ በመመለስ ጥቃት መሰንዘሩና ከዚያ በኋላ የሻቢያ ጠብ አጫሪነት ግልጽ ሆኖ የሁለቱ የኢትዮ-ኤርትራው ጦርነት በሁሉም ወገን ታወጀ የህወሃት ጦር አስመራ ሲጠጋ ተመለስ ተብሎ ድርድሩ ተጀመረ ።ብዙ የአገር ኢኮኖሚ ወደመ ከሰማኒያ ሽህ የማያንሱ ውድ ኢትዮጵያውያን የጦርነት ሰለባ ሆኑ ሻቢያ በአሽናፊነት ደመደመ። እንግዲህ የመከላከያ ሠራዊቱ አገር ወዳድነት ወይም በሌላ አነጋገር ለአገሩ ለሉዓላዊነት የነበረው ወኔና ወታደራዊ ብቃቱ የታየው በዚህ ጊዜ ብቻ ነበር።

ለ/ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚስጡትን ተግባሮች ያከናውናል፦በኢትዮጵያችን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀው ህወሃት በምርጫ 97 ሲሸነፍ የምርጫ ሳጥን ለመዝረፍ ፤ በአሸባሪነት ስም የተቃዋሚ ኃይሎችን አንገት ለማስደፋት የታወጀ አዋጅ ካልሆነ በስተቀር የሕዝብን ሰላም የሚያደፈርስና ፀጥታን ሊያናጋ የሚችል ክስተት አለመፈጠሩን ብርቅም ዜና ስለማዳምጥ ስለማነብ የታየ ነገር እንደሌለ እርግጠኛ ነኝ። በነዚህ ተግባሮች የመከላከያ ሠራዊቱ እጁን አስገብቷል። ሀቁ ይህ ከሆነ የመከላከያ ሠራዊቱ የአገርን ሉዓላዊነት ያስከብራል ሲባል የማንን አገር የዚየትኛውን ሕዝብ አገር? ለህወሃት እሰየው የሚያስብል በሕዝብ ዘንድ ግን ከፍተኛ አደጋ ያደረሰ የተፈጥሮ አደጋ ደርሶ በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ቀውስ መፈጠሩን በዜና ሰምቸዋለሁ ምስሉንም አይቻለሁ። አንድ የመከላከያ ሠራዊት አባል የሆነ ግን ድጋፍ ሲሰጥ አልተመለከትኩም ወይንስ ይህ በሕግ አልተደነገገም? ይቅርታ የዚህን አገር የጦር ኃይል ተልዕኮ ስለማይ ነው።የኛዎቹ ከሕዝብ አብራክ የመጡ ቢሆኑም እንዲያልቅ በተፈረደበት ሕዝብ ጉዳይ መግባት እንደሌለበት የታዘዘ ይመስላል። እንግዲህ ከዚህ የባስ የሚመጣ ስለማይኖር ጨው ለራስህ ስትል ጣፍጥ ያለዚያ ድንጋይ ነው ብለው ይወረውሩሃል እንደተባለው የሰላማዊ ትግሉን ወይም የትጥቅ ትግሉን መቀላቀል የተሻለ አማራጭ እንደሚሆን ያለኝን ኃላፊነትና የዜግነት ግዴታየን በዚህች ጦማሬ እንካችሁ ብያለሁ።

4/ የመከላከያ ሠራዊት በማናቸውም ጊዜ ለሕገ-ምንግሥቱ ተገዥ ይሆናል።

ሕገ መንግሥቱን አስመልክቶ ሕግ አውጭው፤ ሕግ ተርጓሚውና ሕግ አስፈፃሚው ተግባራዊ ሳያደርጉት ፤ ሳያምኑበትና ለሕገ-መንግሥቱ ተገዥ ሳይሆኑ በውል ያልተብራራን ሕግ በህዝብ ላይ መጫንና ሕዝብ ስለ ህገ መንግሥት ያለውን ግንዛቤ እንዲዛባ ማድረግ ሥርዓት አልብኝነትን በንቃት ማስፋፋት ብቻ ሳይሆን ሕዝብን በነገር እየተነኮሱ በሕገ-መንግሥት ሽፋን እያጭበረበሩ ሰጥ ለጥ ብሎ እንዲገዛና ስለ ዴሞክራሲ፤ ፍትሕና ነፃነት ስለ ዜግነት መብቱ እንዳያስብ በታጠቀ ኃይል እያስፈራሩ የሥልጣን እድሜን ለማራዘም የሚያገለግል የመከላከያ ሠራዊት እንደትስ አድርጎ ነው ለሕገ መንግሥቱ ተገዥ ይሆናል የሚባለው? ይህን ጉዳይ በሚቀጥለው  ንኡስ ማጠቃለል ስለሚቻል የመከላከያ ሠራዊቱ በማናቸውም ጊዜ ለሕገ-መንግሥቱ ተገዥ ይሆናል የሚለው መቼ በሚል? አልፈዋለሁ።

5/ የመከላከያ ሠራዊት ተግባሩን ከፖለቲካ ድርጅቶች ወገናዊነት ነፃ በሆነ አኳኋን ያከናውናል። በሰለጠነውና ዴሞክራሲ በሰፈነበት አገር የአገር መከላከያ ሠራዊት ከድርጅታዊ ፖለቲካ ወይም ለመንግሥት ከመቆም አልፎ ህግን በማስከበር እንዴት እንደሚንቀሳቀስ እየተመለከትን ወደ አገራችን ስንመለስ በተለይም በዘመነ ህወሃት የአገር መከላከያ ሠራዊቱ ለገዥው ህወሃት በመቆም ገና ትእዛዝ ሳይወርድለት አድራጊ ፈጣሪነቱን በምን አይነት ሂደት እንደሚተረጉመው በስፋት ተመልክተነዋል። የተቃዋሚ ድርጅቶችን በማዋከብ አንድ ቦታ ላይ ብቻ ተወስነው እንዲቀመጡና፡ህዝቡን እንዳያገኙት በማድረግ ቀዳሚውን ሚና የሚጫወተውም ይኸው የመከላከያ ሠራዊት ነው። የሕዝብን እምብኝ ባይነትና የውስጥ ብሶት በመሣሪያ ኃይል አፍኖ ይዞ መኖር እንደማይቻል ከዚህ በፊት በዘውዳዊው ሥርዓት፤ በወታደራዊ አገዛዝ ሕዝቡ አስመስክሯል ይህ ከሆነ የሚጠበቀው «ማየት መልካም ሁሉን እይው ግን በትዳር ቀልዱን ተይው»የሚለውን የሙሉቀን መለሰን የግጥም ስንኝ እያስታወስኩ ለህወሃት የመከላከያ ሠራዊት የመጨረሻውን ምክሬን በዚህ መጣጥፌ እደመድማለሁ። ወደፊት ሕግ ተርጓሚ የሚባለውን የኢትዮጵያ የፍትሕ ሚንስቴርና በህወሃት ጊዜ ተወልደው በህወሃት ጊዜ ተምረው ዳኛ ስለሆኑትና ዳኝነትና ዳኛ በኢትዮጵያችን በሚል ርእስ አንድ ጹሑፍ ይዥ ለመምጣት እሞክራለሁ ። እስከዚያው ደህና እንሰንብት!

አዲሱ 2006 ዓ/ም የሰላም ፤ የጤና ፤ የመተሳሰቢያ ፤ የእድገትና የድል ዘመን ይሁንልን!!

ቅዳሜ ከሰዓትን ከአቶ ግርማ ሰይፉ ጋር በቶሮንቶና ኦታዋ ቆይታ ያድርጉ (Toronto City Hall)

አውስትራሊያን ከኢትዮጵያ ጋር የማመሳሰል ሕልም

$
0
0

 መስከረም 8 2013

ከታክሎ ተሾመ

 

አውስትራሊያ ቀለመ ብዙ አገር  ናት። ከ200 በላይ  ቋንቋ  የሚናገሩባት በዝንቅ ማኅበረሰብ የተመሰረተች፤በጥሬ ማዕደኗ፤ ወንድ ሴት ሳይል የሰዎች የተፈጥሮ ሰብአዊ መብት የተከበረባት አገር ማን ትባላለች ብሎ ለሚጠይቅ  መልሱ አውስትራሊያ  ናት ብሎ በድፍረት መናገር ይቻላል።

 

አዎ እርግጥ ነው አውስትራሊያ በስደት የምኖርባት አገር ናት፤ ከዚህ በፊት ዴሞክራሲ የሚባል ነገር ስላላየሁ  ከዚህች አገር ውጭ ዴሞክራሲ ያለ መስሎ ስላልታየኝ  ወደድኳት፤ ተመችታኛለች። መፋቀርና መቻላል  ስላለ ብዙ እድሎችና ሕይወትን የሚለውጡ አጋጣሚዎች  የተመቻቹ  ናቸው።

 

አውስትራሊያን  ጥሩ  አገርና  መልካም ሕዝብ ያሰኛት የተለያዩ ምክንያቶች  አሏት። አውስትራሊያ ራሷን  የቻለች አገር  ከመሆኗ  በፊት  እርግጥ ነው ብዙ ጦርነቶች  ተካሂደውባታል።  ይሁን እንጂ ራዕይ ባላቸው ሰዎች አማካኝነት ከችግር  ተላቃ  ዴሞክራሲ የሰፈነባት አገር ለመሆን የቻለቸው  ሌበርና ሊበራል  የተሰኙ ሁለት አንጋፋ ፓሪቲዎች  በመፈጠራቸው  ነው። ሁለቱ  ፓርቲዎች  የየራሳቸውን  የፖለቲካ ፕሮግራም ይዘው  ሲከራከሩ ከዚህ ቀደም የሰሩት ሥራ እየተገመገመ  ሕዝቡ የሚበጀውን  ይመርጣል።

 

በአውስትራሊያ የፌደራሊ ምርጫ ሲደረገ  ጦርሰራዊት፤ ፖሊስ ወይም ደህንነት የሚባሉ በየምርጫ ጣቢያው  አካባቢ ድርሽ አይሉም። የአውስትራሊያ ዜጋ ሁሉም የሚበጀውን ፓርቲ የመምረጥ ኃላፊትም ሆነ ግዴታ አለበት። መስከረም 7 ቀን 2013 ቅዳሜ  ከጧቱን 8 ሰዓት  ጀምሮ እስከ ምሽቱ 6 ሰዓት ድረስ  ምርጫ ተካሂዷል።  በዚህ ወቅት ለውድድር  የቀረቡ፤ የአውስትራሊያ ሌበር ፓርቲና የአውስትራሊያ ሊበራል ፓርቲ በዋናነት ሲወዳደሩ እንዲሁ አናሳ የሚባሉ 1 ናሽናል ፓርቲ 2  ግሪን ፓርቲ  3 የግል ተወዳዳሪዎች 4  ዩናይትድ ፓርቲ  የመሳሰሉት ለውድድር  ቀርበው  ነበር። ከ2007  እስከ  2013 ዓ.ም ድረስ  የአውስትራሊያ  የሠራተኞች ፓርቲ ሌበር ሥልጣን ላይ  ነበር። ነገር ግን መስከረም 7 ቀን 2013 ዓ.ም በተደረገው ምርጫ ከምሸቱ 8.45 ሰዓት ላይ ተቃዋሚ  የነበረው  የአውስትራሊያ ሊበራል ፓርቲ 88 ድምጽ ሲያገኝ ሌበር ፓርቲ 54  ድምጽ አግኝቶ የሥልጣን ባለቤት ለመሆን በቅቷል።

 

ከላይ እንዳልኩት በምርጫ ወቅት የሳጥን ስርቆት አልነበረም፤ ሥልጣን ላይ የነበረው ሥልጣን አለቅም ብሎ ጦር አላዘመተም። እንዲያውም አሸናፊውን እንኳን ደስ ያለህ በማለት ወደፊት እየተመካከሩ አገርና ሕዝብ ለመምራት ቃል ኪዳን በመግባት የእለቱ ምርጫ  ተጠናቋል።

 

ይህንች አጭር ጽሁፍ ላቀርብ የተገደድኩበት ምክንያት የአውስትራሊያው ምርጫ በኢትዮጵያ መቼ ይሆን የሚደገም የሚለው ጥያቄ  ስላስገደደኝ  ነው። እርግጥ ነው፤ አንድ አገር  እንደ አገር ሲቆረቆር ብዙ ውጣ ውረዶችን  ማለፍ ግድ  እንደሚለው  ይታወቃል። ከታሪክ  መረዳት  እንደሚቻለው አገራችን ኢትዮጵያ ከዓለም ቀደምት መሆኗን ነው የሚነግረን። ነገር ግን ረጅም  እድሜ  ብታስቆጥርም ከአብራኳ በሚፈጠሩ መንግሥታት ሕዝቦቿ  በነፃነት እንደ ዜጋ እየኖሩ አይደለም።

 

ኢትዮጵያ ከዓለም የሚወዳደሩ ምሁራን ልጆች እንዳሏት አይካድም። ነገር ግን አገርና ሕዝብን ለመታደግ የታደለች አገር  አይደለችም። በመሆኑም  በየጊዜው  እስር፤ ስደትና ሞት የዘወትር እጣ ፈንታችን  ሆኗል። ይሁን እንጂ ችግሮችን አስወግዶ ዴሞክራሲያዊ የሆነ በሕዝብ የሚመረጥ መንግሥት ለማምጣት ረጅም  ዓመታት የተለያዩ ትግሎች ተካሂደዋል። ለትግሉ ስኬት አለመበቃት የተለያዩ ምክንያቶች እንዳሉ አይካድም።  ከፓለቲካ ድርጅት  መሪዎች  እስከ ግለሰቦች ድረስ ያለውን ብሎም ከሕይወታችን ጋር በንፅፅር ማስቀመጡ ተገቢ  ይመስለኛል።

በመጀመሪያ ደረጃ ዓላማን  በትክክል በመረዳት ወደየትኛው መስመር ነው የምንጓዝ፤ የምንታገለው ለጐጂ ወይስ ለጥሩ ዓላማ የሚለው ተለይቶ ከታወቀ  ትግሉ ትርጉም ያለውና የተሟላ  ይሆናል። ይህ ማለት የትግሉ ዓላማና የጉዟችን አቅጣጫ ከታወቀ ሕዝቡ ሊከተል ይችላል። ከተለያዩ ዓለም ትግሎች ተሞክሮ መረዳት እንደሚቻለው  ትግላቸው ውጤት ከማምጣቱ በፊት  ብዙ እልህ አስጨራሽ ትግልን ማለፍ ይጠበቅባቸው ነበር።  በመሆኑም  በደቡብ  አፍሪካ፤ በሰሜን  አሜሪካና በሌሎች አገራት ለነፃነት የታገሉ ድርጅቶች ለአሸናፊነት የበቁት  ሽንፈትንና  ተስፋ  መቁረጥን በፀጋ  መቀበልን  ባለመፈለጋቸው  ነው።

 

ከዚህ በፊት የተደረጉ ትግሎች በድርጅቶችም ሆነ በግለሰቦች ላይ አስደሳችና አሳዛኝ ገጠመኞችን ተመልሰን ስንቃኝ ብዙ ትምህርቶችን መቅሰም  ይቻላል። ለአገራችውና ለሕዝባቸው ሲሉ ከዚህ በፊት የተሸነፉ ፓርቲዎች በችግሮች ተስፋ  ሲቆርጡ  አንዳንዶች  ዛሬም ድረስ  የሚችሉትን  ያህል  እየተፈረጋገጡ  ይገኛሉ።

 

 

በአገራችን የተፈጠሩ በርካታ ተቃዋሚ ድርጅቶች በውስጥና በውጭ  እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ። ይሁን እንጂ ስንቶች ናቸው መሰናክሎችን ማለፍ የሚችሉ ብለን ስንጠይቅ በጣት የሚቆጠሩ ሆነው እናገኛቸዋለን። በመጀመሪያ ደረጃ  ይጠንክሩም  ይኩሰሱ  አገር ቤት ውስጥ  የሚንቀሳቀሱ  ድርጅቶች የለውጥ ተስፋ እንደሚሆኑ እገምታለሁ።

 

ከላይ ከተጠቀሱት  የተስፋ ፓርቲዎች በተጨማሪ በውጭ የተሰባሰቡ ጅርጅቶችም እንዲሁ የአጋዥነት ግዴታ  እንዳለባቸው ብዙዎች ሲናገሩ እየተደመጠ ነው። እርግጥ ነው በውጭ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ከጉልበት እስከ ገንዘብ ድረስ የሚችለውን ያህል ለአገሩ እያበረከተ መሆኑን ማንም አይክድም። ነገር ግን  አንዳንድ የፖለቲካ ድርጅቶች እርስ በርሳቸው በሚያደርጉት ፍክቻ  ትግሉ ወጥነት ኑሮት ስኬታማ እንዳይሆን መሰናክል መፍጠሩ አልቀረም።

 

ዋናው ነገር ግን ትግሉ ስኬታማ ሊሆን የሚችለው አገር ቤት በሚደረገው ትግል ስለመሆኑ አምንበታለሁ፤ ብዙዎችም አባባሌን  የሚስማሙበት ይመስለኛል። እነዚህ የአገር ቤት ተቃዋሚ ድርጅቶች ለአገራቸውና ለሕዝባቸው  መብት  መከበር  ሲሉ ብዙዎች የእሳት ረመጥ እስከ መሆን ደርሰዋል። እስር፤ ግርፋት ቢደርስባቸው የጀመሩትን ሰላማዊ ሕዝባዊ ተቃውሞ ትግል ከግብ ለማድረስ ቆርጠው መነሳታቸውን  በአንደበታቸው  እየሰማንና  ተግባራቸውን  እያየን  ነው።

 

እርግጥ ነው የአገር ቤት ድርጅቶች ለመስዋዕትነት መዘጋጀታቸው ቢያስደስትም የጀመሩት ትግል ውጤት እንዲያመጣ ከተፈለገ  ማበረታቻ  ያስፈልጋቸዋል። ይህ ሲባል  በስደት የተበተነው ትውልደ ኢትዮጵያዊና የፖለቲካ ድርጅቶች በሞራል፤ በገንዘብ፤ በዲፕሎማሲ፤ አገር ቤት ገብቶ አብሮ  መታገልን ግድ ይላል። እያንዳንዱ ለአገሩና ለሕዝቡ ሲል የራስ ተነሳሽነት ስሜት  ካለውና ከልብ የሚታገል ከሆነ ውጤታማ  ይሆናል። ብሎም የድርጅት መሪዎች ተነሳሽነታቸውም ቢሆን ዘላቂነት ይኖረዋል። ለዚህ ደግሞ ኃይል ሊሆን የሚችለው እምነት መሆኑ  አያጠያይቅም።  ስለሆነም እያንዳንዱ ኃላፊነትን መቀበል ሲጀምርና ወደ አንድ መመጣት ሲችል የትግሉ አቅጣጫ  ይስተካከላል ብሎ  በድፍረት  መናገር ቢያስ  ነው።

 

ከመግቢያየ ላይ  እንዳልኩት አውስትራሊያ  ዛሬ ከደረሰችበት የእድገት ደረጃ ከመድረሷ በፊት ብዙ ፈተናዎችን እንዳለፈች ከአውስትራሊያ ቤተ መጽሃፍት ውስጥ ገብቶ የታሪክ መጽሕፍቶችን ለሚያገላብጥ አስቀያሚና አስደሳች ታሪካቸው በሚገባ ተቀምጧል።  መስከረም 7 2013  በአውስትራሊ የተካሄደውን  የመንግሥት  ምርጫ በቅርበት ማየት ብቻ ሳይሆ  ተሳትፊ  እንዳየሁት ከሆነ  ተሽናፊው ለአሸናፊው ሥልጣኑን በሰላም አስረከቧል።

 

ከላይ ይህን ካልኩ ዘንዳ  ከምርጫ በኋላ   ቤቴ ቁጭ ብየ ቴሌቭዝኝ እየተመለከትኩ እግሬን ሳይሆን አእምሮየን  ኢትዮጵያ አድርጌ ጉደኛዋ አገራችንስ በምን ላይ  እንደምትገኝና የ1997 ቱ  ምርጫ ተመልሸ ስቃኝ አዘንኩ፤ ተከዝኩ እርር ትክን አልኩ። እርግጥ ነው ሃዘኔ ግን ተስፋን  ያዘለ ነው። ምክንያቱም ከዚህ ቀደም በተናጥል ይደረግ የነበረው ትግል አሁን፤አሁን በተቀናጀ መልክ  ሰላማዊ ሕዝባዊ ትግል ለማካሄድ  መስማማታቸውን እየሰማን ነው። ስለሆነም  ተስፋ ጥሩ ነው “ቸር  ተመኝ በጐ “እንድታገኝ ይሉየል በአውስትራሊያ ያየሁት  የሰላም የሥልጣን ዝውውር በኢትዮጵያም ይደገማል የሚል የተፍሳ  ስንቅ ተሸክሜአለሁ።

 

ሁሉም ፊቱን ወደ ሰላም እንዲያዞር ኃያሉ ልዑል እግዜአብዜ ይርዳን።

ኢሕአፓ አንድና አንድ ብቻ ነው ከኢሕአፓ የእርምት እንቅስቃሴ የተሰጠ መግለጫ !

ግንቡን ለማፍረስ። በአገር ውስጥ በአሉና በውጪ እየተንቀሳቀሱ ባሉ ድርጅቶች መሀል አዋጩ ግንኙነት። በዳዊት ዳባ – Friday, September 06, 2013

$
0
0

ገዥዎቻችን መከፋፈል ስልጣንን ለሀያ ሁለት አመታት ያፀኑበት ዋና መሳርያቸው ነው። ሁሌም ለማራራቅ አጠንክረው ሲሰሩባቸው ከኖሩት ማህበረሰባዊ ልዩነቶች አንዱ በአገር ቤትና በውጪ አገራት የሚኖረው ኢትዮጵያዊ መሀከልም ነው። አሁን አሁን ይህ በተጠናከረና በረቀቀ መንገድ እየተሰራበት እንዳለ በግልፅ ይታያል። በወያኔዎች ዘንድ ትላልቆቹን መህበረሰባዊ ልዩነቶች አይደለም ከቅርበት አኳያ የተወሰኑ ዜጎች የሀመረኖ የቀሩት ደግሞ የጎርፍ አሶጋጅ እድርተኛ መሆናቸው እንደ አንድ ልዩነት ይወሰዳል። ወስደውትም በጠረጴዛ ላይ ያስተኙታል። መዶሻና መሮ ይዘው ለማለያየት መቆርቆርን ታላቅ ሞያ አድርገው ይዘውታል። የዳበረ ልምድ አለን ብለው የሚያቅራሩበትም ነው።

በአገር ቤትና በውጪ በሚኖረው ኢትዮጵያዊ መሀል እየፈለፈሉ ያሉት ልዩነት በሁሉም ዘርፍ የተከፋፈለ ማሀበረሰብ እየፈጠርን መሄድ ለአገዛዝ ያመቸናል ከሚለው መነሻ አላማቸው በተጨማሪ ዋናው ጉዳይ በውጪ አገራት መሰረታቸውን አድርገው የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ትግሉ ላይ ሊያሳርፉ የሚችሉትን ጉልበትና ተቀባይነት መቀነስ ነው። ልፅፍብት ያሰብኩት ይህንኑ በድርጅቶቹ ማሀል ሊኖር ስለሚገባው መልካም ግንኙነት ነው።

በውጪ አገራት እየተንቀሳቀሱ ያሉ ኢትዬጵያዊ የፖለቲካ ድርጅቶች በሙሉ እንቅስቃሴያቸውን ከውጭ ማድረግ ምርጫቸው አይደለም። መሰረታቸውን በውጪ አገራት እንዲያደርጉ ያደረጋቸው የበዙት ተክልክለው ነው፤ የቀሩት ያለውን ያፈና ግዙፍነት ግምት ውስጥ አስገብተው መሰረታቸውን በውጭ አድርግው መታገልን የተሻላ አማራጭ ሆኖ አግኝተውት ነው ብሎ በሁለት መመደብ ይቻላል። ሁለተኛው ምድብ ውስጥ ያሉት የበዙት ለሰባዊ መብት መከበር የተቋቋሙ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ሲሆኑ ጥቂት ንቅናቄዎችና የፖለቲካ ድርጅቶች አሉብት።
ወያኔ የዳበረ ልምድና ተሞክሮ ያላቸውን ድርጅቶች ለይስሙላ እንኳ ያለውን የህግ አግባብ እንኳ ሳይከተል ነው በአገራቸው ፖለቲካ ተሳትፎ እንዳያደርጉ በጠዋቱ ጀምሮ የከለከላቸው። ሌሎችን በይስሙላው ፓርላማ ፍርደ ገምድል ውሳኔ አግዷቸዋል። ባይከለከሉም ኖሮ አዋጭ አደርገው በመረጡት የትግል አይነት የተነሳ መሰረታቸውን በግላጭ በአገር ውስጥ አድርገው መንቀሳቀስ እንደማይችሉ ግልፅ ነው። የበዙትና ብሄር ተከል የሆኑት ድርጅቶች ወያኔ ወደ ስልጣን ከመጣ በሗላ በሰላማዊና በህጋዊ መንገድ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ለማድረግ ሞክረው ብዙ መሰዋትነት አስክፈሏቸው በጭራሽ በአገር ውስጥ መቆየት የማይቻሉ መሆኑን አይተው ሌላ አማራጭ ፍለጋ የወጡ ናቸው።

ወያኔዎች መሰረታቸው በውጪ የሆኑ ድርጅቶችን በሙሉ ጦርነት ናፋቂዎች፤ ህገመንግስት ናጆች፤ ፤ ሽብርተኞች፤ ተገንጣዮች፤ የደርግ ርዝራዦች፤ የነፍጠኛ ስርአት ለመመለስ የሚጥሩ አይነት ክሶች ለድፎባቸዋል። ሁሉም ክሶቹ መሰረት የሌላቸውና ሆን ተብሎ ለልዩነት መፍጠርያና ለማሸማቀቂያ ዌያኔ የፈበረካቸው ናቸው። አላማው ድርጅቶቹ እውቀታቸውን፤ ድርጅታዊ ጥንካሬያቸውንና የገንዘብ አቅማቸውን በአገር ውስጥ ከሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ጋር አቀናጅተው ትግሉ ላይ ጉልበት በሚሆነን መንገድ መጠቀም እንዳይችሉ ለማድረግ ነው። በእርግጥ እስካሁን መሰረታዊ ልዩነት መፍጠር በአይችሉም ተቀናጅተው ትግሉን ለማካሄድ ቴክኒካል የሆኑ እንቅፋቶችን ግን መፍጠር ችለዋል ማለት ይቻላል።

በአገር ውስጥና በውጪ ባሉ ድርጅቶቹ መሀል መፈራራት እያደገ ነው። አገዛዙ ሊከለክልና ሊያስፈራራ የሚችለው በአገር ቤት ያሉ ድርጅቶችን ነው። ስለዚህም አባላትና አመራሮቻቸውን አንዴ ከዚህ አንዴ ከዛኛው ውጪ ካሉ ድርጅት ጋር ሲዶልቱ ይዘናል በሚል ላፈና ምክንያት እየተጠቀመበት ነው ። እነዚህ ህገወጥ የሀይል እርምጃዎቹ ለማሸማቀቂያና እንደመቀጣጫ እንዲያገለግሉ አስቦበት የሚወስዳቸው ናቸው። በተወሰነ መልኩ እየሰራለት ነው ማለት ይቻላል። በአገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የየድርጅቶቹ አመራሮች በሚሰጧቸው ቃለ መጠይቆች ሁሉ በምንም መንገድ ውጪ ካሉ ድርጅቶች ተባብሮ ለመታገል አይደለም የሚያነካካቸውና አገዛዙ ለምክንያት ደግሞ ይጠቀምባቸዋል ብለው ለሚያስቧቸው ጥያቄዎች የሚሰጧቸው መልሶች ጊዜ ተወስዶባቸው፤ ቃላት ፈልገውና ጥንቃቄ በተሞላበት የሚሰጧቸው መሆናቸው የሚታይ ነው። እንዲህ የሆነበትን ምክንያት የምንረዳውም ቢሆንም ወያንያዊ የሚመስሉበት ጊዜም አለ። አንዳንዴ ምክንያታዊነትና ሀቅ ሲጎድላቸውም ይታያል። በአገር ውስጥ ያለው የበዛው ህዝብ ካንድ በኩልና ተደጋጋሚነት ባለው ሁኔታ ውሸት በየቀኑ የሚመገብ መሆኑ ተጨምሮበት በተቃዋሚዎች በኩሉ ያለው መሽኮርመም ሲጨመርበት በእጅጉ ሊያወናበድ ይችላል የሚል ፍረሀት አለ።

በውጪ ያሉ ድርጅቶቹ ጉዳዩን በማወሳሰብና ያገዛዙን መከፋፈልና ህዝባዊ ተቀባይነት የማሳጣትን ተንኮል ውጤታማ በማድረገ ረግድ አልቦዘኑም። ወይ መፍትሄው ላይ በበቂ እየሰሩበት አይደልም። መሰረታዊ ያልሆኑ ልዩነቶች ጣሪያ እስኪነኩ ሲጮሁ ይሰማሉ። በአገር ቤትና በውጪ መሰረታቸውን ስላደረጉ እንዲሁ በሁኔታዎች አስገዳጅነት ምርጫ ባደረጉት የትግል አይነት ልዩነት ምክንያት መወዛገብ የተለመደ ነው። በአገር ውስጥ ያሉ ድርጅቶች የሚንቀሳቀሱበት እጅግ በጣም አስቸጋሪ ሁኔታ በአግባቡ መረዳት ካለመቻል በሚሰነዘሩ ትችቶችና በየቃለ መጠይቁ በማይጠፉ አላስፈላጊ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው ምክንያት ለሰጣ አገባ በር መክፈትን ሊቀንሱት አልቻሉም። በአጠቃላይ ሁሉ በጁ ሆኖ እሱ ብቻ በደንብ መሰማት ቢሚችልበት ሁኔታ ጭንብል የሚለብሱ አሸባሪዎች ወይ ጦርነት ናፋቂ አድርጎ ሊስላቸው እየሰራ ላለ አካል መፍትሄ ይሆናል ብለው የወሰዱት ህዝባችን ይህን ነጭ ውሸት አይገዛምና አልፎ አልፎ አይደለንም አይነት መከላከያ ብቻ ነው። በአገር ውስጥ ያሉ ድርጅቶችን ጉልበት እንዲሰማቸውና ተቀባይነታቸው እንዲጨምር ማድረግን ስራቸው ሲያደርጉ አይታዩም። እንደውም ባንጻራዊ ማንኳሰሱ ነው የሚበዛው።

አገዛዙ በውጪ ባሉና በአገር ቤት ባሉ ድርጅቶች መሀል ሊያቆም የሚያስበው የልዩነት ግንብ ለመናድ ቀላል የሆነ መፍትሄ ያለው ይመስለኛል። መፍትሄው የሁለትዬሽና ነግር ግን በተናጠል ሊወስዱት የሚቻላቸው ፖለቲካዊ እርምጃዎች ናቸው። ምንም ጉዳት የሌለው ጠቅላላ ያገሪችንን ፖለቲካዊ ችግሮች ተረድቶ ቀናነትን የሚፈልግ ፖለቲካዊ ውሳኔ ግን ነው። አሁን ባለንበት ሁኔታ በጋራ መምከር የሚችሉበት ሁኔታ ስለሌለ በራስ አነሳሽነት በተናጠል የሚደረሰበት ፖለቲካዊ አቋም ነው።

1. በውጪ ያሉ ድርጅቶች ቢቻል ቢቻል በህብረት ካለሆነም በተናጠል ትልቁን ወይ ሙሉ የሆነ ፖለቲካዊ እውቅና በአገር ውስጥ ላሉ ድርጅቶች በይፋ መስጠት ነው። {በአገር ውስጥ ያሉ ድርጅቶች ሰላሳ ሶስቱ በሚል በአንድ መሰባሰባቸው አሁን ስራውን አመቺ አድርጎታል}
2. በአገር ውስጥ ያሉ በህጋዊ መንገድ የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች በውጪ መሰረታቸውን አድርገው በተለያየ አይነት መንገድ አገዛዙን የሚታገል ድርጅቶች ይህን ምርጫ ማድረጋቸው እንደ አንድ አገራዊ ችግር ማየት መጀመር አለባቸው። መፍትሄ ሰሪ መሆን ነው። እንደ መፍትሄ አቅራቢ መናገርና መተወን መጀምር ነው ብለሀቱ።

የሞኝ ሀሳብ ብላችሁ እንዳታቆሙ ቀጥላችሁ አንብቡኝ። አንዳንዴ ውስብስብና አስቸጋሪ ለሚመስል ችግር ቀላልና የሞኝ የመሰለ መፍትሄ ሊኖረው ይችላል።
በውጪም ሆን በአገር ውስጥ እየታገሉ ያሉ ድርጅቶች የሚታገሉት አገዛዛዊ ስረአት ጥለው አገዛዛዊ ለመሆን አይደለም። የሚመኙ ቢኖሩም እንኳ ከዚህ በሗላ አይቻሉም። በተረፈ የየድርጅቶቹ አገራዊ ፖሊሲ ተመራጭነትና ትክክለኛነት በምርጫ ሂደት በህዝብ የሚዳኝ ስለሆነ ህዘብ የመምረጥ አቅሙን እስኪያገኝ ለግንዛቤ ማሳደጊያ ልንወያይበት የምንችላቸው ናቸው። ድርጅቶች የጋራ ውሳኔ ለማሳለፍም ሆነ እርቀው ሄድው ለመተባበር የግድ ሁሉንም ፖሊሲያዊ ጉዳዬች በጠረቤዛ ዙሪያ እየተወያዩ ቁጭ ብለው ሊስማሙበት የሚገባ አይደልም። ቢሞክሩትም በሁሉም ዘርፍ ፖሊሲዎች ላይ በመነጋገር አንድ የሚያስማማ ተመራጭ ፖሊሲ አያወጡም። በመወያየት አይደለም እሳት ላይ ጥደው ሲቀቅሏቸው ቢኖሩም ልዩነቶቹ ተዋህደው ሁሉ የሚስማማበት አንድ አማራጭ ሀሳብ ብቻ በየዘርፋቸው አይወጣቸውም። የተለያዩ አማራጭ ፖሊሲ ሀሳቦች ሁሌም ይኖራሉ። መኖርም አለባቸው። ከፖሊሲ ልዩነቶች መለስ ያሉት በሙሉ ምርጫ ያደረጉትን የትግል አይነት ጨምሮ እያወጣን ብናያቸው እዴሜያቸው ከአገዛዙ ጋር የሚያበቃ ነው። በአገር ውስጥና በውጪ ባሉ ድርጅቶች አዋጭ የሆነው መንገድ ብዬ ያስቀመጥኩት መፍትሄ ሀሳብ በድርጅቶቹ መሀል ያሉ ከአገዛዙ ጋር ከሚያበቁ ልዩነቶች ተነስቼ ነው።

ወያኔ በአገር ውሰጥና በውጪ አገር ባለው ህዝብ እንዲሁ በአገር ቤትና በውጪ አገራት መሰረታቸውን አድርገው በሚታገሉ ድርጅቶች መሃል ሊያቆም የሚጥረው የልዩነት ግንብ የሚሰራለት ተቃዋሚና የተለየ አይነት አላማና ግብ ይዞ ሚንቀሳቀስ ሌላ አይነት ተቃዋሚ ደግሞ ካለ ነው። አለበለዚያ ባይኖርም እንዳለ አድርጎ በህዝብ ዘንድ መሳል ከቻለ ብቻ ነው። ድርጅቶች መሰረታቸውን አገር ውስጥና ወጪ እንዲሁ ደግሞ በሁለገብ ትግል ወይ በሰላማዊና ህጋዊ በሆነ መንገድ እየታገሉ ስላሉ ብቻ የልዩነት ግንብ ማቆም አይቻለውም። ከቻለ ባጭሩ ያለውን ያላማን እንድነት እንዲሰማና እንዲታይ ማድርግ ድርጅቶቹ አልቻሉም ማለት ነው።

ማናም እንደሚረዳው ችግር የሆነው በድርጅቶቹ መሃል ያለ ያላማና የግብ ልዩነት መኖሩ አይደለም። በአገር ውስጥ እያታገሉ ያሉ ድርጅቶች አፈሙዝ ተደቅኖባቸው ስለሚንቀሳቀሱ በውጪ ካሉ ድርጅቶች ጋር ያላቸውን ያለማ አንድነት እንዲሰማ አድርገው ለማወጅ ተቸግረዋል። በውጪ ያሉ ድርጅቶች ደግሞ አስፈላጊነቱ እስካሁን አልዞረላቸውም። ሲጀመር ወያኔ ለሚያቀርባቸው የፈጠራ ክሶችን ለመከላከል ከመሞከር አዋጩ መንገድ የነበረው አገር ውስጥ ካሉ ድርጅቶች ጋር ያለውን ያላማ አንድነት እንዲሰማና የሚታይ ማድረጉ ነበር። ወደፊትም ይህን ሀሳብ ጠቃሚ ሆነው አግኝተውት ሊጠቀሙበት ካሰቡ አንድነታቸውን አለም እንዲያውቀው የማድረጉንና ከፍተኛውን ፖለቲካዊ እውቅና በአገር ውስጥ ላሉና በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ ለሚታገሉ ድርጅቶች የመስጠቱን የመጀምርያውን ፖለቲከዊ እርምጃ መውሰድ ያለባቸው በውጪ ያሉ ተቃዋሚዎች መሆን አለባቸው።

መሰረታቸው በውጪ ከሆኑ ድርጅቶች የሚጠበቀው ሙሉ ፖለቲካዊ እውቅናና ለህጋዊ ተቃዋሚዎች ጉልበት መስጠት።

- ችግራችን ስልጣን ላይ ካለው አንባገነናዊ አድሏዊ ጨፍጫፊ ፓርቲ ጋር ነው። ገዢው ፓርቲ በአገራችን ፖለቲካ እንዳንካፈል ከልክሎናል። መሰረታችን በውጪ አድርግን የምንታገለው ገዢው ፓርቲ ስልጣን ላይ እስካለ ብቻ ነው። በቀጣይ በአገር ውስጥ ያሉ ህጋዊ ተቃዋሚ ድርጅቶች ከሚያቆሙት መንግስት ጋር በሰላማዊና የአገሪቷ ህግ በሚያዘው መሰረት በአገራችን ገብተን በሰላማዊ የፖለቲካ ውድድር ውስጥ እንካፈላለን።
- ስልጣን ላይ ባለው አገዛዝ አንባገናኒወነት ምክንያት ተገደን ምርጫ ያደረግነውን የትግል መንገድ አገር ውስጥ ያሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ስልጣን የያዙ እለት የምናቆመው ነው። የመንግስት ስልጣን ይዘው አይደለም ከዛም በፊት በተቀናቃኝ ፓርቲነትም ደረጃ ሆነው ህዝብ አለምንም ጣልቃ ገብነትና ወከባ በሚደረግ ምርጫ የሚፈልገውን መንግስት መምረጥ አሁን ይችላል ብለው ማረጋገጫ መስጠት ከቻሉና ለደህንነታችንና ላጠቃላይ ሂደቱ ሀላፊነት የመስጠት አቅሙ ሲገነቡና ሀይላቸውን ልናየው ስንችል እንዲሁ እነሱም ሀላፊነት እንወስዳለን ሲሉ ላሁኑ ምርጫ ያደረግነውን ትግል እርግፍ አድርገን ትተን በህጋዊና በሰላማዊ መንገድ በመርጫ ለመሳተፍ መሰረታችንን በአገር ቤት እናደርጋለን።
-በሰላማዊና በህጋዊ መንገድ አገር ቤት እየተንቀሳቀሱ ያሉት ድርጅቶች የያዙት አገራዊ እራአይ ላገራችን የሚጠቅም ነው። በኢትዮጵያችን ዲሞክራሲያዊ ስረአትን ማስፈንና አገሪቷን የተሻለ የእድገት ደረጃ ላይ ማድረስ በደንብ ይችላሉ። ህዝባችንን ወደ ብልፅግና ለመውሰድ በሚያደርጉት ሁሉ መቶ በመቶ አብረናቸው ነን። ሙሉ እገዛችን ይኖራቸዋል።
- በአገር ውስጥ ያሉ ድርጅቶችንም ሆነ በየድርጅቶቹ ስር ሆነው ለለውጥ እየታገሉ ያሉ ዜጎቻችን ሆን ብለው አገራቸውንና ህዝባቸውን የሚጎድ አይደሉም። የአገራችን ሉአላዊነትና ጥቅሟን በማስጠበቅ ረገድ አሁን በተቃዋሚነት ሆነው ሆነ መንግስት ቢሆኑ በሚወስዷቸው እርምጃዎች እናምናቸዋለን። ተሳስተው ጎጂ ሊሆን የሚችል አቋም ወይ እርምጃ ሊወስድ ቢያስቡ እንኳ ቁጭ ብለን መክረን ለመተራረም አገር ውስጥ በሰላምና በህጋዊ ምንገድ ከሚታገሉ ድርጅቶች ጋር በደንብ እንችላለን።
- በአገራችን የልተመለሱና እየጨመሩ የሄዱትን መሰረታዊ የመብት ጥያቄዎች በበቂ ለመመለስ አገዛዙ አልቻለም። አገር ቤት በሰላምና በህጋዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ያሉ ድርጅቶች ግን ሊመልሷቸው ይችላሉ። እስካሁን በአገሪቷ ወስጥ በተለያየ ጊዜ የሚፈጠሩ ችግሮችን የሚያዩበትና መፈታት አለበት የሚሉበት መንገድ በተጨማሪም ቅሬታዎች መያዝ አለባቸው ብለው የሚያቀርቧቸው የመፍትሄ ሀሳቦች የሚስማሙን ናቸው። ለወደፊቱም በዚህ አይነት ጉዳይ ላይ እየተመካከርን ተስማምተን መስራት እንችላለን።
- አገዛዙ ከኛ ጋር መደራደር የሚያስፈልግበት ሁኔታ ብዙም አይታየንም። አገር ውስጥ ካሉትና ሰላማዊና ህጋዊ የሆኑትን ድርጅቶች ጥያቄ መመለስ ከቻለና የሚደሰቱበትን ስምምነት መቋጨት ሲችል በርግጠኛነት የበዛው ጉዳይ በቀጥታ ከኛም ጋር የሚያስማማው ነው የሚሆነው።
- በአገር ውስጥ ያሉ ድርጅቶች እያደረጉት ያለውን ህጋዊና ሰላማዊ ትግል የምንደግፈው ነው። በጣም በአአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ለውጥ ለማምጣት እየጣሩ እንዳሉ ብናውቅም አፈናውን ሊቋቋሙት እስከቻሉ ሰላማዊና ህጋዊ ትግላቸውን ብቻ አጠንክረው እንዲቀጥሉ እንሻለን።

ሙሉ እውቅናው ይህንን አይነት መምሰል አለበት። በአዋቂዎች ሊከሸን ሊጨመርበት ሊቀነስ ይችላል። ይህ ፖለቲካዊ እርምጃ መሰረታቸውን በውጪ አድርገው በየትኛውም አይነት ትግል እየታገሉ ያሉ ድርጅቶች ትግላቸውን አሁን በሚያካሂድበት መንገድ ለመቀጠል ሳንካ አይሆንም። እንደውም አጠንክረው እንዲቀጥሉ ያግዛል። ይህ ፖለቲካል እርምጃ በየትኛውም መንገድ ትግሉን የሚጎዳበት ወይ በሂደት ድርጅቶችን አጣብቂኝ ውስጥ የሚከትበት መንገድ ቢኖረው ኖሮ አይቀርብም ነበር። አንባቢ ይህ እርምጃ በየትኝውም አቅጣጫ ያልታዩ ጦሶች ልታዩበት ከቻላችሁ ግን ሁሌም ብታሳዩ ጠቃሚ ነው። በተረፈ ደርጅቶች አገላብጠው ሳያዩት አይገለገሉበትም።

በአገር ቤት ያሉ ድርጅቶች የመተባበር ሚስጥሩ የተገለፀላቸው ይመስላል። በተቃዋሚዎች መሃል የኔ ይሻላል የምርጫ ፖለቲካ የትም እንደማያደርስ ገበቷቸዋል። የሚገርመው የፉጉም ቢሆን የምርጫ ጉዳይ ውስጥ ያሉትና ለምርጫ ቅርብ የሆኑት ግን እነሱ ናቸው። በርግጥ በተመሳሳይ ለችግሩና ለዱላው ቅርብ መሆናቸው ሳያግዛቸው አልቀረም። እስካሁን በውጪ ሆነው የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች በጋራ ትግሉን የሚያካሂዱበትን አንድ አይነት ትብብር ማቆም ግን አልቻሉበትም። ችግር የሆነው ትግሉን አስተባብሮ በተቀናጀ መልክ ማስኬድ አለመቻላቸው ብቻ ግን አይደልም። ትግሉ በዚህ አይነት ፖለቲካዊ ውሳኔዎችም መታገዝ ነበረበት። የጋራ መድረክ ማቆም ስላልቻሉ ብዙ የዚህ አይንት የጋራ ውሳኔን የሚፈልጉ ጉዳዬች ውሳኔ የሚሰጥባቸው አጥተው ተወዝፈው ነው ያሉት። ትግሉን ደግሞ ወደፊት እንዳይሄድ ቀፍድደው ይዘውታል። ድርጅቶች በተናጠል የተወሰኑት ላይ ውሳኔ ለማድረግ ቢሞክሩም አይሰራም። አንዳንዶቹ ደግሞ በበቂ ውጤታማ አይሆኑም። አገር ውስጥ ላሉ ህጋዊና ሰላማዊ ድርጅቶች ጉልበት የሚሆናቸውን ሙሉ እውቅና የመስጠቱ ጉዳይ ላይ ግን ተባብረው ቢያደርጉት ይመረጣል እንጂ በተናጠል ቢያደርጉትም በደንብ የሚሰራ ነው። በይበልጥ በአገር ውስጥ ፖለቲካ እንዳይሳተፉ የታገድና የተከለከሉ ሁለገብ ትግልን ምርጫ ያደረጉ ድርጅቶች አፅኖት ሰተው ሊያስቡበት የሚገባ ነው።

በውጪ ያሉ ድርጅቶች ወደፊትም ቢሆን ተቀምጠው መምከር ከቻሉ የሚነጋገሩበትን ጉዳይ መምረጥ አለባቸው። በፖሊሲ ጉዳይ ላይ፤ ምርጫ በሚያደርጉት የትግል አይነት፤ አገራዊ ፍልስፍና ጨምቆ ለማውጣት፤ በበዛ ሁኔታ ሽግግር ጉዳይ ላይ ወይ ከወያኔ በሗላ የሚኖሩ ችግሮች መፍትሄ ለማስቀመጥ ባይሆን እመረጣለው። ምክንያቱም አሁን ስለማይቻልና ለነዚህ በቂ ጊዜ ስላለ ብቻ ነው። ማሸነፍ ለሚባለው ዋና ጉዳይ እሩቅ ነው ያለነው። ማሸነፍ እንደሚችሉ እርግጠኛ ሳይሆኑና ሳይቃረቡ በዚህ አይነት ታላቅ አገራዊ ቁም ነገሮች ላይ የሚያስማማ ነገር ላይ መድረስ እንደስካሁኑ ወጡ ሳይወጠወጥ እየሆነ የምር ሊወሰድት አልተቻለም። እስቲ ትግሉን አቀናጅተው አሸናፊ የሚያደርጉበት ብለሀት ላይ ለማነጋገር ይጀምሩ። በርግጠኛነት ይስማማሉ። ተቀራርበው መስራት ሲጀምሩ ደግሞ ተራራ አድርገው የሚወስዷቸው ጉዳዬች መስመር እየያዙ እየጠፉ ይሄዳሉ።

በተረፈ ሌላ አይነት በአገር ውስጥና መሰረታቸውን በውጪ ያደረጉ አጋር ድርጅቶች መሀል ወያኔ ሊገነባው የሚያስበውን ግንብ ሊያፈርሱበት የሚችሉበት፤ ትግላቸውን ሊያስተባብሩበትና ሊያቀናጁበት የሚችሉባቸው መንገዶች ይኖሩ ይሆናል። ይሰሩ ይሆናል ብዬ ያየሗቸው ብለሀቶች በሙሉ አሁን ባለው ያገራችን ፖለቲካዊ ሁኔታ ትግሉን የሚያወሳስቡበት ጎን አላቸው። በርግጥ በምርጫ 97 ትልቅ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የነበረው የብዙ ድርጅቶች የተካተቱበት ህብረት ጥሩ ድልድይ ሆኖ ሲያገለግል ነበር። በነበረው አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥም ህልውናውን በአገር ውስጥ ለማስቀጠል በቂ ጥረት ተደርጎ ቢሆን እንዴት ጠቃሚ ነበር። አሁንም ተመሳሳይነት ያለው ትብብር ከተቻለ መሞከሩ አይከፋም። ሁሉም ድርጅቶች ባይሆኑ የዚህ አይነት ትብብር ለማቆም የሚችሉ ድርጅቶች በውጪ አሉ።
በህጋዊና በሰላማዊ መንገድ በአገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች መፍትሄ ሰሪ፤ አቅራቢና ተዋኝ መሆን አለባቸው ።

ህጋዊ ተቃዋሚ መሆን ማለት ጠቅለል ተደርጎ ሲታይ ቀጣይ መንግስት ለመሆን እየሰራና እየተዘጋጀ ያለ አካል ማለት ነው። አገር ቤት ያሉ ህጋዊ ተቃዋሚ ደርጅቶቻችን በአሉበት የከፋ አፈና ውስጥም እንደቀጣይ መንግስት ለመተወን የሚቻልበት እድሉ አለ። ህጋዊ ተቃዋሚ ሆነው እስከቀጠሉ አማራጭ ሆኖ መታየትን የግድ አሳምረው ሊሰሩት ይገባል። እስከእስካሁኑ እንደ ቀጣይ መንግስት ሲተውኑ ግን አይታይም። በህዝብ አመኔታንና አማራጭ እየሆኑ መታየት የሚጀምሩት እንደ ቀጣይ መንግስት መተወንን ሲጠበቡበትና የሚታይ እየሆነ ሲሄዱ ብቻ ነው። እስካሁን ስልጣን ላይ ያለውን አገዛዝ አጋላጭ የህዝብ ብሶት አቅራቢ በቃ ተቃዋሚዎች ብቻ ናቸው። ዋንኛው ምክንያት ቀጣይ መንግስት የመሆኑን ጉዳይ ህዝብ ሊያጤነው በሚችል ደረጃ ለነሱም እርቆ የሚታያቸው መሆኑ ነው። ይህ መቀየር አለበት። በእርግጥ አፈናውን ያልተባበረ ተቃዋሚ የነበሩ መሆናቸው የራሱ አስተዋፆ አድርጓል።

ለምሳሌ የእስልምና እምነት ዜጎቻችን በጣም ቀላል የመብት ጥያቄዎች አንስተዋል። አገዛዙ ሙስሊሙን ማህበረሰብ በሙሉ አሸባሪ ሲል ሰይሞ ጥያቄያቸውን መመለስን መደፈር አድርጎ ወስዶታል። አሸባሪዎች ብዬ በገፍ ገድዬና አስሬ ጭጭ አሰኛቸዋለው የሚለውን መንገድ ምርጫው አድርጓል። በሌላ በኩል ተቃዋሚዎች የስልምና እምነት ተከታይ ዜጎች ያነሷቸው ጥያቄዎች ቀላል የመብት ጥያቄዎች መሆናቸውን ይስማማሉ። መንግስት ቅራኔውን ሊፈታ ያሰበበት የሀይል መንገድ ያወግዛሉ። ጥያቄዎቻቸውን በሰላማዊ መንገድ እያቀረቡ እንደሆነም መስክረዋል።

ይህ ከሆነ ታዲያ በዚህስ መንገድ አስተናግደውትስ ቢሆን። የእስልምና እምነት ተከታይ ዜጎች ያነሷቸው ጥያቄዎች አንድ ሁለት ብለው ዘርዝረው እነዚህ ናቸው። እነዚህ ቀላልና ህጋዊ የመብት ጥያቄዎች ናቸው። በተጨማሪም ጥያቄዎቹ በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ የቀረቡ ስለሆኑ ገዥው ፓርቲ በአስቸኳይ ሊመልስላቸው ይገባል። እንደግመዋለን በአስቸኳይ ሊመልስላቸው ይገባል። ገዥው ፓርቲ ደም ካላፈሰስኩበት የሚለውን ችግር በኛ በኩል በርግጠኝነት በቀላሉ ሰላማዊ መፍትሄ ልንሰራለት የምንችለው ነው። የስልምና እምነት ተከታይ ዜጎቻችን ያቀረባችሗችሗቸውን ጥያቄዎች ሲጀመር ጥያቄ መሆን አልነበረባቸውም። ለነዚህ ጥያቄዎች ይህን ያህል መታገላችሁ ያስቆጨናል። በኛበኩል ሁሉንም ጥያቄዎች በጠየቃችሁት መሰረት እንመልሳቸው ነበር። ስልጣን ላይ ያለው ፓርቲ በመግደልና በገፍ ሰብስቦ በማሰር ጥያቄዎቹን አዳፍናለሁ ካለ የሀይሉን መንገድ ምርጫው ስላደረገና ስለፈለገ ብቻ እንጂ ጥያቄዎቹ ሊመለሱ የማይችሉ ስለሆኑ ወይ የሊሎች ዜጎችን መበት በምንም መንገድ የሚጋፋ ሰለሆነ እንዳልሆነ እውቀናል። እዚህ ጉዳይ ላይ ህዝባችንም ግንዛቤ እንዲኖረው እንፈልጋለን። እነዚህን ቀላል የመብት ጥያቄዎች በሀይል ሊፈታ ማሰቡ በራሱ ገዥው ፓርቲ የማስተዳደር ችሎታ እንዴሌለው በግልፅ የሚያሳይ ነው። መላው የኢትዮጵያ ህዝብ መብታቸውን የጠየቁ የስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችሁ ድህንነት መንግስት እወስዳለው በሚለው እርምጃ ምክንያት እጅጉኑ የሚያሳስብ ደረጃ ላይ መድረሱን ይገንዘብ። ሂደቱንም አፅኖት ሰጥታችሁ ተከታታሉ። በሚችለው አቅም የመንግስትን የእብደት እርምጃ ለማስቆም መሞከር አለበት። በኛ በኩል ስልጣን ላይ ያለው ፓርቲ እነዚህን ቀላል የመብት ጥያቄዎች መልሶ ችግሩን መፍታት ከከበደው ንፁሀን ዜጎችን ያላአግባብ ከሚፈጅ ስልጣኑን በቶሎ በህዝብ ለተመረጠ መንግስት አሁኑነ እንዲያስረክብ እንጠይቃለን። መንግስት በማን አለብኝነት ሊፈፅም የሚያስበውን ወንጀል አምርረን የምንታገለው መሆኑን ግልፅ እናደርጋለን። የሚል አንድምታ ኖሮትስ ቢሆን።

በሁለቱ አቀራረብ ላይ ያለው ልዩነት እስካሁን ተቃዋሚዎች የያዙት አቋም ስህተት መሆኑ አይደለም። ነግር ግን እዚህ ቀላል ጉዳይ ላይ እንኳ እነሱ እንዴት ችግሩን እንደሚፈቱት ወይ መፍትሄ ይሰሩለት እንደነበር አልፈውታል። አገዛዙ ለመፍጀት ቀጠሮ ሰጥቶ እያለ እንዲህ ብለህ እንዳትገድል መሆን ሲገባው ሁሉም እስኪጨፍጭፍ ጠብቀው ነው ያወገዙት። የሁሉንም ድርጅቶች መግለጫዎች ከመረመርን ይዘታቸው አገዛዙን የመጨፍጫፍ አባዜ በበቂ አያሳዩም። ሁሉም ዜጋ ችግሩን እንዲከታታል መፍትሄውም ላይ በንቃት እንዲሳተፍ አይጋብዙም። የመግለጫዎቹ ይዘት አገዛዙን አያገልም። አንዳንዶቹ እንደውም ሆን በሎ ችግር ከሚፈጥር አካል መፍትሄ አፅኖት ሰጥተው ይጠይቃሉ። በአጠቃላይ ጥሩ ተቃዋሚ እንጂ ቀጣይና አማራጭ መንግስት አድርጎ አላሳያቸውም። በህዝብ ዘንድም አመኔታንና አማራጭ ሆኖ የመታየት የፖለቲካዊ ጉዳይ ላይ ይህን አይነቱ የእስካሁኑ አያያዛቸው አልጠቀመም። ተቃዋሚዎች ችግሩን እነሱ የሚፈቱበትን መንገድ ግልፅ ብሎ በሚታይ መንገድ ቢያካትቱ ኖሮ ጅራፍ እራሱ ገርፎ አይነት በገደላቸው፤ ባሰራቸውና በቀጠቀጣቸው ንፁሀን ሊሸማቀቁ በተገባ ነበር። የልብ ልብ ባንሰጣቸው ንፁሀንን መግደላችሁ አግባብ አይደለም ያሉትን ተቃዋሚዎች ተመልሰው ተሞዳመዳችሁ ብለው ሊያሸማቅቁ ባልዳዳቸው ነበር። ፈራ ተባ እየተባለ የሚደረግ ነግር ጦሱ ብዙ ነው። ነገ ደግሞ በዚሁ ሰበበ ከውስጣቸው የተወሰኑትን አገዛዙ አስሮ ማሰቃየቱ አይቀርም።

ለማንኛውም ወደ ጀመርኩት ጉዳይ ልመለስና መሰረታቸውን በውጪ አድርገው ለለውጥ እየታገሉ ያሉ ወይ የተለየ የትግል አይነት ምርጫ ያደረጉ ድርጅቶችን በሚመለከት በህጋዊ መንገድ በአገር ውስጥ እየተንቀሳቀሱ ያሉ ድርጅቶች የመናገር እድሉን ባገኙ ወይ በተጠየቁ ቁጥር ሁኔታው የተፈጠረበትን ምክንያትና ያለውን እውነታ እንቅጭ እንቅጩን እንዲሰማ አድርገው ደጋግመው ከመናገር ጎን ለጎን በዋናነት ማድረግ ያለባቸው እንደቀጣይ መንግስት የራሳቸውን መፍትሄ አቅራቢ፤ ሰሪና ተዋኝ መሆን ነው። አገዛዙ መፍትሄ አድረጎ ከያዘው ህግ ማምረት፤ ጦርነት ማወጅ፤ ፊልም መስራት፤ መግደልና ማሰር የተለየ ሰላማዊ መፍትሄ አለን ነው ብለሀቱ። የጎደለውም ይህ ነው።

ዜጎች የሀይሉን መንገድ የመረጡት አፋኝና ጨካኝ አንባገነን ስለሆንክ ነው። ከዜጎች ጋር ገባሁበት የምትላቸው ችግሮች ባንተ አንባገነናዊነት ምክንያት የተፈጠሩ ናቸው። ሰላማዊ መፍትሄ መስራት ካልቻልክ ስልጣኑን ላኛ አሳልፍ። እኛ ሰላማዊ መፍትሄ ልንሰራበት ቀላላችን ነው የሚመስሉ አገላለፆች በዝተው መሰማት አለባቸው። እነዚህ ሁሉ በጭራሽ ያልተጋነኑም እውነትነትም ያላቸው ናቸው። ለነገሩ ግን የፖለቲካ ትግል ውስጥ ትልቁን ድርሻ የሚወስደው የቃላት ጫወታ መጫወቱን እወቁበት። ችግሩ ላይ አውደ ጥናቶች፤ የምክክር መድረኮችን በተደጋጋሚ አዘጋጁ። ምሁራኖችን ጋብዙ፤ ህዝብን አወያዩ ባጠቃላይ የመፍትሄ ተቃዋሚ ሁኑ።

የተከበሩ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ በኢሰት ራዲዮ ቀርበው ከህዝብ ለቀረበላቸው ጥያቄ ቀጥተኛ መለስ በሚሰጡበት ጊዜ ዛሬ መፍትሄ ብዬ በአቀረብኩት እነዚሁ ጉዳዬች ላይ የመጠየቅ እድሉን አግኝቼ ነበር። በጊዜውም ጥያቄውን ያቀረብኩት አጥጋቢ መለስ ያኔውኑ ይሰጡበታል ብዬ ሳይሆን ሀሳቡ ህዝብ ዘንድ ይድረስ። ይዘውትም ይሄዳሉ በማለት ነው። በርግጥ በጊዜው ቀዳሚ የመፍትሄ እርምጃ አገር ውስጥ ካሉ ህጋዊ ድርጅቶች ሊፈልቅ ይችላል ወይ ያንድ ወገን ብቻ መፍትሄ አለው የሚል የተሳሳተ እይታም ነበረኝ።

ጥያቄው የነበረው። አገዛዙ በውጪ ሆነውና በተለየ መንገድ የሚታገሉትን ድርጅቶች ጦርነት ናፋቂ አሸባሪ እያለ እየወነጀለ ነው። በዚህ ሰበብ በህጋዊ መንገድ መብታቸውን የሚጠይቁ ዜጎችን ያናንተንም አባለት ጨምሮ አስሮ እያንገላታ ነው። ወያኔ ይህን ችግር አስሬ ገድዬ እፈታለው ብሏል። እንደቀጣይ መንግስትና ህጋዊ ተቃዋሚ ወያኔ ከሚከሳቸው ድርጅቶች ጋር ሰላማዊ መፍትሄ ለምን ለማስቀመጥ አትሞክሩም። ይህንን ሰል በጭራሽ በድብብቆሽ የሚሰራውን አይደለም። እንደ አንድ አገራዊ ችግር አይታችሁት በግልፅ መፍትሄ ልትሰሩለት ስለሚገባ ጉዳይ ነው የሚል ነበር።


አቶ ግርማ ሰይፉ – የአንድነት ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር በዲሲ ሜትሮ ለአንድነት አባላትና ደጋፊዎች ያደረጉት ንግግር

$
0
0

የተከበራችሁ የዲሲ እና አካባቢው ነዋሪዎች
እንዲሁም የነፃነት ወዳጆች
ዛሬ ለዚህ መድረክ የማስተላልፈውን መልዕክት ከምን እንደምጀምር ሳስብ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል መርዕ የተጀመረውን ህዝባዊ መነሳሳት መፍጠሪያ መድረክ እንደሚሆን ጥርጥር አልነበረኝም፤ ነገር ግን ሀገር ውስጥ በሚታተም አንድ መፅሄት ላይ ወጥቶ ለንባብ የበቃውን የአንዱዓለም አረጋጌን “የሐምሌ ጨረቃ” መጣጥፍ ሳነብና የእርሱን የሰለማዊነት መንፈስ ለገዥዎቻችን ግን የአሸባሪነት ድምፅ ትንሽ ማለት እንዳለብኝ ተሰምቶኛል፡፡ የአንዱዓለም መዝሙር የእኛም መዝሙር ስለሆነ፡፡ በገዢው ፓርቲ እና በእኛ በኩል ከፍተኛ ደረጃ የደረሰ የመደማመጥ ችግር እንዳለም ማሳየ ነው፡፡ ሰለ ሰላም የሚዘምርን ሰው አሽባሪ ለማለት ያለ የሌለ ጉልበታቸውን ያባክናሉ፡፡

በቅርቡ ብዙዎቻችሁ በሚዲያ እንዳያችሁት “የፀረ አሸባሪነት ህግና የፓርቲዎች አቋም” በሚል ርዕስ ውይይት ተደርጎ ነበር፡፡ ይህ ውይይት በእኛ እምነት “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” የሚለው ዘመቻ ካሰገኛቸው ውጤቶች አንዱ ነው ብለን ነው የምናምነው፡፡ በ2001 የፀደቀን አዋጅ እንደገና ወደ መድረክ ማምጣ መቻል ትልቅ ነገር ነው፡፡ ይህ የቴሌቪዥን ውይይት ተቆርጦ ተቀጥሎ የቀረበ ቢሆንም አንድነት ነጥብ አስቆጥሮ የወጣበት ነው፣ በዚህ ውይይት የፀረ አሸባሪነት ህጉ ዜጎችን ከአሸባሪ ጥቃት ለመታደግ ሳይሆን ኢህአዴግ ድምቸውን የሚያሰሙ ዜጎችን ማፈኛ እና ሲከፋም ህዝቡን የሚያሸብርበት እንደሆነ ለህዝብ ይፋ ተደርጎዋል፡፡

ከህዝብ በሚሰበሰብ ግብር የሚተዳደሩ ሚዲያዎች የአንድ ፓርቲ ወገንተኛ ሆነው ሲያገለግሉ ማየት በሀገራችን ኢትዮጵያ መደብኛ እና ትክክል እስኪመስል ድረስ የዕለት ተዕለት ተግባር ሆኖዋል፡፡ እዚህ ማንሳት የፈለኩት በሚዲያ የተላለፈው ዝግጅት የእነ አንዱዓለምና እስክንድር እንዲሁም ሌሎች የፖለቲካና የእሊና እስረኞች ስም የተነሳበት ቦታ በሙሉ ከተቆረጠና ከወጣ በኋላ ነው፡፡ ኢህአዴግ አንዱዓለምን ውጭ ሆኖ ሲታጋል ሳይሆን በሚዲያም ሰሙ ሲጠራ ይፈራል ማለት ነው፡፡ የአንዱዓለም እስር በምንም ዓይነት ከአሸባሪነት ጋር የተያያዘ እንዳልሆነ ስለሚያውቁ ሰማቸው ሲነሳ መንፈሳቸው ይረበሻል፡፡ በፈንጂ የሞቱ ሰዎችን ፊልም እያሳዩ፣ በአሸባሪነት የከሰሱና እሰከ እድሜ ልክ እስር የፈረዱባቸው አንዱዓለም እና እስክንድር ግን ብዕር ይዘው ነው የታሰሩት፡፡

አንዱዓለም የታሰረው ሹሞች በሁለት ሺ ሁለት ምርጫ በያዙበት ቂም ነው ብለን ነው የምናምነው፡፡ አንዱዓለም ግን በተቃራኒው እስር ቤት የወረወሩትን ሰዎች በፍቅር ለማሸነፍ እንደሚቻል ከእስር ቤት ሆኖ ሰለ ሰላም ይሰብካል፡፡ በተቃራኒው የኢህአዴግ ሹሞች ሰለ እነ አንዱዓለምና እስክንድር መናገር አሸባሪነትን በተዘዋዋሪ ድጋፍ እንደማድረግ ነው በሚል አንገታችንን ሊያስደፉን ይፈልጋሉ፡፡ በዚህ አጋጣሚ እኛም የአንዱዓለምን የሰላማዊ ትግል መንፈስና ጥንካሬ ሊኖረን እንደሚገባ አሰረግጨ መናገር እፈልጋለሁ፡፡ ሰለማዊ ትግል የሚሞትለት እንጂ ግዳይ ተጥሎ የሚፎከርለት አይደለም፡፡ የምንሞትለት እንጂ የምንገልበት አንድም በቂ ምክንያት አይኖረንም የለንምም፡፡ የሰላማዊ ትግል ጀግንነት ለሞት ጭምር ደፍሮ ለመግደል ፈሪ መሆንን ነው፡፡

የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት ዘመቻ ይህን ሰላማዊ ትግል ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሳደግ መሰረት የሚጣልበት ይሆናል ብለን አምነን ነው የተነሳነው፡፡ የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት አይጋ ፎረም እና ደጋፊዎቹ እንደሚሉት ሚሊዮን ፊርማ አሰባሰቦ የፀረ አሸባሪነት ህግ እንዲሰረዝ ግፊት ማድረግ ብቻ ሳይሆን፣ ሌሎች ሚሊዮኖች ነፃ መሆናቸውን የሚያሳዩበት የህዝብ ንቅናቄ ነው ፣ ይህ ለሁላችን ግልፅ እንዲሆን በአጭሩ ላስረዳ፤
• ሚሊዮኖች ፊርማቸውን በግልፅ በማኖር ከፍርኃት ነፃ መሆናቸውን ያሳያሉ፤
• ሚሊዮኖች ህዝባዊ ስብሰባ እና ሰላማዊ ሰልፍ በመሳተፍ ድምቸውን
• ሚሊዮኖች ይህን እንቅስቃሴ ፋይናንሰ በማድረግ በገንዘብ ወይም በእውቀታቸው እና በጉልበታቸው ይሳተፋሉ
• በመግቢያ እንዳነሳሁት በፀረ አሸባሪ ህግ ሰለባ የሆኑትን ታሳሪዎች በግንባር ተገኝቶ መጠየቅ ማበረታት
• ቤተሰቦቻቸውን በሁሉም መልኩ መደገፍ የነፃነት መገለጫ ነው፡፡

እነዚህን ማስፈራሪያዎች በጣጥሶ ወጥቶ የነፃነት ጌታ መሆን ያሰፈልጋ፡፡ ከዚህ በላይ የተዘረዘሩት ደፍሮ ማድረግ የቻለ አንድ ኢትዮጵያዊ መብቱ ሲነካ እንቢ በቃኝ ለማለት ድፍረት ያገኛል የሚል እምነት አለን፡፡ ሚሊዮኖች በአንድ ወይም በሌላው ለነፃነታቸው መቆማቸው ገዢዎች በፍርሃት ቆፈን ውስጥ አድርገው የሚገዙበት ሁኔታ እንዲያበቃ ዕድል ይፈጥራል፡፡ ለነፃነት ለሚደረገው ትግልም በቂ የሰው ሀይል እና በማቴሪያል ለማሰባሰብ እና ትግሉን ወደፊት ለመምራት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡

ሰላማዊ ትግል ለምን ውጤት አላመጣም ለሚለው ጥያቄ የሰላማዊ ትግል የገባው ሰራዊት ማፍራት ያለመቻላችን ዋነኛው መንስዔ ሲሆን የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት ለዚህ ተገቢውን ምላሽ ይሰጣል የሚል ተሰፋ ሰንቀን ነው የጀመርነው፡፡ ዛሬ በዚህ ቤት የተገኛችሁ ሁሉ ይህን ድምፅ ተቀላቅላችሁዋል ብዬ መውሰድ እችላለሁ፡፡ በተለምዶ ከምናውቀው የጦርና ጎራዴ፤ የፈረስና ታንክ፣ ጅግንነት ወደ የሰላመዊ ትግል ጀግንነት ልዕልና ልናሳድገው ይገባል፡፡ ለእኛ እን አንዱዓለም ናትናኤልና እስክንድር የሰላማዊ ትግል ጀግኖቻችን ናቸው፡፡ ዛሬም በወህኒ ቤት ሆነው ብዕራቸው ፍቅርና ሰላምን ይሰብካል፡፡ በቀልን ያወግዛል፡፡ የሰላማዊ ትግል ጀግንነት የሚወዱህን በመውደድ ሳይሆን የሚጠሉህን ጨቋኞች ለሰላም እጃቸውን እንዲዘረጉ ሰላማዊ በመሆን ነው፡፡

የዛሬ አራት ወር አካባቢ በዲሲ ተገኝቼ በኢትዮጵያ ሙስሊሞች ሰላማዊ እንቅሰቃሴ ብዙ እንደምንማር ነግሬያችሁ እንደነበር አስታውሳለሁ፤ አሁንም ብዙ የምንማረው ነገር ቢኖርም እሰከ አሁን ባደረግነው እንቅስቃሴ ሰላማዊ አድርገን እንቅስቃሴያችንን ለመምራት የቻልነው ግርግር ሳንፈጥር መልዕክት ማሰተላለፍ እንደምንችል ለደጋፊዎቻችን እንደምሳሌ በማሳየት ነው፡፡ ይህ ብቻ አይደለም መዋቅራችን አስፍተን መስራትና ሁሉንም የኢትዮጵያ ክፍል ለመድረስ የምንችለውን ለማድረግ በቁርጠኝነት በመስራታችን ነው፡፡ ይህ በቀላሉ የተገኘ ሳይሆን ባለፉት ሁለት ዓመታት በስትራቴጅክ እቅድ በተቀመጠቅ መሰረት ዘላቂነት ያለው መዋቅር ለመግንባት ባደረግነው እንቅስቃሴ የተገኘ ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ ሙስሊሞች በፖለቲካው ተሳትፎ ከዚህ በፊቱ በላቀ ሁኔታ በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ ይህ ግን ገዢውን ፓርቲ አላስደሰተውም፡፡ ያስደስተዋል ተብሎች አይጠበቅም፡፡ ለዚህም ነው ዘወትር እምነትና ፖለቲካ ቀላቀላችሁ እያለ ፕሮፓጋንዳ የሚነዛው፡፡

የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት ዘመቻ እንደሚታወቀው በመስከረም 5 በሚደረግ የአደባባይ ስብሰባ እንደሚጠናቀቅ እና ከዚህ እንቅስቃሴ በተገኘው ተሞክሮ በመነሳት ሌላ ዕቅድ የሚወጣ ሲሆን በሁሉም መመዛኛ እሰከ ዛሬ የተደረገው እንቅስቃሴ ግን በሀገር ውስጥ የተንሰራፋውን ልክ ያጣ ፍርሃት ድባብ ለመግፈፍ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረ ለዚህም በሁሉም መስክ ድጋፍ ያደረጋችሁ ሁሉ ልትኮሩ ይገባችሁዋል፡፡ ወደፊትም በውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያዊያ የአቅማችሁን በማድረግ ትግሉን ማገዝ ምርጫ ሳይሆን ግዴታ መሆኑን መረዳት ይኖርባቸዋል፡፡ ማስገደጃውም አብሮን ያለው የህሊና ፍርድ ነው፡፡ ከሃላፊነት ለመሸሽ ምንም ዓይነት ሰበብ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡

በመጨረሻም በሀገራችን ኢትዮጵያ ያለው አምባገነን ሰርዓት እንዲወገድ ፍላጎት ያለን ሁሉ ማድረግ ያለብን ከፍርሃት የተላቀቀ ዜጋ ከማበርከት ጎን ለጎን በድፍረት ወንጀልን ከመስራት የሚቆጠብም ጭምር እንዲሆን በማድረግ ነው፡፡ የወንጅል ስር የሚጀምረው ደግሞ ከመጠላላት፣ ከቂምና በቀል ነው፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ ባለፉት አርባ ዓመታት ለለውጥ ፍላጎት ያላቸው ልጆቿ በተለያየ ጎራ ተሰልፈው መስዋዕትነት ከፍለዋል፡፡ ከመስዋዕትነት የተረፉት አሁን በተለያየ ጎራ ተሰልፈው ይገኛሉ፡፡ አሁንም በውል ያልተቋጨ የእርስ በእርስ ያለመተማመን፣ መፈራትና የአሸናፊነትና የተሸናፊነት ሰነ ልቦናዎች በፖለቲካው ሜዳ ላይ ገዢ ሆነው ይታያሉ፡፡ እነዚህን ወደ ጎን ትተን ሀገራዊ መግባባት የምንፈጥርበት ምቹ ሁኔታ መፍጠር ይኖርብናል፡፡ ይህ ደግሞ ሊሆን የሚችለው በመከበባር እና ተቀራርቦ በመነጋገር እንጂ በመናናቅ እና በስድብ ሊሆን አይችልም፡፡ በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን የመሳሪያ ሀይልን የጉዳይ ማስፈፀሚያ መሳሪያ አድርጎ መውሰድ በየትኛውም መመዘኛ ጠቃሚ አይደለም፡፡

“በስልጣን ምክንያት ህወሓት ለሁለት የተከፈለ ይመስለኛል” – አቶ ገብሩ አስራት (ቃለ ምልልስ)

$
0
0

ሐገር ቤት የሚታተመው ሎሚ መጽሔት አቶ ገብሩ አስራትን በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አነጋግሯቸዋል። ዘ-ሐበሻ ለአንባቢዎቿ ይጠቅማል በሚል እንደወረደ አቅርባዋለች።

ገብሩ አስራት 1

ሎሚ፡- ባለፈው መቀሌ ላይ “አረና” ሕዝባዊ ስብሰባ አከናውኖ ነበር፡፡ የነበረው ሁኔታ በአጠቃላይ ምን ይመስል ነበር;
አቶ ገብሩ፡- እንግዲህ የመቀሌውን ስብሰባ ከሁለት ጉዳዮች አንፃር ልንመለከተው እንችላለን፡፡ አንዱ ሕዝቡ እንዴት እንደተቀበለው ስብሰባውን … ሁለተኛው መንግስት ወይም በክልሉ ያለው ፓርቲ ስብሰባው እንዳይካሄድ ያደረጉትን ጫና በተመለከተ መመልከት ይቻላል፡፡ እንግዲህ አስቀድሜም መንግስት ስብሰባው እንዳይካሄድ የፈጠረውን ጫና ነው የማየው፡፡ እንግዲህ ትግራይ ውስጥ ገዢው ፓርቲ ህወሓት ነው፡፡ ህወሓት ከእሱ ውጭ ሌላ ፓርቲ እዛ ቦታ ላይ እንዲንቀሳቀስ ፍላጐት የለውም፡፡ ይህም ባፈለው 2002 ዓ.ም. በተካሄው ምርጫ ጠ/ሚ መለስ ትግራይ ውስጥ ምንም አይነት ክፍተት መኖር የለበትም፣ ምንም አይነት የሀሣብ ልዩነት መኖር የለበትም ብለው የተናገሩበትና በርካታ ስድቦች የተሰነዘረበት በተለይም በ”አረና” ላይ በርካታ ስድቦችን ያወረዱበት ጊዜ ነበር፡፡ እንግዲህ አሁን ያለው አመራርም የእሣቸውን “ሌጋሲ” ፈለግ እከተላለሁ የሚል ስለሆነ አካሄዱ ተመሳሳይ ነው፡፡ በትግራይ ውስጥ ምንም አይነት የፖለቲካ አስተሳሰብ እንዲኖር አይፈልግም፡፡ በህገ መንግስትም ፣ በቃልም ተቃዋሚ ቢኖር አንጠላም ሊሉ ይችላሉ፡፡ ዋናው ስጋታቸው በአካባቢው የተለየ ሀሣብ ፣የተለየ አመለካከት ፣ የተለየ አደረጃጀት እንዳይኖር ስጋትና ጭንቀት ያለባቸው ስለሆነ አጠቃላይ ድርጅቱን በእነሱ ስር የተደራጀ ሲቪክ ማህበረሰብ፣ የመንግስት ድርጅቶችን አደራጅተው ነው አንድ ፓርቲ በዛ አካባቢ ስብሰባ እንዳያካሂድ የሚያደርጉት፡፡ ባለፈው ጊዜም ስብሰባ ስናካሂድ እንደውም እነሱ በሚመሯቸው ድርጅቶች ፣ ኩባንያዎች /ኢፈርት/ ሠራተኞችን ሰብስበው በዚህ ስብሰባ ላይ መገኘት ከጠላት ጋር እንደማበር ይታሰባል ብለዋቸዋል፡፡ እና ስለዚህ ስራ ለማግኘት አትችሉም፣ ስጋት ላይ ትወድቃላችሁ ፣ ከጠላት ጋር የመተባበር ያህል አድርገን ነው የምናየው ሲሉ ነው የተናገሩት፡፡

ይህንን ካሉ በኋላም በዚህም አላበቃም በኢትዮጵያ የምርጫ ሕግ መሠረት እንደተፈቀደው ማንም ፓርቲ ሊቀሰቅስ ይችላል፡፡ መቀስቀስ የማይችለው በትምህርት ቤትና በቤተ እምነት ቦታ ውስጥ እንጂ በሌላ ቦታ ድምፅ ማጉያ ተጠቅሞ መቀስቀስ ይችላል የሚል ነገር አለ፡፡ መቀሌ ላይ ግን ሌላ ህግ አውጥተዋል ወይም አውጥተናል ነው የሚሉት፡፡ እኛ ግን አላየነውም፣ ህጉ ምንድነው የሚለው ማንኛውም እንቅስቃሴን ማጉያ ተጠቅሞ መቀስቀስ አይቻልም ነው የሚሉት፡፡ ይሄ እንግዲህ ከሀገሪቱ ህግ ፣ ከፌዴራል ህግ ጋር የሚጣረዝ ህግ ነው፡፡ ህግም ቢሆን ማለቴ ነው፡፡ ማውጣትም አይችሉም፡፡ እንደዚህ ያለ የምርጫ ቦርድ ሕግ እያለ መንግስት ወይም አስተዳደር ይሄንን ህግ ሊያወጣ አይችል፡፡ እኛ ህግ አውጥተናልና መንቀሣቀስ አትችሉም እያሉ ነው የሚናገሩት፡፡ ለምን ስንላቸው ደግሞ ድምፅ ማጉያው ማለት ነፍሰ ጡሮችንና በሽተኞችን ሊያውክ ስለሚችል መናገር አይቻልም ፡፡ በዛ ምክንያት ነው የከለከል ነው ይላሉ፡፡ ያም ሆኖ ግን መስኪዶች፣ ቤተክርስቲያኖች በድምፅ ማጉያ መልእክት ያስተላልፋሉ፡፡ ራሣቸው ህውሓቶችም በድምፅ ማጉያ ዳንኪራ እየመቱ የሚያጥለቀልቁበት ሁኔታ አለ፡፡ ለተቃዋሚዎች ነው ያልተፈቀደው እንጂ ራሣቸው በማይክራፎን ከተማውን የሚያውክ ነገር ይጠቀማሉ፡፡ ስለዚህ በዚህ ምክንያት ያንን ከለከሉን፡፡ እና ይሄ ህግ ይፈቅድልናል ብለው የኛ አባላትም ተንቀሣቀሱ፡፡ ግን አሰሯቸው፡፡ ሁለት ሦስት ጊዜም ነው ይህንን ያደረጉት፡፡ ሹፌሮችንና የተከራየነውንም መኪና አገቱ፡፡ ስለዚህ በዚህ መልኩ ስብሰባ እንዳይካሄድ አግተዋል፡፡ በንጋታው ደግሞ ስብሰባ ስናካሂድ እያንዳንዱ የቀበሌ አስተዳደር ማን እንደሚገባ እንዲመለከት እዛ አሰልፈዋቸው ነበር፡፡ አብዛኞቹም ሴቶች ናቸው፡፡ /የቀበሌ ሴቶች/ እነዚህን አሠልፈው ማነው ወደዚህ ስብሰባ የሚገባው የሚል ሊስት ይዘው አስቀመጡ፡፡
ጭራሽ ስብሰባ እንዳይካሄድ ነው የሞከሩት፡፡ በሌላም እያንደንዱ ቀበሌ ለሕዝቡ ስብስባ እንዲመጣ በፅሁፍ ጭምር ደርሰው እንድትገኙ የሚል አስተላለፉ ….የምንናገረው ስለመልካም አስተዳደር ፣ ስለ ንግድ ምናምን ነው ብለው መቅረታ የለባችሁም ወሣኝ ስብሰባ ነው ብለው ፣ እኛ ስብሰባ በምናደርግበት ቀን እነሱም ስብሰባ ጠሩ፡፡ ይሄ አካሄድ ደግሞ ምንም አይነት ሰው ወደኛ እንዳይመጣ የማድረግ አላማ ያለው ነው፡፡ ያም ሆኖ ግን ሕዝቡ ፍላጐት ነበረው እንዲያውም ስብሰባውን እንድናካሂድ ግፊቱ የመጣው ከሕዝቡ ነበር፡፡ ያም ሆኖ እነሱ ባይከለክሉት ኖሮ አዳራሹም አይችልም ቦታም አይበቃም ነበር፡፡ ይሄም ሆኖ ወጣቱ ይሄን ሰብሮና ጥሶ አድራሹን ሞልቶታል፡፡ እና እዚህ ላይ ለማለት የምፈልገው በተለይ በሁለት ጉዳዮች ላይ እኛ ያቀረብነው በከተማ የሊዝ አዋጆች ላይ ፣ በነጋዴዎች የግብር ጫና፣ በዜጐች ሰብአዊ መብት እጦት እንደዚህ እንደዚህ ያሉ በርካታ ጉዳዮች ላይ ነው፡፡ ሕዝቡ ግን ትኩረት አድርጐ ያቀረበው ነፃነቱን እንደተነፈገ ነው፡፡ ትግራይም ውስጥ እንደተነፈጉ ተናጋሪዎች ናቸው፡፡ እኛ ንግግሩን ጀመርነው እንጂ የጨረሰው እዛ የተሰበሰበው ሕዝብ ነው፡፡
ገብሩ አስራት ሌላው ደግሞ ይሄ የሊዝ መሬት ዜጐችን ጭሰኛ ለማድረግ እየሞከረ እንዳለ በአፅንኦት ተናግረዋል፡፡ መሬታችንን ቀሙን፣ በወላጆቻቸው /ውርስ/ ያገኙት መሬት ላይ ዋስትና እንዳጡ ፣ ይህንንም ተናገሩ፡፡ እንግዲህ የሚገርመው ስብሰባውን በፀሎት ለመጀመር ነው ፕሮግራም የያዝነው፡፡ ሁሉም የስብሰባው ታዳሚ ተነስቶ ለሰማእታት ፀሎት ሲያደርግ አንድ ወጣት ግን ከመቀመጫው ሣይነሳ ቁጭ ብሏል፡፡ ኋላ ላይ ግን ለምን በፀሎቱ ወቅት እንደተቀመጠ ምክንያቱን ተናገረ፡፡ ይሄ ወጣት ሲናገር “እኔ እናንተ ለምን ተነስታችሁ እንደምትፀልዩ አልገባኝም፡፡ ምክንያቱም እኔ አባቴ በትግሉ ተሰውቷል፣ ወንድሜና እህቴ ተሰውተዋል፡፡ ግን ያመጡልን ምንም ነገር የለም፡፡ ለምንድነው የምፀልየው; እኔ የምፀልየው ኢትዮጵያው ውስጥ ነፃነት ሲረጋገጥ፣ መብት ሲረጋገጥ ነው እንጂ አሁን ቆሜ አልፀልይም፡፡ ቤተሰቦቼ የተሰዉበት ሁሉ ተግባራዊ እየሆነ አይደለም፡፡ አፈና ፣ ሙስና ይህንን ለማምጣት ከሆነ የተሰዉት አልፀልይም፡፡ የምፀልየው ኢትዮጵያ ውስጥ ነፃነት ሲረጋገጥ ብቻ ነው” ብሏል፡፡ ይህ ንግግር ተሰብሳቢውን በጣም ያስገረመ ንግግር ነው የነበረው፡፡በአጠቃላይ መንግስትና የክልል ፓርቲ ስብሰባ እንዳይካሄድ ሕዝቡ ሌላ አማራጭ እንዳይሰማ ቢያደርጉም ሕዝቡ ግን ከፍተኛ ፍላጐት ነበረው፡፡ እንዲያውም እኛ ካሰብነው ጊዜ በላይ ተወያይቶ በጥሩ ሁኔታ ስብሰባውን አጠናቀናል፡፡
ሎሚ፡- አንዳንድን ዘገባዎች አሉ ይህ በሕዝብ ውስጥ የሚባለው ነው መረጃውን በእርስዎ አንደበት የማስተላለፉ መልእክት ደግሞ የእርስዎ ይሆናል፡፡ አረና ጥሩ እየተንቀሣቀሰ ቢሆንም የአባላቶቹ ወደ አሜሪካ መጓዝ በፓርቲው ላይ ችግር አይኖረውም ወይ የአቶ ስዬ እና የአቶ አሰግድን የሚያነሱ ሰዎች አሉ;
አቶ ገብሩ፡- ይሄ ምናልባትም የመረጃ ጉዳይ እንዳይሆን ለመናገር እሞክራለሁ፡፡ አቶ ስዬ የአረና አባል አይደሉም፡፡ የአንድነት አባል ናቸው፡፡ አቶ አስግድም ተመልሰዋል፡፡ አሁን ትግራይ ውስጥ ነው ያሉት፡፡ ስለዚህ የእኛ አባል ሆኖ ከሀገር ውጭ የሚገኝ የለም፡፡ ስለዚህ ይህን መረጃ ሕዝብ እንዲያውቀው ይገባል፡፡
ሎሚ፡- በህወሓት ውስጥ እውነት ልዩነት አለ; ህወሓት ለሁት ተከፍሏል የሚባል ነገር አለ ይሄን እንዴት ይገልፁታል;
አቶ ገብሩ፡- እኔ እንግዲህ በፖለቲካ ምክንያት ፣ በፖለቲካ ልዩነት ምክንያት ህወሓት ውስጥ መከፋፈል አልተመለከትኩም፡፡ ያም ሆኖ በስልጣን ምክንያት ህወሓት የተከፈለ ይመስላል፡፡ ይህም የታየው መቼ ነው ባለፈው የፓርቲው ጉባኤ በተካሄደበት ጊዜ ነባሮቹን ሙሉበሙሉ ጠራርጐ አስወጥቷል፡፡ ካድሬዎቹ ይሄ የሆነው ምንድነው ህወሓት ውስጥ የተጠናከረው በካድሬ ደረጃ አባል ነው ስልጣኑን የተቆጣጠረው እንጂ ራሱ ሀሣብ ሊያመነጭ የሚችል ፣ ሀሣብን ሊቀምር የሚችል፣ ንድፈ ሀሣብን በደንብ ተገንዝቦ ሊያስረዳ የሚችል ኃይል ህወሓት ውስጥ አሁን የለም፡፡ ከፋም በጀም የተሻለ አቅም ያላቸው ሰዎች ከዚህ ተገለዋል ብሎ መናገር ይቻላል፡፡ ስለዚህ የስልጣን ሽግሽግ ነው ለዚህ ያነሱት፡፡ ይህንን መሠረት አድርገው ነባር የተባሉትን ጠራርገው አስወጡ፡፡ እዚህ ላይ ግን ነባር የተባሉትንና ተጠርገው ከወጡት እኩል በፓርቲው ረጅም እድሜ ያላቸው ደግሞ እዛው ቀርተዋል፡፡ ስለዚህ ነገሩ የስልጣን ሽኩቻ ይመስላል ብሎ መናገር ይቻላል፡፡
ሎሚ፡- አሁን የኃይል ሚዛኑ የትኛው ክፍል ጋር ነው;
አቶ ገብሩ፡- ይሄ ኢትዮጵያ ውስጥ በጣም አስቸጋሪ ነገር ነው፡፡ እንግዲህ የኢትዮጵያ ፖለቲካና ስልጣን የተመሠረተው በማን ላይ ነው የሚለውን መመልከቱ ጥሩ ነው፡፡ ሦስት አካሎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ አንዱ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ማየት ይቻላል፡፡ ሁለት የመንግስት አካላት፣ ሦስተኛው መከላከያና የደህንነት አካላትን ነው ማየት የሚቻለው፡፡ አቶ መለስ በነበሩበት ጊዜ እነዚህ ሦስት አካላትን ተቆጣጥረው የሄዱበት ጊዜ ነበር፡፡ እንግዲህ የአቶ መለስ መንግስት አምባገነን መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ እንደ አምባገነንነቱም ሁሉንም የስልጣን አካላት ተቆጣጥረው በእጃቸው ውስጥ አስገብተው ቆይተዋል፡፡ እንደውም አሁን ኢህአዴግ ተዳክሟል የሚያሰኘው ምንድን ነው በአንድ ሰው ተሰባስቦ ፣ የአንድ ሰው ፈላጭ ቆራጭ፣ ስልጣን የነበረው አሁን ተበታትኗል፡፡ ከስልት አንፃር ይሄ መዳከምን ያሣያል፡፡ ይህ ከሆነ በኋላ ስልጣኑ የት ላይ ነው የሚለው ነገር በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ እንደ አቶ መለስ ተጠናክሮ የወጣ ሰው የለም፡፡ የአቶ መለስ ፍላጐት ቀድሞም ምንድነው የፑቲን አይነት አስተዳደር ነው በዚህች ሀገር ላይ ፍላጐታቸው የነበረው፡፡ ደካማውን ፊት ላይ አስቀምጠው እሣቸው ከኋላ ሊነዱት ነበር አቶ ኃ/ማርያምንና ሌሎችንም ወደ ስልጣን ያመጡት፡፡
ያም ሆኖ ግን እሣቸው አልቆዩም፡፡ አቶ ኃ/ማርያም በዚህ አጋጣሚ ስልጣን ያዙ፡፡ አሁን አቶ ኃ/ማርያም መከላከያውንና ደህንነቱን በእጃቸው ለመቆጣጠር ይችላሉ 1111 የሞራል ብቃትስ አላቸወይ; የፖለቲካው ብቃትስ አላቸወይ; የሚለው ጥያቄ የሚያስነሳ ነገር ነው፡፡ ፓርቲውንስ ቢሆን እንግዲህ ነባሮች ዳግም ተመልሰዋል ብአዴን ውስጥ አቶ መለስ እያሉ ውጡ ተብለው ታዘው ወጥተው የነበሩትም እንደገና ተመልሰው መጥተዋል፡፡ እነዚህንስ ለማዘዝ ይችላሉ ወይ;ከፍተኛ ውሣኔዎች ላይ የማዘዝ አቅም ይኖራቸዋል ወይ; የሚለው አንድ ጥያቄ ነው፡፡ እንግዲህ በመንግስት የሚባሉት ፣ በፓርላማ፣ በካቤኔ ውስጥ የዚህ ነፀብራቅ ነው፡፡በደህንነቱ፣ በመከላከያው የማዘዝ ስልጣን ከሌለህ በመንግስት ውስጥም የማዘዝ ችሎታህ አነስተኛ ነው ማለት ነው፡፡ ስለዚህ አሁን ችግሩ የስልጣን ክምችት በአንድ አካል ላይ አለ፡፡ ይሄ ነው የሚወሰነው፡፡ ደህንነቱም ሆነ መከላከያው ትልቅ ተፅእኖ አለው በኢትዮጵያ፡፡ እንደውም ወሳኙ እሱ ነው፡፡ እሱን ማዘዝ፣ ማሰማራት ፣ እሱን መቆጣጠር የማይችል ኃይል በኢትዮጵያ የፖለቲካ ኃይል ይዣለሁ ማለት አይችልም፡፡ ይህንንስ ማድረግ ይችላል ወይ; አሁን ያለው አመራር ለሚለው ነገር ጥያቄ ውስጥ ያስገባል፡፡ ፓርቲዎችም ቢሆን ከአቶ መለስ ሞት በኋላ የየራሣቸው ነፃነትና መብት ለማስከበር አዝማሚያም እየታየባቸው ነው፡፡ የብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ህወሓት በአጠቃላይ የፖለቲካ ሂደት ላይ ተፅእኖ ለማሣደር እየሞከሩ ነው ያሉት፡፡ በይፋ ያልወጣ ሽኩቻ እየታየ ነው፡፡ ውስጥ ለውስጥ፡፡ ድሮ የነበረው የአንድ ግለሰብ ተፅእኖ አሁን የመሰበር ሁኔታዎች ነው ያሉት፡፡ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ሁሉንም ለመወሰን ኃይሉም አቅሙም ያለው የለም፡፡ የሚፈለገው እሱ ነው ወይ ሌላ ጥያቄ ሊሆን ይችላል፡፡ ይሄ የአቶ መለስ ሌጋሲ የሚባለው ግን እንደዛ ያለ ሰው ካልፈጠረ በስተቀር ጥንካሬ አለው ብሎ ለማለት አይቻልም፡፡
ሎሚ፡- አሁን እንግዲህ በስርአቱ ውስጥ ሙስና በከፍተኛ ሁኔታ መንሰራፋቱ ይነገራል፣ የሚታይም ነገር ነው፡፡ከሀገር ውጭም ገንዘብ የማሸሽ ሁኔታ አለ ይሄን እንዴት ይመለከቱታል;
አቶ ገብሩ፡- እንግዲህ ሁልጊዜም እንደምለው ራሱ የሙስና ምንጭ በኢትዮጵያ ያለው የሙስና ምንጭ የለሚው ነገር ካልታወቀ መፍትሄም አይገኝለትም፡፡ ኢህአዴግ ሙስናን እየታገልኩ ብሎ ለማስመሰል የተወሰኑ ባለስልጣኖችንና ነጋዴዎችን ያስራል፡፡ ይፈታል፡፡ ግን ይሄ መፍትሄ ነው ወይ; በኢትዮጵያ የሙስና ምንጭ መሠረት የሆነው እነዚህ ነጋዴዎች ናቸው ወይ; የተወሰኑ ባለስልጣናት ናቸው ወይ; የሚለውን ነገር ማንሣቱ የሚጠቅም ይመስለኛል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ሙስና ሊቀንስ፣ ሊቃለል የሚችለው ከስርአቱ ጋር በቀጥታ ተያያዥነት አለው፡፡ የአንድ ስርአት ፓርቲ አገዛዝ ከሆነ ዞሮ ዞሮ ሙስናን ነው የሚያነግሰው፡፡ደጋፊዎቹን ያጠናክራል፣ በሀብት ያጠናክራል፣ በገንዘብ ያጠናክራል፣ ፖሊሲው ነው፡፡ አባሎቼ የሚላቸውን ቢሰርቅ ፣ ቢዘርፍ ምንም ሊላቸው አይችልም፡፡ ፖለቲካውን የሚቃወሙ ሊነካኩ የሚችሉ ሰዎች አንዳንድ ጊዜም በሰውም ምንም ለውጥ አያመጣም ብሎ የሚያስባቸውን ሰዎች በሙስና ይቀጣል እንጂ ከመሠረቱ ስርአቱ ነው፡፡
እንደሚታወቀው ይሄ በውጭ ሀገር ገንዘብ አላቸው ወይ; አስቀምጠዋል ወይ; የሚለው ነገር በተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን የአለም ተቋማት እንደሚነገረው የሸሸው ገንዘብ በርካታ ነው፡፡ ይሄ ገንዘብ የማነው የኔ ነው የሚል ባይታወቅም በኢትዮጵያ በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እየሸሸ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ ግን ወደዛ መሄድ አያስፈልግም፡፡ እዚህ ሀገር ያለው ሀብት ከየት መጣ የሚለው ነገር ቢጠየቅ እኮ መልስ የለም፡፡ሰርቶ ነው ወይ; ከደሞዙ ነው; በተለይ አንድ የመንግስት ባለስልጣን ትላልቅ ቤቶችን የሚያሰራ ደሞዝ አለው ወይ; ህንፃዎችን የሚያሰራ ደሞዝ አለው ወይ; ብዙ ሀብት ቤተሰቦቹን በከፍተኛ ደረጃ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ውጭ ድረስ ልኮ የሚያስተምር ደሞዝ አለው ወይ ተብለው ቢጠየቁ የኢህአዴግ አመራሮች መልስ የላቸውም፡፡ ስለዚህ ሙስናው የራሱ የስርአቱ ባህሪ ነው፡፡ ምክንያቱም ሙስናን እንታገል ቢባል፣ ኢህአዴግ በሚከተለው አግባብ እንዴት ሙስናን መታገል ይቻላል; ነፃ ማህበረሰብ ፣ ሲቪል ማህበረሰብ በሌለበት እኮ ይሄ ሙሳኝ አለ ብሎ መቃወም አይቻልም፡፡ ጠንካራ ነፃ ጋዜጦች “Invest get journalism”መስራት በማይቻልበት ሁኔታ እንዴት ነው ሙስናን መዋጋት የሚቻለው; የመንግስት ተጠያቂነት ግልፅነት በሌለበት እንዴትነው ሙስናን መታገል የሚቻለው; ሕዝብ ሰልፍ ወጥቶ መቃወም በማይችልበት፣ ተሰብስቦ መነጋገር በማይችልበት እንዴት ነው ሙስናን መታገል የሚቻለው; ስርአቱ በባህሪው አምባገነናዊ ስርአት ነው፡፡ “አብዮታዊ ዴሞክራሲ” ብሎ የአንድ ፓርቲ ፈላጭ ቆራጭነት አረጋግጣለሁ የሚል መንግስት ከሙስና አይነፃም፡፡ ነፃ ሊሆን አይችልም፡፡ በአለምም ያየነው፣ በአፍሪካም የሚታየው ፓርቲዎች የህብረተሰቡን እንቅስቃስቃሴ በሙሉ “ገዢ ፓርቲዎች” ሕዝቡ ትንፍሽ እንዳይል ፣ እንዳያጋልጥ የሚያደርጉ ናቸው፡፡ ኢህአዴግም ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ መታየት ያለበት የአንድና ሁለት ባለስልጣን የማሰርና የማጋለጥ ጉዳይ አይደለም፡፡ ዋናው ነገር ስርአቱ በቁርጠኝነት መታገል የሚችል እስከሆነ ብቻ ነው፡፡ ይሄንን ደግሞ ኢህአዴግ አይችልም ያውቀዋል፡፡
የኢትዮጵያ መሬት እንደተዘረፈ ያውቃል፡፡ እሱ ነው የሚያዘርፈው፡፡ የመንግስት በጀት እንደተዘረፍ ያወቃል ግን እራሱ ነው የሚያዘርፈው፣ የመንግስት ልማት ተቋማት በሚሊዮኖች ይዘረፋሉ ያውቃል መንግስት ግን መፍትሄ የለውም፡፡ መፍትሄም ከኢህአዴግ ይመጣል ብሎ ማሰብ የዋህነት ይሆናል፡፡ ምንም ሊመጣ አይችልም፡፡
ለዚህም ነው ከአመት አመት እየተባባሰ እንደውም አሁን የስርአቱ ዋና መገለጫ እየሆነ ያለው ከዚህ በመነሣት ነውና፡፡ አንድ እንደ አቅጣጫ መታየት ያለበት፣ መረሳት የሌለበት ሙስና ከስርአቱ የሚመነጭ ስለሆነ ፣ በፀረ ሙስና በኩል የተወሰኑትን በማሰር የሚቋጭ አይደለም፡፡ሰፊ ነፃነት፣ሰፊ መብት፣ ጠንካራ የህግ የበላይነት፣ ነፃ ባለስልጣኖችን ሊጠይቅ ሊያስር የሚችል አቃቢ ህግ “ነፃነት ያለው” ፍርድ ቤት ሊወስንባቸው የሚችል ያለምንም ተፅእኖ ከሌለ ሙስናን መታገል እንዴት ይቻላል፡፡ ስለዚህ ታዩታላችሁ ሙስና ኢህአዴግ እስካለ ድረስ እየባሰበት የሚሄድ ይሆናል፡፡ አሁን ተራ ሙስና አይደለም የማፍያ አይነት የተደራጀ ሙስና ነው እየተካሄድ ያለው፡፡
ሎሚ፡- እንደታዘቡት ከሆነ ፣የሙስሊሙ ጥያቄ አለ ይሄን እንዴት ይመለከቱታል; ሌላው ከቅርብ ቀናት ወዲህ በመንግስት በኩል አክራሪነት ፣ ሽብርተኝነት፣ አሸባሪነት የሚሉ ቃላት ይሰማል ይሄስ በእርስዎ እይታ እንዴት ታዘቡት;
አቶ ገብሩ፡- እንግዲህ በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙ ጊዜ ተናግረናል፡፡ እኔ እንግዲህ ኢህአዴግ አንዳንድ ችግሮች ሲነሱ የሚሄድበት አግባብ ችግሮች አሉበት፡፡ የሙስሊሙ ጥያቄ ፣ የአባይ ጥያቄ፣ የብሔር ብሔረሰቦች ጥያቄ እነዚህ በዚህ አገር ከባድ ጥያቄዎች ናቸው፡፡ በተለይ በሙስሊሞች ጉዳይ መታየት ያለበት ካለው ማህበረሰባዊ እድገት፣ አለም አቀፋዊ ሁኔታ መንገድ ነው መታየት ያለበት፡፡እንግዲህ የሙስሊሞች ጥያቄ መታየት የጀመረው እኮ መለስ በነበረበት ጊዜ ነው፡፡ እንደማስታውሰው እኔ ከተለያዩ የአለም ክፍሎች የተውጣጡ ፣ የሙስሊም አባላት መጥተው ከአቶ መለስ ጋር ተገናኝተዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የሙስሊሞች አያያዝ የሚያሳስባቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ጥያቄዎችም ያኔ አንስተዋል፡፡ ካነሷቸው ጥያቄዎች መሀል፣ የበአላት ማክበር፣ ወለድ የሌለው ባንክ የመክፈት ጉዳይ እንዲህ እንዲህ ያሉ ወደ አስር የሚጠጉ ጥያቄዎች አንስተው ነበር፡፡ በወቅቱ እናየዋለን የሚል መልስ ነው የተሰጣቸው፡፡ ከዛ በኋላ የታየም ነገር የለም፡፡ ውስጥ ለውስጥ የሚነሱ ጉዳዮች አሉ፡፡ ብዙ የመብት ጥያቄዎች፡፡ ይሄ እያለ ግን ኢህአዴግ ይሄን የሚያባብስ እርምጃ ወስዷል፡፡ ምንድነው እንደምታስታውሰው በተለይ “ፌድራል ጉዳዮች” የሚባል የመንግስት አካል የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን በሌላ ሙስሊም ለማስጠመቅ ሙከራ አደረገ፡፡ “አልሀበሽ” የሚባል ገንዘብ አውጥቶ ይሄን ተማሩት አለ፡፡ እያንዳንዱ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሙስሊም በዚህ ውስጥ እንዲጠመቅ ሙከራ አደረገ፡፡ ሙስሊሞች ተቃወሙት ፣ ሃረር ላይ ….. ሚኒስትሩ ሣይቀር ስብሰባ አደረገ፡፡ ይሄ ጣልቃ ገብነት ነው፡፡ …. አንድን ኃይማኖት በሌላ ኃይማኖት በዚህ እመን ማለት ጣልቃ ገብነት ነው፡፡ ያለጥርጥር ነገሩ ከዚህ ተነሣ ከዛ የአወሊያ ትምህርት ቤትም ተነሣ ይሄ የቆየ ነው፡፡ ድሮ የነበረ ትምህርት ቤት ነው፡፡ ያንን ለመቆጣጠር ሞከረ፣ ያም አይሆንም የሚል ምላሽ ቀረበ፡፡
እንደገና የምርጫ ጉዳይ ተነሣ፡፡ ቀላል ጥያቄ በጣም ቀላል …. ምርጫው በመስኪዶች ይሁን የሚል፡፡ ይሄ ሁሉ ኢህአዴግ የማያዝበት መንገድ ግን ሽንፈት ነው የሚመስለው፡፡ አንዳንዶቹን ጥያቄዎች መመለስ ሽንፈት ስለሚመስለው ነገሩን ያጦዘዋል፡፡ ወደ አስቸጋሪ ሁኔታ ይገፋዋል፡፡ የኢትዮጵያን ሙስሊሞች እንደማውቃቸው በመሠረቱ በጣም ተቻችለው በመኖር ተግባብተው በመኖር የሚታወቁ ሙስሊሞች ናቸው፡፡ የሱፊ እምነት ፣ ካተሚያ እምነት በኢትዮጵያ ያለው ተቻችሎ የኖረና የሚኖር ሙስሊም ነው፡፡ ያም ሆኖ ግን ልክ በክርስቲያኑ ውስጥ እንደሚታየው ድሮ የሚታወቁት ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክ አልፎ አልፎ የድሮ ፕሮቴስታንቶች ይታወቁ ነበር፡፡ በኋላ ላይ ግን ጴንጤዎች መጡ፣ ሌሎችም መጡ፣ ጆባ መጣ ይሄ በነበረው አይን ሲታይ ፅንፈኛ ነው እና ክርስቲያኑ ሁሉ ያኔ ተደናገጠ ግን ሊያቆመው አይችልም፡፡ ከአለም ጋር ይገናኛል፡፡ ሕዝቡ ብዙ ብዙ እምነቶች አሉ ተቀብሎ ያምናል፡፡ በሙስሊምም የሚሆነው ይሄ ነው፡፡ ዋህቢያ መጣ፣ ሳላፊ መጣ ሌሎችም ሌሎችም ሺሀ ሊነሳ ይችላል፡፡ ይሄ እንግዲህ መንግስትም ይሁን ማንም ሊያቆመው አይችልም ይሄንን ዝንባሌ፡፡ መንግስት ማድረግ ያለበት እነዚህ አስተያየቶች፣ እነዚህ መስመሮች፣ ከህገ መንግስቱ ወጥተው፣ ሰላም እንዲኖር፣ መረጋጋት እንዳይጠፋ መቆጣጠር እንጂ ከዛ ባለፈ ይሄ እምነት ነው ትክክለኛ ይሄ ደግሞ ትክክለኛ አይደለም ብሎ መናገር መብቱ አይደለም፡፡ ማስተማርም የለበትም፡፡ ግን ኢህአዴግ ትንሹን ነገር አግዝፎ ስለሚያየው ነው፡፡ ኢህአዴግ መንግስት ሆኖ ከግለሰብ ጋር እየተጣላ የሚውል መንግስት ነው፡፡ በጣም ነው የሚያሣዝነው፡፡ አይንቀውም ትንሽ ነገር ነው እቆጣጠረዋለሁ ብሎ አያምንም፡፡ ሰራዊትይዞ ፣ ስፍር ቁጥር የሌለው ፌድራል ፖሊስ ፣ የክልል ፖሊስ፣ የፀጥታ ኃይሎች ይዞ እያለ በሁለት ሦስት ሰዎች እየተሸበረ ነው ያለው፡፡ ኢህአዴግ ሽብር ነው ውስጡ ያለው፡፡ ስለዚህ በሙስሊሙ ይሄ ነገር ሲነሳ ይሸበራል፡፡ ሲሸበር ደግሞ ለዚህ ምላሽ የሚሰጠው በማተራመስ ነው እንጂ ነገሮችን ከስትራጄክ አንፃር አያያቸውም፡፡ ሰልፍ ያስወጣል፣ አገሪቱን በሙሉ በስብሰባ ያስወግዛል፣ በየቀበሌው ፣በየከተማው …. አውግዙ ይሄ መፍትሄ አይሆንም ፣ ሰልፍ ውጡ ይሄ ፕሮፖጋንዳ ነው፡፡ከፕሮፖጋንዳ በዘለለ ነው መታየት ያለበት፡፡ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ሲነሱ በስትራ
ቴጂክ እንጂ በፕሮፖጋንዳ ሊፈቱ አይችሉም፡፡ ምን ማለቴ ነው የአባይ ጉዳይ ሲነሳ ያነሣነው ነገር ነበር፡፡ አባይን ስንነካ አንድ ስትራቴጂክ ጉዳይ ነው ለኛ …. ስትራቴጂክ ጉዳይ ስለሆነ በአንድ ፓርቲ ፣ በአንድ ክፍል ብቻ መፍትሄ የሚያመጣ አይደለም፡፡ መግባባት ያስፈልጋል፡፡ ተቃዋሚዎች ሁሉ ለዚህች ሀገር ኃላፊነት አለብን የሚሉ ተግባብተው መሄድ አለባቸው፡፡ ምክንያቱም ይሄንን ትልቅ ነገር ከነኩ በኋላ ተባብረው መስራት እንጂ የሚያስፈልገው እንዲሁ “አካኪ ዘራፍ” ብሎ ማሰናበት አይቻልም፡፡ የሙስሊም ጥያቄ ሲነሳ እኔ ኢህአዴግ እንደሚያየው አያስደነግጠኝም፡፡ ያን ያህል የሚያስደነግጥ ፣ የሚያስፈራ፣ የሚያሸብር ነገር የለም፡፡ መቆጣጠር የሚቻል ነው፡፡ ያም እሱ በሚያስበው ችግር ቢኖራም፣ እሱ ባወጣው የፕሮፖጋንዳ አቅጣጫ መመራት ሣይሆን ፣ እስቲ እንነጋገርበት ሙስሊሞችን ሲያነጋገር አንዱን ክፍል ብቻ ማነጋገር የለበትም፣ ሁሉንም አነጋግሮ መፍታት ይችላል፡፡ ከተቃዋሚዎችም ጋር ቢሆን መቶ በመቶ የሚቃወሙትንም ማነጋገር እንጂ የራሱን ደጋፊዎች ብቻ አንድ የዩንቨርስቲ ምሁር ማናገር ተገቢ አይደለም፡፡ ስለኔ ምን ይላል ብሎ የተለየ ሀሣብ ሊያገኝ ይችላል፡፡ ስለዚህ የሙስሊሙም ጥያቄ ከአጠቃላይ የዴሞክራሲና የሰብአዊ መብት ጋር ተያይዞ መታየት ያለበት ነው የሚመስለኝ፡፡

ጳጉሜ 2, 2005 የሙዚቃ ቃና ፐሮግራም( September 14,2013) –ሴፕቴምበር 09, 2013

$
0
0
የዚህ ሳምንት የሙዚቃ ቃና ፐሮግራም የተለያዩ ምርጥ ምርጥ ዜማዎችን ያካተተ ሲሆን በ Billboard ሰንጠረዥ ላይ የበላይንቱን የያዙትን ዜማዎችን ጨምሮ ሙዚቃ ነክ ዜናዎችንም አካቷል፡፡…

የሳምንቱ የስፖርት ዘገባ

$
0
0
ብራዚል ውስጥ ለሚካሄደው የዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር የአፍሪቃ እና የአውሮፓ አገሮች ማጣሪያ ውድድር፣ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ሲካሄዱ ቆይተዋል።…

Hiber Radio: በኑሮ ውድነቱ ሳቢያ የዓመት በዓል ገበያው ቀዝቅዟል

$
0
0

የህብር ሬዲዮ ዕሁድ ጳጉሜ 3 ቀን 2005 ፕሮግራም

እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሰዎ

በዓሉ የሰላምና የጤና እንዲሆን መልካም ምኞታችን ነው !

<... ሎስ አንጀለስ ሊትል ኢትዮጵያ ተብሎ በስሙ በውጭ አገር መንገድ የተሰየመለት ብቸኛ ቦታ ነው። በዚህ ተሰባስበን ኢትዮጵያውያን የአዲስ ዓመት በዓልን እናከብራለን።ይሄ በሎስ አንጀለስ ብቻ ሳይሆን በርካታ ኢትዮጵያውያን ባሉባቸው ቦታዎች መጠሪያችንን ማኖር ይቻላል...>

በሎስ አንጀለስ ዕንቁጣጣሽን አስመልክቶ የተከበረውን ዓመታዊ ፌስቲቫል አስመልክቶ ሊትል ኢትዮጵያ እንዲሰየም ጥረት ካደረጉት አምስት ሴቶች አንዱዋ ሜሮን አሀዱ ለህብር ከሰጠችው ቃለ መጠይቅ የተወሰደ

<<...በናዝሬት/አዳማ ሰልፉ ከመደረጉ በፊትና በሰልፉም ወቅት የተለያዩ ተጽኖዎች ነበሩ። እነዛን ተቋቁመን ከ15 ሺህ በላይ የከተማዋ ነዋሪ አደባባይ ወጥቶ ሶስት ኪሎ ሜትር ያህል በከተማዋ መንገዶች ተዘዋውሮ ተቃውሞውን አሰምቷል።...ሕዝቡ የራሱን መፈክር ያሰማና ብሶቱን ይገልጽ ነበር...ይህ እንቅስቃሴ ነጻነት እስኪገኝ ድረስ የሚቀጥል ነው...>>

አቶ ዳንኤል ተፈራ የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ የሃዝሬት/አዳማውን ሰልፍ አስመልክቶ ለህብር ከሰጡት ቃለ መጠይቅ የተወሰደ።ለዲያስፖራው የአዲስ ዓመት መልክታቸውም ተካቷል።

ልዩ የበዓል መሰናዶ አካተናል

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

<<...ይሄ መንግስት እኮ በህክምና ቋንቋ ሞቷል። የቀረው ቀብሩ እንዴት ነው የሚፈጸመው የሚለው ነው...>> አባ መላ በቬጋስ የአዲስ ድምጽ አገራዊ ጉባዔ ላይ ተገኝቶ ከሰጠው ማብራሪያ (የተወሰነውን አካተነዋል)

<<...የበዓል አመጋገባችን በተለይ ቅባት የበዛበት ነገር ማብዛቱ ለጤና ጉዳት አለው። በእነዚህ ላይ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል...በተለይ ለአዲሱ ዓመት አምስት ምክሮች አሉኝ እነዚህም...>>

ዶ/ር ኤፍሬም መኮንን ከአትላንታ የበዓል አመጋገባችን መሰረት አድርገን አነጋግረናቸው ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)

(ሌሎችም ቃለ መጠይቆች አሉን)

ዜናዎቻችን

በኑሮ ውድነቱ ሳቢያ የበዓል ገበያው ቀዝቅዟል

ዶሮ 180 ብር፣በግ መካከለኛ 1500 ብር፣ በሬ ከ10 ሺህ እስከ 15 ሺህ ብር አንድ ዕንቁላል 2 ብር ከ70ሳንቲም ተሽጧል

አሜሪካ ሶሪያን ማጥቃቱዋ በኢትዮጵያ ንግድ ላይ ተጽዕኖ ይፈጥራል ተባለ

የኢንጂነር ሀይሉ ሻውል <<ሕይወቴና የፖለቲካ እርምጃዬ>> የተሰኘው መጽሐፍ ነገ ለንባብ ይበቃል

የኢራን ዲፕሎማት ኦባማ ሲሪያን ካጠቁ አንዱዋን ልጃቸው ትታፈናለች ሲሉ አስጠነቀቁ

የኢትዮጵአው ዋልያ በሰሞኑ ድል የብራዚል ጉዞውን እያመቻቸ ነው

ሌሎችም ዜናዎች አሉን

Viewing all 13695 articles
Browse latest View live